Tuesday, June 3, 2014

Ethiopian and Eritrean migrants detained in Libya



(Aljazeera) – About 200 migrants, mostly from Ethiopia and Eritrea, have been detained in Zawiya west of Tripoli as they tried to cross to Europe while hidden in vehicles, Libyan officials have said.
The migrants were hidden in boxes inside a vehicle to be smuggled out of Tripoli
The migrants were hidden in boxes inside a vehicle to be smuggled out of Tripoli [AFP]
“Two hundred migrants, including 160 men and 40 women from Ethiopia and Eritrea, were captured. They were hiding in soap boxes,” Nassir al-Shebani, head of legal affairs in the west brigade of Zawiya area, said.
The people were hidden in boxes inside a vehicle to be smuggled outside the capital.
Many migrants from sub-Saharan Africa head to North Africa to escape desperate conditions in their own countries, hoping to find work there or risk a perilous journey to Europe.
The Mediterranean can be treacherous in the autumn and winter months, making spring and summer the best time for small boats with ill-equipped crews to cross the sea.
Italy alone rescued 4,000 migrants from boats trying to reach European shores in early April. At that point 15,000 migrants had already arrived there by sea since the start of the year.
Western powers say instability in post-Gaddafi Libya may have encouraged human traffickers to exploit the country’s lawlessness.
Since the overthrow of Muammar Gaddafi in 2011, the number of migrants passing through Libya has risen sharply and the country’s coastguard and army are ill-equipped to stem the tide.

አገራዊ ስሜት ለምን ይጎድለናል?





በተክሉ አባተ
ከበርካታ ሳምንታት በፊት ከጓደኞቼ ጋር ኢትዮጵያ ስላለችበት ወቅታዊ ሁኔታ እየተወያየን ነበር:: ሁሉም ተሳታፊ የተስማማበት ጉዳይ ቢኖር ኢትዮጵያ ከምንም ጊዜ በላይ እጅግ ከባድ ማኅበራዊ ምጣኔ ሃብታዊና ፖለቲካዊ ቀውስ ውስጥ መግባቷን ነበር:: ለዚህም በግንባር ቀደምነት ተጠያቂው መንግስት እንደሆነ ቢሰመርበትም ህዝቡም ላለንበት ሁኔታ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ታላቅ አስተዋጽዖ እያደረገ እንደሚገኝ ተወስቷል::እንዲያውም ኢትዮጵያውያን ለአገርና ለለውጥ ያላቸው ስሜት እንደ በረዶ የቀዘቀዘ እንደሆነ ተነገረ:: ለዬት ያለና ታላቅ አገራዊና ወገናዊ ጉዳይ ሲነገር ህዝቡ ጸጥ ረጭ ብሎ ሰምቶ ሃሳቡን ሳይሰጥ ሹልክ እያለ እንደሚወጣ ሁሉም የታዘበውን እያነሳ ተናገረ:: ብዙዎች ለወገናቸው ጥልቅ ስሜት ስለሌላቸውና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በንቃት ስለማይሳተፉም መንግስት በጭቆናው እንዲቀጥል ሞራልና ጉልበት እየሰጡት እንደሆነም ተጨመረበት::
ከቀናት በኋላ በሌላ መድረክ ፋንታው የሚባል ወንድሜ ለኦስሎ ነዋሪዎች ከላከው ደብዳቤ ውስጥ “ለነገሩ ብዙ ኢትዮጵያዊ ሰው ለብዙ ነገር ስሜት የለውም” የሚል ትችት አገኘሁ:: ይህ በቀላሉ የማይታለፍ ጉዳይ እንደሆነና ውይይት እንደሚያስፈልገው በማመን ጸሃፊውን ቀጥለው በተዘረዘሩት ጥያቄዎች ዙሪያ ልምዱንና እውቀቱን እንዲያካፍለን ተማጸንኩት::
  • ሰው ስሜት የለውም ስንል ምን ማለታችን ነው?
  • የስሜት አለመኖር ምክንያቱና መንስዔው ምንድን ነው?
  • የስሜት አለመኖር የሚያስከትለው ጉዳት ወይም ጣጣ ምንድን ነው?
  • ስሜት-አልባነትን እንዴት ማጥፋት ወይም መቀነስ ይቻላል?
  • ስሜት-አልባነትን ለማጥፋት ወይም ለመቀነስ በሚደረግ ትግል ዋና ተዋንያን እነማን ናቸው?
የስሜት ያለህ!
አቶ ፋንታውም “የኢትዮጵያዊ ስራና ጥልቅ ስሜት አቅም” በሚል ርዕስ ይበል የሚያሰኝ ትንታኔ አቀረበ:: ስሜትን በሁለት ከፍሎ አብራራ:: ሃሳባዊ ስሜት “ከልባችን ለመውደድና በአእምሮአችን ለመረዳት በዙሪያችን በሚከሰቱ ነገሮች ላይ የምናሳየው ጥልቅ ፍላጎትና የምናደርገው ግንኙነት ነው”::ስሜት በልብ ወይም በአእምሮ ተወስኖ የሚቀር ሳይሆን በሥራ እንደሚገለጥም ምሳሌ እያነሳ አብራርቷል:: የስሜት አለመኖር የሚያስከትለውን መዘዝም ከእድገትና ለውጥ ካለመኖር አኳያ አጠር አድርጎ አንስቷል:: ጽሁፉን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ::
እኔም ፋንታው ባነሳቸው ባብዛኞች ሃሳቦች እስማማለሁ:: በዚህ ጽሁፍ አገባብ ስሜት ማለት በአካባቢያችንና በአገራችን ዙሪያ የሚነሱ ጉዳዮችን በነቃ አእምሮ ተከታትሎና መርምሮ የራስን ግንዛቤ መውሰድ ከዚያም የሚገባውን አስተዋጽዖ ማድረግ እንደሆነም እስማማለሁ:: በስብሰባዎችና የውይይትመድረኮች መሳተፍ: የፖለቲካ ወይም የሲቪል ተቋማትን መምራት ወይም አባል መሆን: የራሱና የሌላ ሰው መብት ሲጣስ መቃወም: እድገትና ለውጥ በሚያመጡ ፕሮጄክቶች መሳተፍ ወዘተ አገራዊ ፖለቲካዊ ስሜት የሚገለጥባቸው መንገዶች ናቸው::
ምናልባት ጥያቄ ቢኖረኝ ስሜት በሌለው ኢትዮጵያዊ ብዛት ላይ ነው:: እንደ ፋንታው አመለካከት ከሆነ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ በቂ ስሜት የለውም:: ይህ ቁጥር እንዴት ታወቀ? አገር ቤት ያለው ወይስ ውጭ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ነው ስሜት የሌለው? እነዚህን ጥያቄዎች ለመመለስ ጥናትና ምርምር ያስፈልጋል::
ዳሩ ግን ከምናየውና ከምንሰማው መገመት አይከብድም:: ከአምስት ሚሊዮን በላይ ህዝብ በሚኖርባት አዲስ አበባ የተቃውሞ ሰልፍ ተጠርቶ የሚወጣው እዚህ ግባ የሚባል አይደለም:: የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያዘጋጇቸው ስብሰባዎች የሚገኘው ህዝብ ከበቂና ከተጠበቀው በታች ነው:: ምክንያቱ ደግሞ መንግስትን ከመደገፍ ወይም የጭቆና አለመኖር ሊሆን እንደማይችል ለማንም ግልጽ ነው:: በውጭ አገራት የሚኖሩት ኢትዮጵያውያንም በዘመናዊ ማህበራዊ የመገናኛ ብዙኃን ስለአገራቸው የሚጽፉና የሚያነቡ ጥቂቱ ናቸው:: ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮችን በሚመለከት የውይይትና ክርክር መድረኮች ተዘጋጅተው የሚሳተፉት ጥቂቶች ናቸው:: በሰላማዊ ሰልፍ የሚሳተፉትም እንዲሁ:: በአንጻሩ ደግሞ የሙዚቃ ምሽት ወይም የስፖርት ዝግጅቶች እንዲሁም ሰርግና ልደት በሚደረግበት ጊዜ ያረፍዳል እንጅ የተጠራው ሁሉ ሽክ ብሎ ይገኛል:: ያልተጋበዘውም ባለመጋበዙ ይሰማዋል::
ለመሆኑ አገራዊ ፖለቲካዊ ስሜት የሚጎድለን ለምንድን ነው? ይህ በተለይ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሁሌ የሚያነሱት ጥያቄ ነው:: በዝግጅቶቻቸው በቂ ሰው አይገኝምና:: ይህ ጥያቄ ባንድም በሌላም መንገድ ቢነሳም አጥጋቢ መልስ አላገኘም:: አንዳንዶች የዚህ ሁሉ ችግር ህዝቡ ያለው ፍርሃት እንደሆነ ተናግረዋል:: ሌሎች ደግሞ ይህ ዝምታ የኢትዮጵያ ህዝብ የትዕግስቱ መለኪያ እንደሆነ ጽፈዋል:: ነገር ግን እነዚህ ምክንያቶች ችግሩን በፍጹም አይገልጹትም:: የሁሉም ሰው ምክንያቶች ሊሆኑም አይችሉም:: የተጠናከረ ውይይት ቢካሄድ ይህን ችግር መቅረፍ እንደሚቻል በማመን በዚህ ጽሁፍና በተከታታይ ጽሁፎች አገራዊ ጉዳዮችን በአንክሮ እንዳንከታተልና በሚገባ እንዳንሳተፍ የሚያደርጉ መንስኤዎችንና ምክንያቶችን በዝርዝር ለማየት እሞክራለሁ::
መንስኤዎችና ምክንያቶች
ለአገራዊ ስሜት አለመኖር መንስኤዎችን ከምክንያቶች ለመለየት የተደራጀ ጥናትና ምርምር ያስፈልጋል:: በዚህ ጽሁፍ ግን ሁለቱን አንድ ላይ አድርጌ አቀርባለሁ:: ይህን ማድረጌም የጽሁፌን ዓላማ ከመምታት አያግደኝም:: ይልቁንም አላስፈላጊ ክብደትን ያስወግድልኛል ብዬ አምናለሁ::
በቂ ስሜት ያለመኖር መንስኤዎቹና ምክንያቶቹ ከሰው ሰው ከጊዜ ጊዜ ሊለያዩ ይችላሉ:: ቢሆንም ግን ዋና ሊባሉ የሚችሉትን መገመቱ አይከብድም:: ከማኅበራዊ ህይወቴ ጋር በተያያዘ ከተመለከትኳቸውና ከታዘብኳቸው የስሜት አልባነት መንስኤዎች ወይም ምክንያቶች መካከል የሚከተሉት ዋናዎቹ ናቸው::
ዝንባሌና ፍላጎት
ሰዎች በተፈጥሮአቸውና በህይወት ተሞክሮአቸው የተነሳ ለተወሰኑ ጉዳዮች ብቻ ልዩ ፍላጎትና ዝንባሌ አላቸው:: በመሆኑም ለአገራዊ ጉዳዮች ምንም ደንታ የሌላቸው ሰዎች ይኖራሉ:: ሌላው ቀርቶ በግል ህይወታቸውም ሲበደሉና መብታቸው ሲጣስም አይገዳቸውም እጅጉን የሚያሳስባቸውና መስዋዕት የሚከፍሉለት ብቸኛው ጉዳይ ሥራቸውና የቤታቸው ነገር ነው:: የተሰማሩበትንም ሥራ የሚመለከቱት ለአገር በሚያደርገው አስተዋጽዖ ጭምር ሳይሆን የደመዎዛቸው መገኛና ማግኛ መሳሪያ በመሆኑ ብቻ ነው::
በዚህ ምድብ ውስጥ በርካታ በትምህርት ብዙም ያልገፉ ሰዎች: ቴክኒሽያኖች: መሃንዲሶች: ፕሮፌሰሮች: ዶክተሮች እና ሌላ ትልቅ ማዕረግና ደረጃ ላይ የደረሱ ሰዎችም ይገኛሉ:: እነዚህን ሰዎች አይደለም በማስታወቂያ በአማላጅም ቢሆን ወደ አገራዊ ውይይት መድረክ ማምጣት ከባድ ነው:: ያለው አማራጭ እነዚህ ሰዎች በተሰማሩባቸው የሥራ ዘርፎች ላቅ ያሉና ተጨማሪ አገልግሎቶችን እንዲያበረክቱ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ብቻ ነው:: በፖለቲካዊ ውይይት ወይም መድረክ እንዲሳተፉ ማስገደድ ከአለት ላይ ውኃ ለማፍለቅ እንደመሞከር ነው:: በአገራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች መሳተፍ የሁሉም ሰው ምርጫ ሊሆን አይችልም::
የአቅም ጉዳይ
ቀላል የማይባሉ ሰዎች ደግሞ በአገራዊ ጉዳዮች ለመሳተፍ እምቅ ኃይል ቢኖራቸውም ለራሳቸውና ለሌሎች ሰዎች ያላቸው የተሳሳተ ግምት አስተዋጽዖ እንዳያደርጉ ያደርጋቸዋል:: ራሳቸውን ዝቅ አርገው ስለሚመለከቱ ወጣ ብለው ለመታየት አይፈልጉም:: ውይይቶች በሚካሄዱባቸው ጊዜ ጥሩ ሃሳቦች ቢኖራቸውም ለመጠየቅ ያመነታሉ:: አልፎ አልፎም ሃሳብ ሊያቀርቡ ይችላሉ:: ከብዙ ሰዎች የሚያበረታታ ምላሽ ካላገኙ በሰው እንደተጠሉና እንደተናቁ በመገመት ራሳቸውን ያስጨንቃሉ:: ከሰዎች የሚያገኙት ግምት አበረታች ስለማይሆን ተሳትፎአቸውን ለመግታት ለራሳቸው ቃል ይገባሉ:: አገራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮችን በተመለከተ አስተዋጽዖ ለማድረግ ይህ ነው የሚባል አቅም እንደሌላቸው ራሳቸውን ያሳምናሉ:: በመሆኑም ቀስ በቀስ በታዳሚነት ከሚገኙባቸው መድረኮች ይርቃሉ::
ሌሎቹ ደግሞ ከላይ ከተጠቀሱት ሰዎች ተቃራኒ ናቸው:: በእውነትም ጥሩ ሃሳብና ተሞክሮ ቢኖራቸውም የሌላውን ለመቀበል ይቸገራሉ:: ሁሌ የራሳቸው ሃሳብ ብቻ እንዲያሸንፍ ይከራከራሉ:: ይህ ሳይሆን ቢቀር ስብሰባው ወይም ውይይቱ እርባና እንደሌለውና ችሎታ በሌላቸው ሰዎች እንደሚመራ ያወራሉ:: ያስወራሉ:: እንደምንም ብለው ለሚቀጥለው ጊዜ የመሪነቱን ቦታ ለመያዝ ይሯሯጣሉ:: ካልተሳካላቸውም ሙከራቸውን እንደ ሽንፈት ቆጥረው ከሱታፌ ይታቀባሉ:: ከተሳካላቸው መድረኩ ወይም ፓርቲው የግል ንብረታቸው እስኪመስላቸው ይቆጣጠሩታል:: ሥልጣን እንዲለቁ ወይም እንዲያካፍሉ ወይም የሌላውንም ሰው አስተዋጽዖ ቦታ እንዲሰጡ ሲጠየቁ ያኮርፋሉ:: ያደረጉት አስተዋጽዖ የተረሳባቸው ይመስላቸዋል:: የመገለል ስሜት ያጠቃቸውና እንቅስቃሴአቸውን ቀስ በቀስ ያቋርጡና በትዝታ መኖር ይጀምራሉ:: ከቻሉም ሲሳተፉባቸው የነበሩትን መድረኮች ወይም ድርጅቶች ይኮንናሉ:: ለማዳከምም ይጥራሉ:: አንዳንዶችም የራሳቸውን ተስፈንጣሪ ድርጅቶች ይፈጥራሉ:: የባሰባቸው ደግሞ የመንግስት ደጋፊና አባል በመሆን ብቸኝነታቸውን ለመቋቋምና ተፈላጊነታቸውን ለመጨመር ይጥራሉ::
//////////// ይቀጥላል ///////////////
ገንቢ አስተያየት ካላችሁ በteklu.abate@gmail.com ላኩልኝ!

ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ በስዊትዘርላንድ በርን





ቀን JUNE 26/2014

በሃገራችን ኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ ከዕለት ወደ ዕለት ወደባሰና ወደለየለት ፖለቲካዊ ምስቅልቅል እየሄደ መሆኑ ይታወቃል፣ ለዚህም ማሳያ የሆኑት ከሰሞኑ የተፈጸሙት ፍጹም ሰላማዊ በሆኑ ዜጎቻችን የሚደርሰው ግድያ፣ የጅምላ እስርና የመብት ጥሰት ሲሆን፣Ethiopians in Switzerland demonstration
በአምቦ፣ በሃሮማያ፣ በመደወላቡ/ወለጋ/ እና ናዝሬት ዩኒቨርሲቲዎች በገዢው መንግስት እየተፈጸሙ ያሉና መብታቸውን በሰላማዊ መንገድ በጠየቁ ኢትዮጵያውያን ኦሮሞ ተማሪዎች ላይ በደረሰው የግፍ ግድያና እስካሁን ድረስ ባልቆመው ከመማርያ ክፍላቸው እና ከማደሪያቸው እየተለቀሙ ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደው በሚሰወሩ ተማሪዎችና የሚፈጸምባቸውን ግፍ በመቃወም፣
በቅርቡም ይበጃል ያሉትን ሃገራዊ ራዕይና በጎ ሃሳብ በመጦመራቸው ምክንያት በማዕከላዊ የጭለማ እስር ቤት በግፍ የሚማቅቁ እና የሚሰቃዩ ጦማርያንና ጋዜጠኞችን እስር በመቃወም፣
ገዢው መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ በመግባት መረን ለቆ የሃገሪቱን ታላላቅ የሃይማኖት ተቋማት በማተራመስና የእምነት ቦታዎቹን በመድፈር እንዲሁም የሃይማኖት መሪዎችን ሳይሆን ፖለቲከኞችን ለመሾም፣ ይህንና መሰል እኩይ ተግባራት በማድረጉ ሂደት በተለይም መጅሊሳችን በመስጊዳችን ያሉ የእስልምና ሃይማኖት የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎችን በማሰር ፖለቲካዊ ህልሙን የእምነት ቦታዎቹን በማርከስ ለማሳካት የሚያደርገውን ጥረት በመቃወም፣
በጠቅላላው የሃገራችን ክፍሎች በጉጅሌው አገዛዝ ካድሬዎች ሆን ተብለው የሚፈጸሙ ዜጎችን እርስ በርስ የማጋጨትና ያለአግባብ ማፈናቀልን በመቃወም ወዘተ…. እነዚህና ሌሎችም ዘርፈ ብዙ የሆኑት መሰረታዊ የሰው ልጆች መብቶች በአምባገነኑ ህውአት ኢህአዴግ የግፍ አገዛዝ በሚጣስባት እንዲሁም ዜጎች የተለየ አመለካከት ስላላቸው ብቻ ህይወታቸውን በሚያጡባት ሃገር. . . ግድያውን፣ እስሩንና፣ ግርፋቱን ሸሽተው የሚወጡ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የስደተኝነት ምክንያታቸው በአግባቡ ባለመታየቱ እና በአብዛኛው ተቀባይነት ባለማግኘቱ የስዊትዘርላንድ መንግስት የወያኔው ዘረኛ እና አምባገነን አገዛዝ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እያካሄደ ያለውን አፈናና ግድያ በመመርመር የዘረኛውን አገዛዝ እኩይ ድርጊት እንዲያወግዝና ከኢትዮጵያ ህዝብ ጎን እንዲቆም በተጨማሪም በስዊዘርላንድ ተጠልለው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የስደት ጥያቄአቸው በድጋሚ ባግባቡ እንዲታይና አዎንታዊ ምላሽ እንዲያገኝ ጥያቄአችንን ለማቅረብ መሆኑን በአክብሮት እናስታውቃለን::
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብትና ዴሞክራሲ ግብረ ሃይል በስዊትዘርላንድ
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!
NB: የሰልፉን ሰዓት፣ ቦታና ዝርዝር የትራንስፖርት ሁኔታዎችን በቀጣይ የምንገልጽ መሆኑን እናስታውቃለን

የኢትዮጵያ መሰረታዊ የልማት ችግር የት ነው እንዴትስ ይፈታል?





ገለታው ዘለቀ
ስለ ልማታዊ መንግስት (developmental state) ስናወራ ልማታዊ የሚለው ቅጽል ስም ገላጭ በመሆኑ መጀመሪያ “ልማታዊ” ሲባል ምን ማለት ነው? ብለው ሰዎች እንዲጠይቁን ያደርጋል። ኣንዱ የዚህ ጥያቄ ምንጭ በኣሁኑ ዘመን ልማት ለሚለው ስያሜ ሰፊ ትርጉም ስለተሰጠው ሲሆን ኣንድ መንግስት ዛሬ ላይ ሆኖና ብድግ ብሎ “ልማታዊ መንግስት ነኝ” ሲል ማን ልማታዊ ያልሆነ ኣለ ብለው ሰዎች እንዲነሱ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሹ የሚያደርግ ጥያቄ ለማኝ ጉዳይ ነገር ያንጠለጠለ በመሆኑ ነው።
ሁሉ እንደሚያውቀው በኣሁኑ ጊዜ ልማት ለሚለው ጽንሰ ሃሳብ የተሰጠው ትርጉም ሰፊ ሲሆን የሰው ልጆችን ሁለንተናዊ ኣዎንታዊ እድገት ይጠቀልላል። የኢኮኖሚ እድገት፣ ትምህርት፣ ጤና፣ ዴሞክራሲና መልካም ኣስተዳደር፣ ወዘተ. ይሸፍናል። በመሆኑም ኣንድ መንግስት በዚህ በኣሁኑ ጊዜ ልማታዊ ነኝ ሲል ማንም መንግስት ለነዚህ ጉዳዮች ቆሚያለሁ ይላልና ምን የተለየ ነገር መጥቶ ነው ልማታዊ የሚያሰኛችሁ በሚል ያስጠይቃል ወይም ለፖለቲካ ትርፍ ከሆነ ደግሞ ህዝብ መቀለጃ ያደርገዋል ማለት ነው። Ethiopian opinions forum
ባለፉት ዘመናት በተለምዶ ልማታዊ መንግስታት ይባሉ ለነበሩት የተሸለመው ይህ “ልማታዊ” የተሰኘ ቅጽል ስም የሚገልጸው እንዲህ እንዳሁኑ ልማትን በሰፊው ኣይቶ ሳይሆን የኢኮኖሚ እድገትን የሚመለከት ጠባብ ጉዳይ ነው።የልማታዊ መንግስትነት ኣንዱ ልዩ መገለጫውም ይሄው ነበር። በኢኮኖሚ እድገት ላይ ከፍተኛ ዝንባሌ ያለው መንግስት ማለት ነው።የኢኮኖሚ እድገት ከመጣ ውስብስብ የሆነው የሰው ልጆች ችግርም ኣብሮ በዝግታ ይፈታል ስለዚህ መጀመሪያ ኢኮኖሚው ላይ እናተኩር የሚል ነገር ከደጋፊዎች ይደመጣል።
በሌሎች ተቃዋሚዎች ዘንድ ደግሞ ልማታዊ መንግስት የሚለው ጉዳይ ስሙ ራሱ ኣደናጋሪ ነው። ልማት ከተባለ ዴሞክራሲንም ማቀፍ ኣለበት ኣብሮ ነው ሁሉም ማደግ ያለበት ይላሉ። ከሁሉ በላይ ደግሞ ይሄ ጉዳይ ቀን የጣለው (outdated) ነው። የዛሬው ትውልድ ስለ መብቱ ይጨነቃል ከኣምሳ ኣመት በፊት እንደነበረው ኣባቱ ኣያስብም የሚል ነገርም ይነሳል።እንደነዚህ ዓይነት ተቃውሞዎች ከማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል ኣካባቢ የሚቀርቡ ናቸው።
ዋናው ክርክር ግን ለምን የኢኮኖሚ እድገት ላይ ታተኩራለህ ኣይደለም። በርግጥ ኣንድ ጎበዝ መንግስት ኣገሩን ከድህነት ለማላቀቅ የኢኮኖሚ ጥርመሳ(breakthrough) ውስጥ የሚያስገባውን ስራ መስራት ኣለበት። ነገር ግን ልማታዊ መንግስትነትን የሚተቹ ሰዎች ለኢኮኖሚ እድገት ጠንክሮ መስራትን ሳይሆን ልማታዊ መንግስት ነኝ የሚለው መንግስት ለኢኮኖሚው ጥርመሳ ኣንድ ዋና መንገድ ኣድርጎ የሚያየው የመንግስትን በገበያ መሃል ጣልቃ መግባትና ኢኮኖሚን በከፍተኛ ሁኔታ መቆጣጠር ከሆነ ነው። ተቃዋሚዎች ይህን ኣስተሳሰብና ዝንባሌ ከምን እንደመነጨ የፍልስፍናው መሰረት ምን እንደሆነ፣ ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል ማወቅ በጥብቅ ይፈልጋሉ። በመንግስት የገበያ ጣልቃ ገብነት ወይም በመንግስት ነጋዴነትና በኢኮኖሚ እድገት መካከል ምን ኣይነት ሳይንሳዊ ግንኙነት ኣለ ብለው ሊጠይቁ ይችላሉ። የመንግስት ጣልቃ ገብነት የሚገለጽባቸው ቅርጾች የተለያዩ ሲሆኑ በኢትዮጵያ ሁኔታ መንግስት በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ጣልቃ ገብነት የምንገልጸው ራሱ መንግስትና ፓርቲዎች በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ የያዙዋቸውን የንግድና የኣገልግሎት ተቋማት በማየት ነው። ለዛሬው ውይይታችን የመንግስት ጣልቃ ገብነት በገበያው መሃል እያልን ስናወራ ጣልቃ ገብነቱን ከዚህ ክብ ውስጥ እያየን ነው።
በተለምዶ እንደሚታወቀው የኢኮኖሚ እድገት የሚመጣው ወይም ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ከጂዲፒ ማደግ፣ ከምርት መጨመር ጋር የተያያዘ ሲሆን በርግጥ ምርት እንዲጨምር የሚያደርጉ እምቅ ጉዳዮች (potential factors) ደሞ ኣሉ። እነዚህ ጉዳዮች መሬት (land) ፣ የሰው ሃይል፣ ካፒታል እና ኢንተርፕሩነርሺፕ ናቸው። በርግጥ እነዚህ ጉዳዮች ሁሉ ኖረው የፖለቲካው ከባቢ ምቹ ካልሆነ ምርት ላይጨምር ይችላል። ይሄ የታወቀ ነው። ነገር ግን የመንግስት ጣልቃ መግባትና ያለ መግባት ከኢኮኖሚ እድገት ጋር የሚያያይዛቸው ቀጥተኛ ሳይንሳዊ ግንኙነት የለም። ብዙ ኣገሮች መንግስት በገበያ ጣልቃ ሳይገባ ወይም ጣልቃ ገብነቱን ሲያቆም ኣድገዋል ጥቂት ሃገሮች ደግሞ መንግስት ጣልቃ ገብቶ ኣድገዋል። ኣንዳንድ ኣገሮች መንግስት ጣልቃ ባይገባም ኣላደጉም፣ ብዙ ኣገሮች መንግስት ጣልቃ ገብቶ ኣላደጉም። ይህ የሚያሳየው በመንግስት ጣልቃ ገብነትና በኢኮኖሚ እድገት መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት ኣለመኖሩን ነው። ኣንዳንድ ወገኖች ቻይናንና ኣሜሪካንን ይጠቅሳሉ።እነ ኣሜሪካና እንግሊዝ ኢኮኖሚያቸውን ደብል ለማድረግ ሃምሳና ስልሳ ኣመት ሲፈጅባቸው ቻይና ደግሞ በኣንድ ኣስርት ውስጥ ደብል ማድረግ የቻለችው መንግስት በማክሮና ማይክሮ ኢኮኖሚው ውስጥ ጣልቃ በመግባቱ ኢኮኖሚውን በመቆጣጥሩ ነው ሊሉ ይዳዳቸዋል። ለምን የኢኮኖሚውን ፈጣን እድገት ከመንግስት ጣልቃ ገብነት ጋር ፈጥነው እንደሚያያይዙት ኣይታወቅም። ለቻይና ጂዲፒ እድገት ብዙ ፋክተርስ ኣስተዋጾ ኣድርገዋል። ኣንዱና ትልቁ ኢንቨስትመንት የመሳቡዋ ጉዳይ ነው። ቻይና ውስጥ በግል ከተያዙ ከፍተኛ የንግድ ድርጅቶች መካከል ሰማኒያ በመቶ የሚሆኑት በውጭ ኢንቨስትመንት የተያዘ እንደሆነ ኣንድ ጥናት ያሳያል። ይህ ግዙፍ ኣሃዝ የሚያሳየው ኢንቨስትመንቱ ምን ያህል እድገቱን እንዳፋጠነው ነው። እነ ኣሜሪካ፣ እንግሊዝና ሌሎች የዘመናዊነት ቀዳሚ ኣገሮች እድገት መነሻው ከባድ ነበር።እነዚህ ኣገሮች ኢኮኖሚያቸውን በጥንድ ቁጥር ለማሳደግ ስልሳና ኣምሳ ኣመት ከዚያም በላይ ሲፈጅባቸው በኣሁኑ ሰዓት ለማደግ ምቹ ሁኔታ ያገኙ ኣገሮች ግን ያን ያህል ጊዜ የማይፈጅባቸው ኣንዱ ምክንያት የውጭ ንግዱ ያደገበት ጊዜ መሆኑ፣ ኣጠቃላይ የግሎባል ዲማንድ የጨመረበት ጊዜ ላይ መሆኑ፣ሳይንስና ቴክኖሎጂ ያደገበት ጊዜ መሆኑ ሲሆን ኣሁን በርትተው የተነሱ ኣገሮች በጥንድ ቁጥር የማደግ እድላቸው ከሃምሳ ኣመት በፊት ከነበረው እድል ይሰፋል።ለዚህም ነው የምስርቅ እስያ ኣገሮች በየኣስር ኣመቱ ደብል ማደግ የቻሉት።
ሌላው እንደ ኮርያ ያሉ እርዳታን በትክክል ለእድገት የሚጠቀሙ ሃገሮች ደግሞ መነሻ ስለሚያገኙ ለመስፈንጠር እና ኢኮኖሚያቸውን በጥንድ ለማሳደግ መሰረት ይኖራቸዋል።ሰፊ የፋይናንስ እርዳታዎችን እያገኙ ማደግ ከባዶ ተነስቶ ከሚታደግ ጋር ሊወዳደር ኣይችልም። ዛሬ ብዙ የኣፍሪቃ ሃገራት የተለያየ ብድርና እርዳታን እያገኙ ኣንዳንዶቹ ጋናን መጥቀስ ይቻላል ሲያድጉ ኣንዳንዶቹ ኢትዮጵያን ጨምሮ የሚሰጠውን እርዳታ ያክል በየኣመቱ ያባክናሉ። ከዚህም የተነሳ ከድህነት ሳይወጡ ይቆያሉ።
ኮርያና ኣንዳንድ የምስራቅ እስያ ኣገሮች በመጀመሪያው የእድገት ወራታቸው ከፍተኛ የሆነ የውጭ ኢንቨስትመንት የመሳብ ዝንባሌ ያሳዩ ሲሆን በዚህም ኢኮኖሚያቸው በፈጣን ሁኔታ ሊያድግ ችሏል።ስለ ኮርያ ከተነሳ ኣይቀር ጥቂት ማለቱ ተገቢ ነው። ኮርያ የኢኮኖሚ ጥርመሳ የጀመረችው በ1970 ዎቹ ነበር። በዚህ ጊዜ በወቅቱ ስልጣን ላይ የነበሩት ፕሬዚደንት ፓርክ ዲክቴተር የሚባሉ ኣይነት ነበሩ። የኮርያ ኢኮኖሚ ማንሰራራት የጀመረው በእኚሁ መሪ የስልጣን ዘመን ቢሆንም ለኮርያ መነሳት(economic takeoff)ግን ብዙ ፋክተርስ ኣሉ። ከነዚህም ውስጥ ምን ኣልባትም ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው የቀዝቃዛው ጦርነት ጉዳይ ነው። እንደሚታወቀው ደቡብና ሰሜን ኮርያ በወቅቱ ዓለምን ለሁለት በከፈለው የፖለቲካ ኣስተሳሰብ ከተለያዩ በሁዋላ ደቡብ ኮርያ የካፒታሊስቱን ስርዓት ኣጥብቃ የያዘች ሲሆን ይህ ኣቋሟ ከተባበረችው ኣሜሪካና ከምእራብ ሃያላን ኣገራት ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዲኖራት ኣደረገ። በተለይ የተባበረችው ኣሜሪካ በሰሜንና በደቡብ ኮርያ ጦርነት ወቅት 34 ሺህ ወታደሮቿን የሰዋችባት ኣገር ናት ኮርያ። በጦርነቱ ወቅት ከሞተው ሌላ የቆሰለውን ቤቱ ይቁጠረው። ለጦርነቱ ያወጣችው ወጪ በብዙ ቢሊየን ዶላር የሚቆጠር ነው።ይህ መስዋዕትነቱዋ ኣሜሪካ የኮርያን እድገት እንድትፈልግ ኣድርጓታል። ኣሜሪካ ብቻ ሳትሆን በሁለቱ ኮርያውያን ጦርነት ጊዜ በወቅቱ ደቡብ ኮርያ ከተባበሩት ህዝቦች ድርጅት(UN)እርዳታ በመጠየቋ ከራሺያና ከቻይና ውጭ ዓለም በሙሉ ከደቡብ ኮርያ ጋር የቆመበት ታሪካዊ ወቅት ነበር። UN በኣራቱም ማእዘናት ኮርያን ለመታደግ ጥሪ ሲያስተላልፍ በሊግ ኦፍ ኔሽንስ ምስረታ ወቅት ጉልህ ሚና የነበራቸው ኣጼ ሃይለስላሴም ለጥሪው ፈጣን ምላሽ በመስጠት በሺህ የሚቆጠር ጦር በመላክ ኢትዮጵያም ኮርያን ኣግዛለች።
ከፍ ሲል እንዳልነው ጦርነቱ ከቆመ በሁዋላ የተባበረችው ኣሜሪካም ሆነች የዓለም ህዝቦች ይህቺ ኣገር ተቋቁማ፣ በኢኮኖሚ ጠንክራ ማየቱ ኣስፈላጊ ሆኖ የታያቸው ይመስላል። ከዚህ በተጨማሪም በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት የነበረው የሁሉቱ ጎራዎች ፉክቻ ከኮሚኒስቱ ኣካባቢ በኣብዛኛው የቃላትና የስድብ ውርጅብኝ ሲሰነዘር ከምእራቡ ዓለም ኣካባቢ ደግሞ ከቃላቱ ጦርነት ይልቅ በኢኮኖሚ እድገትና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ምጥቀት በልጦ ለመገኘት እልህ ውስጥ የመግባት ሁኔታ ይታይ ነበር። በመሆኑም የኮሚኒስት ደጋፊ የነበረችውን ሰሜን ኮርያን ለማስቀናትም ጭምር የተባበረችው ኣሜሪካና ምእራባውያን ለደቡብ ኮርያ በመለገሳቸው ለኮርያ የኢኮኖሚ ጥርመሳዋ ከፍተኛ የሆነ ጥሩ ከባቢ ፈጥሮላታል።ኮርያ በዚያን ጊዜ እርዳታና ድጋፍ በከፍተኛ ሁኔታ ያገኘች ሲሆን በርግጥ የኮርያ ትልቅ ምሳሌነቱዋ የሚሰጣትን እርዳታ መጠቀም መቻሏ ነው። ብዙ ኣገሮች እርዳታ እያገኙም ማደግ ያልቻሉ ሲሆን ደቡብ ኮርያ ለዓለም ያስተማረችው ትልቁ ጉዳይ እርዳታን ለእድገት መጠቀም መቻሏ ነው። በዚያው በ1970ዎቹ የኮርያ ወርቃማ ዘመናት ጊዜ ፕሬዚደንት ፓርክ ያቋቋሙት ሴማእል ኡንዶንግ የተባለው ድርጅት በተለይ ለገጠሩ ክፍል እድገት ከፍተኛ ኣስተዋጾ ኣድርጓል። ይሁን እንጂ ሴማእል ኡንዶንግ (ኣዲስ ንቅናቄ)የተሰኘው የልማት ድርጅት በገጠሩ ወይም በእርሻ ላይ ያተኮረ ስራ የቱንም ያህል ቢሰራ ሃገሪቱን በከፍተኛ ሁኔታ ሊለውጣት ኣይችልም ነበር። ምክንያቱም ኮርያ በተፈጥሮ ሃብት የበለጸገች ኣገር ኣይደለችም። እስካሁንም በከፍተኛ ሁኔታ የጥራጥሬ እህሎችንና ጥሬ ሃብቶችን ከውጭ ነው የምታስገባው። ካላት ዝቅተኛ የተፈጥሮ ሃብት የተነሳ ለማደግ ኣቅጣጫዋን ወደ ኢንዱስትሪው እንድታዞር ኣድርጓታል። በርግጥ ሴማእል ኡንዶንግ በገጠር ያለውን ማህበረሰብ በማህበራዊ ኣገልግሎት ኣቅርቦት፣ በውስጥ ለውስጥ መንገድ ስራ በኣጠቃላይ የእርሻውን ስራ በከፍተኛ ሁኔታ የለወጠው ሲሆን ከሁሉ በላይ የፈጠረው የህብረተሰብ መነሳሳት(community mobilization)ወዲያው ወደ ኢንዱስትሪው ኣካባቢም መንፈሱ በመዛመቱ ከፍተኛ የሆነ ለእድገት የመነሳሳት ሁኔታን ፈጥሮ ነበር። በዚያው በ1970ዎቹ ጊዚያት የመሰረተቻቸው ኢንዱስትሪዎች መንቀሳቀስ ሲጀምሩ እድገቷን የናፈቁ የዓለም ህዝቦች የመጀመሪያ ምርቶቿን በመግዛት በማበረታታት ከፍተኛ ሚና የተጫወቱ ሲሆን ኣሜሪካ ከፍተኛ ድጋፍ ኣድርጋለች። ከዚህ በተጨማሪም 1970ዎቹ በዓለም ታሪክ ውስጥ የኢኮኖሚ እድገቶች የተመዘገቡበት ኣስርታት በመሆኑ ኣጠቃላይ ከባቢው ለእድገት ኣስተዋጾ ነበረው። ከሁሉ በላይ ደግሞ የህዝቡ ጠንካራ ሰራተኝነት ለኮርያ የኢኮኖሚ ጥርመሳ ከፍተኛ ኣስተዋጾ ኣድርጓል። በዚያ ጊዜ ኮርያውያን በተመቸ የኣስተዳደር ስርዓት ውስጥ ስለ ነበሩ ዓይደለም ያደጉት። ወይም ዲክተተርሺፕ ለኮርያ እድገት ኣስተዋጾ ኣላደረገም። የሆነው ምንድነው ኮርያውያን በኣንድ በኩል ኢኮኖሚውን እያሳደጉ ጠንክረው እየሰሩ በሌላ በኩል ደግሞ ዲክቴተርሺፕን ይቃወሙ ነበር። የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኣጠቃላይ ህዝቡ ለዓመታት ታግለው በመጨረሻም ኣምባገነናዊ ስርዓትን ለመገርሰስ ችለዋል። ኣምባገነኑን መንግስት ጥለው ወደ ዴሞክራሲ ጎዳና ከገቡ በሁዋላ የሚያስገርም የኢኮኖሚ እድገቶችን ማስመዝገብ ጀምረዋል። በኣጠቃላይ የኮርያን እድገት መነሻዎች ስናይ በብዙ መልካም ከባቢዎች ውስጥ የታጀበ መሆኑን እንረዳለን።ለዴቨሎፕመንታል ስቴት ምሳሌ ከሆኑት የምስራቅ እስያ ኣገሮች መካከል የኮርያ የእድገት ሁኔታ እዲህ የሚታይ ሲሆን ሌሎቹንም ብናይ በርግጥ ዲክተተር መሆን ኣላሳደጋቸውም ወይም መንግስታቱ በገበያው መሃል ጣልቃ በመግባታቸው ኣይደለም እድገት ያመጡት። ለኢኮኖሚ እድገት ቀጥተኛ ኣስተዋጾ ያላቸው ጉዳዮች በመገጣጠማቸውና ጠንክረው በመስራታቸው ከሁሉ በላይ ደግሞ ኢንቨስመንት በመሳባቸው የተመቻቸ የኢኮኖሚ ፖሊሲ በመንደፋቸው ነው።
ለኣንድ ኣገር የኢኮኖሚ እድገት ጥርመሳ መንግስት ኢኮኖሚውን መቆጣጠር ኣለበት የሚሉ ወገኖች ከሚያነሱት ኣሳብ መካከል ኣንዱ መነሻ ላይ ግለሰቦች ታላላቅ የሆኑ ኢንቨስትመንቶችን ለማንቀሳቀስ ኣይችሉም፣ ዜጎች ለብዝበዛ ሊጋለጡ ይችላሉ፣ ከግለሰቦች ኣካባቢ የኣቅም(capacity) ችግር ስለሚኖር መንግስት የተደራጀ ነውና ኢኮኖሚውን ቢቆጣጠር ኣመርቂ ውጤት ያመጣል የሚሉ ዋና ዋና ናቸው። በሌላ በኩል ደግሞ የሊብራል ኣስተሳሰብ ያላቸው ወገኖች ከፍ ሲል እንዳልነው በመንግስት ጣልቃ ገብነትና በኢኮኖሚ እድገት መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት የለም እንዴውም የመንግስት ጣልቃ ገብነት ለኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ ኣስተዋጾ ያለውን ኣንዱን ኢለመንት ማለትም ኢንተርፕሩነርሺፕን ያጠፋና እድገቱን ያዘገየዋል ከሁሉ በላይ የእኩልነት የብዝበዛ ጉዳዮችን መንግስት የሚያስተካክልበትን ሜካኒዝም ሊፈጥር ይችላል። በገበያ መሃል መግባቱ መፍትሄ ኣያመጣም የሚሉ ናቸው። ከሁሉ በላይ ያለው ስጋት ደግሞ መንግስት በኢኮኖሚ እየበረታ ሲሄድ የራሱን መደብ ፈጥሮ የተጠራቀመውን ገንዘብ መጨቆኛ ሊያደርገው ይችላል። ግለሰቦችን እያደኸዩ መንግስትን ማደለብ ኣደጋ ኣለው። ኣሳቡ ራሱ ኣንድ ፓርቲ በስልጣን ላይ ለረጅም ጊዜ እንዲቆይ የሚያበረታታ ኣዝማሚያ ስላለው ሃብት መጮቆኛ ሊሆን ይችላል ብለው ይሰጋሉ። መንግስት በገበያ መሃል ጣልቃ በመግባቱ እድገት የሚመጣ ቢሆን የደርግ መንግስት ከማምረቱ ጀምሮ EDDC (Ethiopian Domestic Distribution Corporation) መስርቶ እስከ ማከፋፈሉ ተቆጣጥሮት ኣልነበረም ወይ? እድገት መቼ መጣ? ጎረቤት ኣገሮች ሁሉ ኢትዮጵያን ጥለዋት ኣልሄዱም ወይ? የሚል ጥያቄ ያስነሳል። ይልቁን መንግስት የግል ኢንቨስትመንትን ማበረታታት፣ የውጭ ንግድን መሳብ የሚገባ ሲሆን፣ ሊከሰቱ ይችላሉ ተብለው የሚፈሩትን ችግሮች ለመግታት መንግስት ለኢንቨስተሮች ከፍተኛ የምክርና የሰለጠነ የሰው ሃይል ድጋፍ ሊያደርግ ነበር የሚገባው።ጣልቃ ገብነቱ በዚህ መንገድ የሚገለጽ ቢሆን ይመረጣል ለማለት ነው። ኢንቨስተሮች ለትርፍ ብቻ የሚነሱ ስግብግብ ኣድርጎ ማሳብ ትክክል ኣይደለም። የኣገልግሎት ሰጪነት ስሜት ያላቸው፣ ከትርፍ ይልቅ ኣገልግሎት በመስጠት ልባቸው የሚረካ ዜጎች ኣሉ። በቅርቡ እንኳን ኣቶ ብርሃነ መዋ ሲናገሩ ልብ የሚነካ ነገር ነው። እኚህ ሰው ሚሊየነር ሆነው ቤት እንኳን ኣልሰሩም። ይደክሙ ይሰሩ የነበሩት ውስጣቸው ለተቀመጠው የህዝብ ኣገልጋይነት ጸጋ ነበር። እንዲህ ኣይነት ዜጎች ስላሉ መንግስት ራሱን የተለየ ኣድርጎ ሃላፊነት የሚሰማው እሱ ብቻ እንደሆነ ኣድርጎ ማሰቡ ከመነሻው የተሳሳተ ነው።ሌላው ጉዳይ በተለምዶ ልማታዊ መንግስት የሚለው ጉዳይ በርግጥ ቀን የጣለው ነው። ከለውጥ ጋርና ከሰው ልጆች እድገት ጋር ኣብሮ መሄድ ኣይችልም። ዛሬ በግሎባላይዜሻን ዘመን፣ የሰው ልጆች ስለ ሰብዓዊ መብትና ስለ ዴሞክራሲ በነቁበት ዘመን የዛሬ ኣምሳ ኣመት የነበረውን ኣሰራር ተግባራዊ ለማድረግ መሞከር ኣስቸጋሪ ነው። መንግስት ኣንዱ ትልቁ ጥራቱ ለውጥን የተረዳ ሲሆን ነው። የቴክኖሎጂ እድገትና የሰው ልጆች የማህበራዊ ሳይንስና የተፈጥሮ ሳይንስ እውቀት እየጨመረ መሄድ ኣለምን ወዴት እየወሰዳት እንዳሆነ መገመት ተገቢ ነው። ቴክኖሎጂው እና ንግድ እንዴት ኢንተር ዲፐንደንሲን እየፈጠረ እንደሚመጣ ማየትና መተንተን ብሎም ግንዛቤ መያዝ ተገቢ ነው። የዓለም ህዝቦች ግንኙነት እየጠበቀ እርስ በርስ የመተዋወቁና የመቀራረቡ ጉዳይ እየገፋ ነው የሚሄደው። የብዙ ያላደጉ ኣገሮችን ውስብስብ ችግር መፍቻ ከሆኑት ቁልፎች መካከል ኣንዱ ኣለማቀፋዊ ትብብር መሆኑን መረዳትና ክፍትነት(oppennes) በጣም ኣስፈላጊ ነው። ራሺያን ከገባችበት ኣዘቅት የታደጋት የሚካኤል ጎርቫቾቭ የውጭ ፖሊሲ መሻሻልና ለሌላው ዓለም ክፍትነትን ማሳየት በመቻሉ ነው።
የሊብራል ፖለቲካል ኢኮኖሚ ዋና መነሻ ዜጎች ገበያውን ይምሩት፣ ኢንተርፕሩነርሺፕን እናበረታታ የሚል ሲሆን ይህ ኣሳብ የሚፈልቀው ከጽኑ የዴሞክራሲ ኣስተሳሰብም ነው። ዜጎች የሚመሩት ገበያ እርስ በርሱ የሚያጫርስ ኣድርጎ ማሰቡ በዜጎች የሃላፊነት ስሜት ላይ መረማመድ ነው።ወይም ከባለፈው የኮሚኒዝም ትምህርት የመጣ፣ የቀዝቃዛው ጦርነት ፕሮፓጋንዳ የወለደው ማስፈራሪያ ሊሆን ስለሚችል ቆም ብሎ ማሰብ ተገቢ ነው። ወደድንም ጠላንም ኣለም ነጻነትን (liberty) በሁሉም የህይወት ኣቅጣጫዋ እያስከበረች ነው። በዚህ ጊዜ ከውጪያዊና ውስጣዊ ለውጥ ጋር ተጋጭቶ ለመኖር መሞከር እድገትን ይጎዳል።
የዴቨሎፕመንታል ስቴትስ ችግራቸው በገበያው ጣልቃ መግባታቸው ብቻ ሳይሆን ለኢኮኖሚ እድገት ቅድሚያ ለመስጠት ሌሎች ጉዳዮችንም መጎተታቸው ነው። ከነዚህ ጉዳዮች መካከል የፕሬሱን ጉዳይ እንይ። ፕሬሱን ልማታዊ ሁን በማለት ትኩረትን ወደ ኣንድ ኣቅጣጫ በመሳብ በመንግስት ላይ ፖለቲካዊና ሰብዓዊ ሂሶችን ለመገደብ ይሞክራሉ። ይህ ዝንባሌ በርግጥ ለኢኮኖሚ እድገት ይጠቅማል ከሚል ሳይሆን በስልጣን ላይ ለመቆየት ይጠቅመኛል ከሚል ስሜት ነው። ፕሬሱን ማቀዝቀዝ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶችንም ይዘጋል። በተለይ በሰባዊ መብትና በመልካም ኣስተዳደር ኣካባቢ የሚሰሩትን እያባረረ ለኢኮኖሚ እድገት ቅድሚያ ሰጥቻለሁ “ልማታዊ ነኝ” በሚል ሽፋን የዴሞክራሲን እድገት ያቀጭጫል።
ከሆነስ ሆነና ኢትዮጵያ የልማታዊ መንግስት ኣገር ናት ወይ?
ኣጠቃላይ የሆነን በልማታዊ መንግስት ላይ ያለውን ያልጠራ ጉዳይ ሁሉ ትተነው እንደሚባለው የኢኮኖሚ እድገት ለማምጣት የመንግስት ጣልቃ ገብነት ይኑር እንኳን ቢባል ኢትዮጵያ ከባቢው ኣላት ወይ? ብለን እንጠይቃለን። ይህንን ጉዳይ ስንመረምር በመጀመሪያ ደረጃ ኢትዮጵያ ጠንካራ ብሄራዊ ስሜትን እየገነባች ያለች ኣገር ኣለመሆኗ ብቻ ሳይሆን ያላት የፖለቲካ ስሪት የጋራ ሃብትን በመንግስት ካዝና ለማፍራት እምነት የሚጣልበት ስርዓት ኣልገነባችም። በሌላ በኩል በኢንዱስትሪው ንግድ ውስጥ የጦፈ ነጋዴ የሆነው መንግስት ሳይሆን ፓርቲዎች ሆነው ነው የሚታየው። ለዚህ ኤፈርትን መጥቀሱ ይበቃል። ኤፈርት በህወሓት የተመሰረተ ኣሁንም በህወሃት ማእከላዊ ቢሮ ኣባላት የሚመራ ንብረትነቱ የቡድን የሆነ ድርጅት ነው። ይህ ድርጅት ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ድርጅቶች ሁሉ የሚበልጥ ሲሆን ወደ መቶ የሚጠጉ ድርጅቶችን የሚያንቀሳቅስ የንግድ ተቋም ነው። ኢትዮጵያዊያን ይህ ድርጅት እየደለበልን ነው ኣንድ ቀን ችግራችንን ይፈታል ብለው ተስፋ ኣያደርጉም። ምክንያቱን ራሱ የፖለቲካው ተፈጥሮ ለዚህ ከባቢ እምነት (trust) የሚፈጥር ባለመሆኑ ነው።በኣጠቃላይ ኢትዮጵያ ባላት የፖለቲካ ኣሰላለፍ ልማታዊ መንግስት ለመሆን ኣትችልም። ዘውጌ የፖለቲካ ኣስተሳሰብን ይዞ ዴቨሎፕመንታል ስቴት መገንባት ኣይቻልም ለማለት ነው። ይህን ያመጣሁት እንዴው ሌላውን ሁሉ ትተነው ዴቨሎፕመንታል ስቴት የሚባለው ከለውጥ ጋር የማይሄድ መሆኑን ሁሉ ትተነው በመንግስት ጣልቃ ገብነት የኢኮኖሚ ጥርመሳ እናመጣለን ለማለት የሚያስችል የፖለቲካ ቅርጽ እንኳን ኢትዮጵያ የላትም ለማለት ነው።
ከዚህ በፊት በ 2009 “Unbalanced growth strategy a potential for conflict in Ethiopia” በሚል ኣርቲክል ላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚታየው የሙስና መስፋፋት፣ የእምነት(trust) መውረድ የተቋማት ነጻ ኣለመሆን ከፍተኛ የሆነ ተስፋ ማጣትን (uncertainity about the future) ስላመጣ ኢትዮጵያ ዴቨሎፕመንታል ስቴት ለሚባለው ጉዳይ የማትመች ኣድርጓታል። ይልቁን መንግስት ልማታዊ መንግስት ነኝ የሚልበት ትልቁ ምክንያት ዴሞክራሲን ለማስረሳትና በኢኮኖሚ እድገት ለመደለል ብሎም በስልጣን ለመሰንበት ነው። ይህ ኣዝማሚያ ግን የሚያዋጣ ባለመሆኑ ዛሬ የልማታዊ መንግስትነት ስያሜ ጉዳይ የኢትዮጵያ ህዝብ መቀለጃ ኣድርጎታል።
የኢትዮጵያ መንግስት ሊገነዘብ የሚገባው ጉዳይ ለልማታዊ መንግስትነት ኣብነት ኣድርጎ የሚጠቅሳቸው ኣገሮች ሁሉ ለእድገታቸው የተለያዩ ፋክተርስ ያለ ሲሆን ኣምባገነን በነበሩበት ሰዓት እድገት የጀመሩትን ከዓለም ላይ ስማቸውን እየነቀሱ እያወጡ ኣምባገነን መሆን፣ ነጻነትን ነፍጎ በገበያ ጣልቃ ገብነት እናድጋለን ማለት ስህተት መሆኑን ነው። ሌላው ኣንዱ የመንግስትን ጣልቃ ገብነት የሚደግፉ ሰዎች የሚሉት ጉዳይ ደግሞ ሃብትን ለመቆጣጠር ይረዳል ይላሉ ነግር ግን ኣፍሪካ በየዓመቱ ሃምሳ ቢሊዮን ዶላር የሚሆን ገንዘብ ታጣላች ሲሉ የቀድሞው የደቡብ ኣፍሪካ ፕሬዚዳንት ታቦን ቤኪ በቅርብ ጊዜ ተናግረዋል። ሃብት በኣንድ ሃገር በሚገባ ሊጠበቅ የሚችለው በግል ነው። ዜጎች ሁሉ ሃብታቸውን ነቅተው ይጠብቃሉ። በተግባር እንደሚታየው በከፍተኛ ሁኔታ ዝርፊያ ያለው በግሉ መስክ ሳይሆን በመንግስት መስሪያ ቤቶች ኣካባቢ ነው።
የኢትዮጵያ መሰረታዊ የኢኮኖሚ ችግር የት ነው እንዴትስ ይፈታል?
የሚያሳዝነው ችግሮቻችን ከባድ ኣልነበሩም። የከበደን የኢትዮጵያ መንግስታት ኣልሰማ ማለታቸው፣ ቅድሚያቸው ለራሳቸው የስልጣን ጊዜ በመሆኑ ነው። ኢትዮጵያ በኣሁኑ ሰዓት ትልቅ ችግር ሆኖባት ያለውና በኣስቸኳይ ሊፈታ የሚገባው የምግብ ዋስትናና የድህነት ጥግ (extreme poverty) ጉዳይ ነው። ይህ የሚፈታው ደግሞ እነደነ ኤፈርት ኣይነቱ ድርጅት ከተማ ከተማውን ስላውደለደሉ ኣይደለም። ብዙ ኢኮኖሚስቶች እንደሚያምኑት ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናዋን ለማረጋገጥና የኢኮኖሚ ጥርመሳ ውስጥ ለመግባት ግብርናውን የመለወጥ ስራ መሰራት ኣለባት።ኣንዳንድ ወገኖች ግብርናው ላይ ያተኮረ ስራ መስራት ያስፈልጋል ሲባል ከተማው ችላ የተባለ ይመስላቸው ይሆናል። ግን ኣይደለም። ኣጠቃላይ የሃገሪቱን ምርት ከፍ ለማድረግ የትኛው መንገድ ይመረጣል ለማለት እንጂ ከእድገቱ ተጠቃሚው ሁሉም ዜጋ ነው። ዓላማው የሃገሪቱን ጂዲፒ ከፍ በማድረግ ያንድን የህብረተሰብ ክፍል ከመጥቀም ጋር የተያያዘ ኣይደለም።
ኢትዮጵያ እንደ ሃገር የሚገልጻትን ኑሮዋን እንመልከት። ለምሳሌ ኣንድ ገበሬ ገብስ ያመርታል እንበል። ይህ ገበሬ በሬውን ተጠቅሞ፣ ኣነስተኛ መሬት ላይ ኣብቅሎ፣ በኣብዛኛው በጥንታዊ መንገድ ኣርሞ፣ ኣጭዶና ወቅቶ ወደ ጎተራው ካስገባ በሁዋላ ለሚፈልጋቸው ኣንዳንድ የኑሮው ጉዳዮች ማለትም እንደ ጨው፣ ጋዝ የመሳሰሉትን ለመግዛት ሲሻ ካለችው ላይ ይቀንስና በኣህያ ጭኖ ወደ ከተማ ይዞ ይወጣል። ከተማ ውስጥ ሜዳ ላይ በተኮለኮሉ ገበያዎች ላይ ይዘረጋና ከተማ ላሉት ሰዎች እየሰፈረ ይሸጣል። የቀረችውን ገብስ ደግሞ ግማሹን እየቆላ ግማሹን ወይ ሚስቱ በድንጋይ ፈጭታ ወይ በባቡር ወፍጮ ኣስፈጭቶ ዱቄትና ውሃን ኣገናኝቶ እየጋገረ ይበላል። ከተማ ውስጥ ያለው ሰውም ልክ ገበሬው እንዳደረገው ኣስፈጭተው እየጋገሩ ይበላሉ።በገበሬውና በከተሜ መካከል ያለው መስተጋብር ድሮ ጊዜ እንደነበረው ቀጥታ ግንኙነት ነው። ከተማ ወይም ገጠር ያለው ሰው ገብሱን ጠላ ማድረግ ከፈለገ ኣንድ ኩንታል በእሳት ኣቃጥሎ ኣሻሮ ኣድርጎ ጥቂት ጠላ ይወጣውና በዚያ ለመደሰት ይሞክራል። ገበሬው በገብስ ውስጥ እስካሁን ያየው ኣቅም(potential) ጥቂት ሲሖን በነዚያ ዙሪያ ብቻ በጥንታዊው መንገድ እየተጠቀመ ይኖራል። የኢትዮጵያ የግብርና ችግር ያለው እዚህ ጋር ነው። በተጠቃሚውና በኣምራቹ መካከል መሃል ላይ ሰንጥቆ የገባ ሳይንስ የለም። ገበሬውና ከተሜው ቀጥታ እየተገናኙ በዱሮው የኣኗኗር ዘይቤ እየተጠቀሙ ስለሚኖሩ በምግብ በኩል ያለን ዋስትና ሳይሻሻል ቆየ። በመሃል የመጣው ክፍተት(gap) የግብርናው ኢንዱስትሪ ኣለመስፋፋቱ ሲሆን ይህ ኢንዱስትሪ ቢስፋፋና ምርቱን በቴክኖሎጂ ሂደት ውስጥ ኣስገብቶ ኣባዝቶ፣ ኣክሞ፣ ፕሪዘርቭ ኣድርጎ ወደ ተጠቃሚው ቢያደርስ የምግብ ዋስትናቸን ይረጋገጥና በዚያ በኩል የኢኮኖሚ ጥርመሳ ውስጥ ለመግባት ይቻላል። የኢትዮጵያ የዘመናት የምግብ ዋስትና ኣለመረጋገጥ ችግር የመጣውና ኣሁን ድረስ ፈተና የሆነብን በቂ ምርት ስለማናመርት ብቻ ኣይደለም። ኣልፎ ኣልፎ ተረፈ ምርትም ይገኛል። በልግ ወይም መኸር ሲሰጥ ምርት የሚትረፈረፍበት ጊዜ ነበር ። ይሁን እንጂ ምርት በሰጠ ሰዓት ገበሬው ለጋስ ይሆንና ወደ ከተማ ሄዶ ሲሸጥ ከተሜው የሚገዛው ሁል ጊዜም በሚፈልጋት በወር ቀለቡ ልክ ብቻ ነው። ኣንድ ጊዜ በ1990 ዎች ኣካባቢ በቆሎ በከፍተኛ ሁኔታ ተመርቶ ነበር። የኣንድ ኩንታል በቆሎ ዋጋ እስከ ሃያ ብር ድረስ ወርዶ ገበሬው የሚገዛው ኣጥቶ ሲንከራተት ነበር። ያቺ ሃያ ብር የገበሬውን የትራንስፖርት እንኳን ኣትሸፍንም። ትንሽ ኤክስፖርት ለማድረግ የተሞከረ ቢሆንም ግን ገበሬውን ገዝቶ ፕሪሰርቭ ለማድረግ እንኳን ኣልተቻለም ነበር።ይህ ችግር የመጣው በመሃል የተፈጠረ ክፍተት ስላለ ሲሆን ይህ ክፍተት የግብርናው ኢንዱስትሪ ኣለመስፋፋት ነው። ይህንን ምርት እየገዛ ፕሪዘቭ ቢያደርግ በቆሎን በተለያየ መንገድ እያዘጋጀ ወደ ተጠቃሚ ቢያደርስ ኣክሞ ኣባዝቶ ቢሸጥ ምርቱ ይበዛል ገበሬውም ለፍቶ ለፍቶ የልፋቱን ዋጋ ያገኘል። ጃፓኖችና ኮርያዊያን ቻይናዎች በሩዝ ውስጥ ያለውን ኣቅም በሚገባ እየተጠቀሙበት ነው። የሩዝ ቅባት፣ የሩዝ ዳቦ፣ የሩዝ ኣይብ የሩዝ ብስኩት፣ የሩዝ ፓስታና ማኮረኒ የሩዝ ዘይት፣ የሩዝ ኬክ፣ ስንቱ ተዘርዝሮ። በኢትዮጵያ ውስጥም የግብርናው ኢንዱስትሪ መጠናከሩ የሚጠቅመው ያሉንን እጅግ ብዙ ኣዝርእት እያባዛን ብዙ ነገር ኣድርገን እየሰራናቸው የምግብ ዋስትናችንን ለማስከበር ያስችለን ነበር።የግብርናው ኢንዱስትሪ ጣልቃ መግባት ያለበት ብዙ ለማምረት የሚያስችሉ ግብዓቶችን መጠቀሙና ማቅረቡ ላይ ለመስራት ብቻ ሳይሆን የተመረተውን ምርት ማከም፣ ማባዛትና መጠበቅ የሚያስችል ሂደት ስለሚያስፈልግ ነው። በኣሁኑ ጊዜ ዘይት ምን ያህል ውድ እንደሆነ ይሰማል። ዘይትን ከኑግና ከሰሊጥ ብቻ መጠበቃችን እና የኑግና የሰሊጥ ምርት ደግሞ ለውጭ ምንዛሬ ትንሽ ደለብ ያለ ገንዘብ ስለሚያስገኝ መንግስትም ወደ ውጭ በመላኩ የሚያገኘው ዶላር ስላጓጓው ዘይት በሃገራችን ኣልቀመስ ኣለ። የሚገርመው ግን ይህንን የዘይት ፍላጎት ክፍተት ለመሙላት ከሌሎች ኣዝርእት ለምን በስፋት እንደማይሰራ ነው። ለምን የገብስ፣ የስንዴ፣ የበቆሎና የሌሎች ኣዝርዕቶች ዘይት ኣይመረትም? ብለን ብንጠይቅ ዞሮ ዞሮ ያው ቅድም ያነሳነውን ክፍተት ማለትም የግብርናውን ኢንዱስትሪ ኣለመጠናከር ነው የሚነግረን። እነዚህ ኣዝርዕቶች ሁሉ ለምግብ ዘይት ለመሆን የሚችል እምቅ ሃይል ኣላቸው ነበር። በፍራፍሬም በኩል ያለው ችግር ይሄው ነው። ኣንዴ በኣንድ ወቅት የሚመረትን ፍራፍሬ በሁዋላ ቀር መንገድ ስለምንጠቀምበት ሳይባዛ ይቀርና የፍራፍሬ ፍላጎታችንን ሳያሙዋላ ቀረ። በስጋ በኩል ደግሞ ምንም እንኳን ብዙ የቀንድ ከብት ቢኖረንም በስጋ ምርት በኩል በጣም ዝቅተኛ የሆነ ኣቅርቦት ነው ያለን። ብዙ ከብት መኖሩ በኣንድ በኩል ከፍተኛ ማስጋጥ(over grazing) ስለሚያመጣ መሬቱን በማራቆት በኩል ከፍተኛ ችግር ያመጣል። ለስጋ የሚሆኑ ከብቶችን ሰብሰብ እያደረጉ የማድለብ ስራ ለብቻው መስራት ከባድ ኣልነበረም።ሌላው ደግሞ ኢትዮጵያዊያን የተለያየ ኣመጋገብ ባህል ያለን በመሆኑ እንደየ ባህሉ በኣጭር ጊዜ በብዛት ሊራቡ የሚችሉ የእንስሳት ዓይነቶችን ማርባት ለስጋ ምርት ኣቅርቦት ይረዳል። ከዚህም በላይ ገበሬውን ከሁለገብ የእርሻ ባህል እያወጡ ወደ ኣንድ የግብርና ስራ እንዲያተኩር የማድረግ ስራም መስራት ያስፈልጋል። ለዚህ ሁሉ የግብርናው ኢንዱስትሪ መስፋፋት በኢትዮጵያ ውስጥ ወሳኝ መሆኑን ያሳያል።ሌላው ጃፓኖች ይጠቀሙበት የነበረ ኣንድ መንደር ኣንድ የተለየ ምርት(one village one special product) ለኢትዮጵያ ትልቅ ትምህርት ይሆን ነበር። በዝንጅብል የሚታወቀውን ኣካባቢ ሌላን ችላ ብሎ ዝንጅብል ላይ እንዲያተኩር፣ ሁለገቡን ችላ ብሎ ሃይሉንና ጉልበቱን ወደ ኣንድ ኣቅጣጫ እንዲያዘነብል ማድረግና ገበያ መፍጠር ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ ሚና ኣለው። ሌላው ደግሞ የገበሬውን ኣሰራር ለመቀየር በሁሉም ገበሬ ላይ ኢንቨስት እያደረጉ ከማቃመስ ይልቅ ኣንድ ፐርሰንት ሊሆን የሚችልን ገበሬ ይዞታውን በማስፋት ወይም በማስፈር ይህንን ኣነስተኛ ቁጥር ያለውን የለውጥ ሃዋርያ ኣድርጎ ሜካናይዝድ በማድረግ በነዚህ ጥቂት ገበሬዎች የኢትዮጵያን የምግብ ኣቅርቦት ማሻሻል ይቻላል። የኢትዮጵያ ገበሬ የማይሞክረው የለም። ቅይጥ እርሻ (mixed farming) የሚባለውን እርሻ እየሰራ ሁሉንም እየሞከረ የሚኖር ነው። ይሄ የሚበረታታ ኣይደልም።ይህን ገበሬ ከእንዲህ ዓይነቱ ኣሰራር እያወጡ በኣንድ የግብርና ስራ ላይ እንዲያተኩር ማድረጉ ምርት እንዲጨምር ያደርጋል። ለምሳሌ ያህል ለሺህ ዓመታት በበሬ የሚያርሰውን ገበሬ ኣራትና ኣምስት እየሆነ በቡድን ኣንድ ትራክተር እንዲገዛ ማድረግ ይቻላል። ይህ ገበሬ ይህን ለማድረግ የበሬው ዋጋ ይበቃዋል። ይህን ማድረጉ ጥቅሙ ኣንደኛ ከፍተኛ ማስጋጥን ስለሚቀንስ የመሬቱን መሸርሸር ይቀንሳል። በሌላ በኩል በሬ በመጠበቅ ስራ ምክንያት ከትምህርት ያስቀረውን ልጁን ወደ ትምህርት ቤት ይልካል። በኣመት ሁለቴና ሶስቴ ለማረስ ሲል በየቀኑ የሚቀልበውን በሬ ወጪ ስናየው ብዙ ስለሆነ ከወጪም ይተርፋል። በሌላ በኩል የማድለብ ዝንባሌ ያለው ገበሬ ይህን ስራ በዘመናዊ መንገድ ኣድልቦ እንዲሸጥ እድሉን ያሰፋለታል። መሬት የግል መሆኑ ኣንዱ ጠቀሜታው ኣንዳንድ ገበሬዎች መሬታቸውን ሸጠው ወደ ሌላ የግብርና ስራ እንዲሰማሩ እድል ስለሚሰጥ ነው። መሬቱን የሸጠው ገበሬ ለምሳሌ የእርባታ፣ የወተት ምርት ወይም ሌሎችን ስራዎች ሊሰራ ሲችል ኣነስተኛ መሬት የነበረው ሰው ደግሞ ሌላ ገዝቶ መሬት ሲጨምር የተሻለ ምርትን ማምረት ይጀምራል። የመሬት ባለቤትነት ሲረጋገጥ ገበሬው መሬቱን እየሸጠ ጥሎ ይሄዳል ብሎ ማሰብ ተላላነት ነው። ገበሬው ሞኝ ኣይደለም። ከሸጠም ሾጦ ሊሰራ ላሰበው ጉዳይ መነሻ እንዲሆነው ነው። ኣንዳንዴም የራሱን መሬት ሸጦ ሌላ መሬት ሊገዛም ሊያስብ ይችላል። ኣንድ ስለ ልጆቹ ስለ ራሱ የሚያስብ ገበሬን ሸጦ ከተማ ይገባል ወይም ገበሬው ሁሉ እየተነሳ ይሸጥና የድሮው የፊውዳል ጊዜ ይመለሳል ማለት የኢትዮጵያን ገበሬ ኣለማወቅ ነው። ይልቅ ከፍ ሲል እንዳልኩት የመሬት ባለቤትነት መብት ሲረጋገጥ ገበሬው ከኣንድ የእርሻ ስራ ወደ ሌላ የእርሻ ስራ ለመዛወር መነሻ ሊሰጠው ይችላል።
ሌላው ጉዳይ ኣንዳንድ የገበሬ ልጆች ወደ ከተማ የመፍለሳቸው ጉዳይ መንግስትን ሊያሳስበው የሚገባ ጉዳይ ኣልነበረም። ይሄ ሂደት የለውጥ ሂደት ውጤት ነው። በተግባር እንደሚታየው ባደጉ ኣገሮች ሁሉ የገበሬው ቁጥር እየቀነሰ ነው የሚሄደው። ይሄን ማቆም ኣይቻልም በጎም ነው። ከተሜነት ሲጨምር ኣንዱ የእድገት ነጂ የሆነው የፍላጎት ሃይል (Demand force)እንዲጨምር ስለሚያደርግ ለእድገት ኣስተዋጾ ኣለው። ኣሜሪካንን ብናይ የገበሬው ቁጥር ሁለትና ሶስት ፐርሰንት ነው። ጃፓንን ብናይ ከኣንድ ፐርሰንት በታች ነው። ግማሽ ሚሊዮን እንኳን የማይሞላ ገበሬ ነው ያላት። በመሆኑም ኢትዮጵያም የገበሬው ቁጥር እየቀነሰ የመሬት ይዞታ እየሰፋ መሄዱ መልካም ሲሆን ከገጠር ወደ ከተማ የሚፈልሰውን ገበሬ ኣዳዲስ በሚፈጠሩ የግብርና ኢንዱስትሪዎች ላይ የማሰማራት ስራ መስራት ኣስፈላጊ ነው።ሌላው የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በዝናብ ላይ ብቻ ጥገኛ የሆነውን ገበሬ ለምን በኣካባቢው ያሉትን ወንዞች እንዲጠቀም እንደማይደርግ ኣይገባም። ከወንዝ የሚገኝን ውሃ በርቀት ማሳ ላይ ወስዶ ማፍሰስ እንዴት ይሳነናል። ለዚህ ከባድ የሆነ የመስኖ ልማት ስራም ኣያስፈልግም። ቢያንስ እዚያው ኣገር ቤት ሊመረት የሚችል የሸራ ቧንቧ ሰርቶ ማኑዋል በሆነ የውሃ መግፊያ መሳሪያ ውሃን ኣስፈንጥሮ ማሳን ማጠጣት በጣም ቀላል ስራ ሲሆን ይህን በስፋት ኣናይም። በከፍተኛ ወጪ የሚሰሩ የመስኖ ግድቦችን እያቀድን ገበሬውን ሳንደርስለት ሳናሳየው በመቅረታችን ያሳዝናል። የሸራ ቧንቧ ቢሰራና የእርሻ ተማሪዎች ኣንድ ማኑዋል ማሽን ቢፈጥሩ ገበሬው ከወንዙ ራቅ ያለ ቦታ ሳይቀር ደርሶ ሊያለማ ይችል ነበር። ባለፈው ጊዜ ኣንድ የሚገርም ዜና ተሰማ። በመላው ኣገሪቱ ገበሬው ውሃ ኣቁር ተብሎ ጉድጓድ ሲቆፍር ከረመ። ሁዋላ ላይ ዝናብ ሲመጣ ጉድጓዱ ውሃ ይሞላና ሲያበቃ ክፍቱን ስለሆነ ኣንዳንዴ ጥጆች ኣልፎ ኣልፎም ህጻናት ገቡ ተብሎ ከላይ በመጣ ትእዛዝ የተቆፈረው ጉድጋድ እንዲደፈን ተደርጓል። ሌሎች የተፈጥሮ ምንጮችና ጉድጓዶች ይህ ኣዋጅ ሲመጣ ምን እንደዋጣቸው ኣልታወቀም። በስንት ወጪ የተቆፈርን ጉድጓድ እንደገና ጥጃ ኣለቀ ተብሎ የወባ መራቢያ ሆነ ተብሎ ድፈኑ ተባለ። እንዴት መክደኛ ማበጀት ይሳነናል? የሚለው ይገርማል።ገበሬውስ ኣይታዘብም ወይ? ነገ የምናስተምረው ትምህርት ላይ እምነት ኣያጣም ወይ? ብለን ማሰብ ያስፈልጋል።ለዚህ ስህተት ይቅርታስ የጠየቀ ኣካል ይኖር ይሆን? ይሄ በሃገሪቱ የግብርና ኤክስቴንሽን ስራ ላይ ከፍተኛ ኣሉታዊ ተጽእኖ ኣለው። ገበሬው እምነቱ እንዲሳሳ ስለሚያደርግ ሌላ ኣዲስ ቴክኖሎጂ ሲመጣ ለማስረጽ ከባድ ፈተና ያመጣል። ከመነሻውም ቢሆን የሆነ ፓይለት ሙከራ ሳይደረግ በሙሉ በሃገሪቱ ጉድጓድ እንዲቆፈር መደረጉ ምናልባትም ከሙያተኞች ኣካባቢ ሳይሆን የፖለቲካ ውሳኔም ይመስላል።ሌላው ድርቅን ለመቋቋም የሚረዳን ደግሞ የከርሰ ምድር ውሃን በተገቢው መንገድ መጠቀም ነው። ዋናው ለማለት የፈለኩት ጉዳይ ችግሮቹ ከባድ ሆነው ሳይሆን ቀለል ያሉ መፍትሄዎችን ያለማየት ነገር ይንጸባረቃል። ኣንድ ጊዜ ኣንድ መንፈሳዊ ሰው ሲያስተምሩ የሰማሁት ታሪክ በምናቤ ሲታየኝ ይኖራል። እኚህ ሰው ያስተምሩ የነበሩት ስለ ኣጋር ነበር። ኣጋር በመጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተጠቀሰው የኣብርሃም እና የባለቤቱ የሳራ የቤት ሰራተኛ ነበረች። ሁዋላ ላይ ከኣብርሃም ጋር በነበራት ግንኙነት ምክንያት ልጅ ትወልዳለች። ሳራ ጠልታት ነበርና ከእለታት ኣንድ ቀን ከቤት ኣስወጥታ ኣባረረቻት። ኣጋር ረጅም ጉዞ ተጓዘች።በቤርሳቤህ ምድረ በዳ ተንከራተተች።የኣብርሃም ሚስት ሳራ የሰጠቻት ኣንዲት ኣቁማዳ ውሃ ኣለቀች። እሷና ልጇ በውሃ ጥም ተቃጠሉ። በተለይ ልጁ በውሃ ጥም ምክንያት ሊሞት ደረሰና ማቃሰት ሲጀምር የልጁዋን ሞት እንዳታይ ብላ ፈንጠር ብላ ታለቅሳለች። ሁዋላ ላይ የእግዚኣብሄር መልዓክ ተገለጠላትና የህጻኑን እንባና ልቅሶ ሰምቻለሁና ኣይዞሽ በውሃ ጥም ኣትሞቱም ኣላት። ዓይኑዋን ከፈተላትና ዘወር ብላ ስታይ የውሃ ጉድጓድ ኣየች። የሚገርመው ውሃ ጥም ይዙዋት የምትሰቃየው በኣካባቢው ውሃ ሳይኖር ቀርቶ ሳይሆን ኣካባቢዋን ስላልቃኘች ነው። የውሃ ጉድጓድ ስር ቁጭ ብላ ነው ታለቅስ የነበረው:: ኣጋር ምንጩ ኣደናቅፎ ካልጣላት ወይም ፊት ለፊት ካልተደቀነባት ግራና ቀኝ የማታይ ነበረች ብለው ኣስተማሩ። ርግጥ ነው ኣንዳንዴ በቀላሉ በኣካባቢያችን ልናያቸው የሚገቡ መፍትሄዎችን ሳናይ እየቀረን እንዲሁ ከድህነት ሳንወጣ ቆይተናል።
የደን ሃብታችንን በሚመለከት ድንጋይ ያለቀብን ይመስል ብዙ ያዘንን ሲሆን ከዚህ ይልቅ መትከሉ ይሻላል። ሌላው እየተከልንም መቆረጡ መጨፍጨፉ ኣይቀርምና ገበሬውን ከማስተማሩ ጎን ለጎን ኣማራጭ ሃይል መፈለግ ነው። የሶላር ኤነርጂን ጨምሮ ሃይልን ማቅረብ ካልተቻለ ጭፍጨፋው ኣይቆምም።ገበሬው ደን የሚጨፈጭፈው ዝንባሌ (hobby) ስለሆነው ኣይደለም። ኑሮው ሁሉ በከፍተኛ ሁኔታ ከዛፍ ጋር ስለተቆራኘበት ነው። መስራት ለፈለገው ነገር ሁሉ እንጨትና ገመድ ወሳኝ ሆነውበት ነው። ሞፈር ቀንበሩ፣ቅትርትና ድግሩ፣ ቤቱ መቀመጫው፣ የከብቶቹ ቤት፣ ምርኩዙ የሚበላበት ገበታ፣ የሚተኛበት ኣልጋ እግር፣ ምግቡን የሚያበስልበት ሃይል ከዛፍ ጋር የተያያዘ ነው። እነዚህን ጉዳዮች ብረት እንኳን ቢከብድ ከፕላስቲክ የሚሰሩ የገበሬው መገልገያ እቃዎች እንደልብ መገኘት ቢችሉ ጭፍጨፋውን ይቀንሰው ነበር። የፕላስቲክ ቀንበርና ቅትርት መስራት፣ ኣንዳንድ ወደ ፕላስቲክ ሊቀየሩ የሚችሉ የገበሬውን የመገልገያ እቃዎች መቀየር ብዙ ከባድ ስራ መሆን ኣልነበረበትም። ሌላው ደግሞ ከተሜው ራሱ ከተማ ይኑር እንጂ የሃይል ኣቅርቦቱ ተመጣጣኝ ስላልሆነ ከፍተኛ የከሰል ምርትን ከገበሬው ይጠብቃል። ይህ ደግሞ ለገበሬው ትንሽ የኢኮኖሚ ኢንሴንቲቭ ስለሰጠው ደን እያጠፋ ወደ ከተማ ከሰል ጭኖ ይመጣል። ይህ ጉዳይ የሚቀንሰው ከሰልን በመከልከል ሳይሆን ኣማራጭ ሃይል ለከተሜው በማቅረብ ነው። ኣብዛኛው የከተማ ነዋሪ ለምግብ ማብሰያው የሚጠቀመው እንጨት በመሆኑ በከተሜውና በገጠሩ ነዋሪ በኩል ከፍተኛውን የሃይል ክፍተት የሞላው እሱ በመሆኑ ጭፍጨፋው ቀጥሎኣል።
የኣፈርና ውሃ ጥበቃችን ትልቅ ችግር ያለበት ነው። የኢትዮጵያ ገበሬ በስራ በታታሪነት የማይታማ ጀግና ሲሆን በኣፈርና ውሃ ጥበቃ በኩል ያለው ግንዛቤ፣ ለኣፈር መሸርሸር የሰጠው ዋጋ ግን ዝቅተኛ ሆኖ ይታያል። ይህ ችግር በርግጥ ኮንሶን ኣይመለከትም። የኮንሶ ህዝብ ከባህል ጋር ተያይዞ የዳበረ ግንዛቤ ስላለው የኣፈር ዋጋው ውድ ነው። በሰሜን ኣካባቢ በኣንዳንድ ግብረሰናይ ድርጅቶችና በግብርና የልማት ሰራተኞች መሪነት የሚሰራው የመቀልበሻ ቦይ፣ ክትር፣ ግማሽ ጨረቃና እርከን የላይኛውን ኣፍር ለመጠበቅ የሚጠቅም ነው። ከሁሉ በላይ ግን የጎልማሶች ትምህርት በገበሬው ኣካባቢ መሰጠቱ ወሳኝ ነገር ነው።ማንኛውም ዜጋ በውዴታ ግዴታ መማር ኣለበት። ኣለበለዚያ ኣዳዲስ ቴክኖሎጂዎችንና ግብዓቶችን ገበሬው የመቀበል ኣቅሙ ዝቅተኛ ይሆናል።ሌላው ደግሞ ገበሬውን ለውጭው ኣለም የማጋለጥ ስራና የቅስቀሳ ወይም ኣኒሜሽን ስራ በሰፊው ቢሰራ ኣካባቢውን ሊለውጥ ይችላል። ኣርብቶ ኣደሩ የእርባታ ስራውን ወደ ዘመናዊነት እንዲቀይር ሞባይል ትምህርት ቤቶች ጠንክረው ማስተማር ካልቻሉ፣ የረጋ ኑሮ እንዲኖር ካልታገዘ ህይወቱ ሳይለወጥ የዚህን ዓለም ብርሃን ሳያይ ይኖራል።
በቅርብ ቀን የግብርና ሚንስትሩ እንደገለጹት ግብርናው በዓመት በዓማካይ በስምንት በመቶ ምርቱ እያደገ ነው የመጣው ብለዋል። ይህ ከሆነ የህዝብ ብዛት የሚያድገው በሶስት በመቶ ሲሆን የኢትዮጵያን ህዝብ ሳይራብ ሊያቆይ የሚችል እድገት ኣለ ማለት ነው።በሌላ በኩል መንግስትም በየዓመቱ የእለት ደራሽ ርዳታ ሲለምን ነው የሚታየው። ግብርናው በዚህ ከፍታ የሚያድግ ከሆነ ምርቱ የት ሄደ? ተብሎ ይጠየቃል። በዓማካይ እስከ ሶስት ሚሊየን ህዝብ በየዓመቱ ርሃብ ኣለ:: በቅርቡ እንኳን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንዳስታወቀው ስድስት ነጥብ ኣምስት ሚሊየንን ህዝብ ለመመገብ ዝግጅት ተደርጓል ።
በኢትዮጵያ ውስጥ ከገበሬው ይልቅ የከተሜው ችግር እጅግ ውስብስብ ነው። በኣቅርቦትና በዲማንድ መካከል ሰፊ ልዮነት የሚታይበት የህብረስተሰብ ክፍል ያለው ከተማው ኣካባቢ ነው።የከተሜውን ችግር እንደ ገበሬው ችግር በኣንድ ወጥ እይታ ለማስቀመጥ ይከብዳል። የገበሬውን ችግር በማጠቃለል የጋራ መፍትሔ ለመፈለግ በኣንጻራዊነት የሚቀል ሲሆን የከተሜው ግን ሲበዛ ውስብስብ ከመሆኑ የተነሳ በተጠቃለለ መልኩ ችግሩን ለማስቀመጥ ይከብዳል። የትናንሽ ከተሞች ነዋሪው፣ የመካከለኛ ከተሞች ነዋሪው፣ የከፍተኛ ከተሞች ነዋሪው፣ የመንግስት ሰራተኛው፣ የነጋዴው፣የጎዳና ተዳዳሪው፣ የኣነስተኛ ንግድ ሰራተኛው የሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ችግር የሚገናኝበት የጋራ ባህርይ ቢኖረውም ደግሞ ይለያያል። የቤት ችግር መፍታት ደግሞ ከመንግስት የሚጠበቅ ቢሆንም እስካሁን ችግሩ እየከፋ ሲሄድ ነው የሚታየው። :: የዚህን ማህበረሰብ ችግር ለመፍታት ግብርናውን መሰረት ያደረገ የጂዲፒ ጭመራ ስራ ነው የሚሻለው። ኣጠቃላይ የሆነው እድገት ከግብርናው ገፍቶ ሲመጣ የከተማውን ህዝብ ጓዳ ሁሉ ቀስ እያለ ይለውጠዋል። ይህ ማለት ኢንዱስትሪው ይቀራል ማለት ኣይደለም። ግብርናው ይደግ ሲባል ግብርናው ኢንዱስትሪያላይዝድ ይሁን እያልን ነው። ይህ ማለት የኢንዱስትሪው ስራ ኣለ:: የሚለየው የሚቋቋሙት ኢንዱስትሪዎች በኣብዛኛው ግብርናውን በገፍ የሚያስመርትና የተመረተውን የሚያክም የሚያበዛ የሚያከማች ከዚያም ወደ ኤክስፖርት የሚሄድ ለማለት ነው።
ሌላው ኣገራችን እስካሁን ድረስ የዓለም ንግድ ድርጅት ዓባል ኣለመሆኗና የዓባልነት ጥያቄው መጓተቱ የሚያሳየው የመንግስትን ትልቅ ድክመት ነው። ኢትዮጵያ ቶሎ ቶሎ ብላ ፎርማሊቲውን ኣሙዋልታ መግባት ነበረባት። በተለምዶ የዚህ ድርጅት ኣባል መሆን ጨቅላ የሆኑ ኣገር በቀል ድርጅቶችን ሊያቀጭጭ ይችላልና ለኣዳጊ ኣገሮች ኣስቸጋሪ ነው የሚለው የሚሰራ ኣይመስልም። በመጀመሪያ ደረጃ ኢትዮጵያ ምን ጨቅላ የሆነስ ኢንዱስትሪ ኣላት? ብለን መጠየቅ እንችላለን። ሁልጊዜም ኤክስፖርት የሚደረገው የግብርና ውጤቶች ማለትም የቅባት እህሎች፣ ቆዳና ሌጦ ቡናን የመሳሰሉትን ነው። እነዚህ ምርቶች ደግሞ ምን ጊዜም በዓለም ገበያ ላይ ተፈላጊ ናቸው። ሌላው ወደዚህ ድርጅት በመግባት የሚኖረው የንግድ ልውውጥ ከለማው ዓለም ጋር ብቻ ዓይደለም። ኣባል ከሆኑት ኣገሮች መካከል ሰባ ኣምስት በመቶ የሚሆኑት በማደግ ላይ ያሉ ኣገሮች በመሆናቸው በዚህ ድርጅት መካከለኛነት ከነዚህ ኣገሮችም ጋር የሁለትዮሽ ስምምነቶች ማድረግ የሰለጠነ ሲስተም ውስጥ ገብቶ ንግድ ለመለዋወጥ ሰፊ እድል ይሰጣል። ከበለጸጉ ሃገራት ጋር የሚኖረው የሁለትዮሽ ስምምነትም ኢትዮጵያ ያሉዋትን ተፈላጊ ምርቶች ጥራት በመጨመር ገቢዋን ምርቷን ከፍ ለማድረግ እንድትችል መነሳሳትን ይፈጥርላታል። ከሁሉ በላይ ያሉዋትን ምርቶች ቢያንስ በኣንድ ደረጃ በኢንዱስትሪ ሂደት ውስጥ ኣሳልፋ የምታቀርብበትን ሁኔታ ለመፍጠር የሚያስችል ሲስተም ውስጥ እየገባች እንድትሄድ ያደርጋታል።ለምሳሌ ያህል ቡናን ብንወስድ ቢያንስ ቆልቶ ኤክስፖርት ለማድረግ ሽንጧን ገትራ ልትከራከርና ልታሳምን ይገባታል። የዓለም ንግድ ድርጅት በሃገሮች መሃል ፌር ትሬዲንግን የሚያራምድ በመሆኑ በዚያ ጥላ ስር ሆና ከብዙ ሃገራት ጋር እንዲህ ዓይነት የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ለማድረግ ጥቅሙዋን ኣስጠብቃ የሌላውን ጥቅም ኣክብራ የንግድ ስራዋን እንድትሰራ ያግዛታል። ይህቺን ዓለም ከንግድ ልውውጥ ውጭ ማየት ይከብዳል። በመሆኑም ይህን እድል ተጠቅማ በዚያ መድረክ ላይ ወገብዋን ታጥቃና ጠንክራ ሃሳብ እያመጣች ምርቶቹዋን በፌር ትሬድ መርህ መሰረት ማስወጣትና ማስገባት ካልቻለች ተገልለን ኣናድግም:: ኢትዮጵያ ምርቶቹዋን ይዛ በእንደዚህ ዓይነት ዓለም ኣቀፍ ተቋም ፊት መቅረብ ካልቻለች በተደራጁ ሃገራት በሆነ ሲስተም ውስጥ በገቡ ሃገራት ልትበለጥ ትችላለች። ስለዚህ እንዲህ ዓይነት እድሎችን ቶሎ ወደ ራስ እድል የመቀየር ስራ ካልተሰራ እድገት ኣይመጣም።
በዚህ ድርጅት ውስጥ ሳንታቀፍ ከዓለም የንግድ ሲስተም ወጥተን በግላችን ስንዳክር ቆይተን ገበሬውን ተስፋ በማስቆረጥ ጫት ማስተከል ትልቅ ታሪካዊ ጥፋት ነው። የረጅም ጊዜ ትልም ኖሮን በእንዲህ ዓይነት ዓለማቀፋዊ ድርጅቶች መድረክ ላይ የኢትዮጵያን የቡና ገበሬ ችግሮች ማንሳት ካልቻልን ስንፍና ይሆንብናል። ቡና ምንም እንኳን ሃገራችን የሚበቅል ቢሆንም ንብረትነቱ የኛ ቢሆንም የዓለም ህዝቦች ገጸ በረከትም በመሆኑ በኣንድ በኩል ለፌር ትሬድ እየተሙዋገትን በሌላ በኩል ግን ምርታችንን ከፍ የማድረግ ሃላፊነት ኣለብን። ገበሬው የበለጠ እንዲያመርት ማበረታታት ይገባናል። የኢትዮጵያ ኤክስፖርት በዋናነት የግብርና ውጤት በመሆኑ ኢንቨስተሮችን ወደዚህ ሴክተር በመሳብና የግብርናውን ኢንዱስትሪ በማሳደግ የሚላኩትን ምርቶች መጨመር ከዚያም ገቢን ለማሳደግ ያስፈልጋል ። ውድድር ይበዛብኛልና ትንሽ ለብቻየ ልቆይ ለማለት የሚያስችል ዓለም ውስጥ ኣይደለንም። የዚህ ድርጅት ኣባል ባንሆንም በዚህች ፕላኔት ላይ ሆነን ከውድድር ኣንወጣም። ውድድርን እንደ የትምህርት ገበታና እንደ እድል እያዩ ኣዳዲስ ኣሳቦችን እያፈለቁ በገበያ መሃል መቆም ነው የሚያዋጣው።
በርግጥ መንግስት ወደዚህ ድርጅት ለመግባት ኣንዱ ያስፈራው ነገር በከፍተኛ ሁኔታ የንግድ ስራ የያዘው መንግስት በመሆኑ፣ግልጽነት የሌላቸው የንግድ ስራዎች ውስጥ በመግባቱ ከነዚህ ግልጽነት ከጎደላቸውና በሚጥር ከሚሰሩ ንግዶች በሚገኘው ትርፍ ተቃዋሚን ዝም ለማሰኘት መጠቀሚያ መሆኑ፣ ከዚያም የሰርቪስ ሴክተሩ እንደ ባንክና ቴሌን ወደ ግል ለማዛወር ባለመፈለጉ ነው። እነዚህን ተቋማት በተለይም ቴሌን ስናይ የመንግስት ዋናው ስጋት ኢኮኖሚያዊ ጉዳይ ሳይሆን የሰኪዩሪቲ ጉዳይ ነው። ኣንዱ የህወሃት የመጨቆኛ መሳሪያ የሆነው ይህ ተቋም ነው። ዜጎች በሃገራቸው የፈለጉትን በስልክ የማውራት መብታቸውን የነፈገ፣ ዓለም በኢንተርኔት ኣገልግሎት ሰማይ በደረሰችበት ዘመን ኢትዮጵያዊያን የፈለጉትን መረጃ እንዳይለዋወጡበት የተደረገበት ሁኔታ ነው ያለው። በመሆኑም የቴሌ ወደ ግል መዛወር ለኢትዮጵያዊያን የነጻነት ጥያቄም ሆኖ ይታያል። ባንኮችም ቢሆኑ ኣብዛኛዎቹ በፖለቲካ ፓርቲዎችና በመንግስት ተይዘው በኣድልዎ እንደሚሰሩ ይታወቃል። ባለፉት ሁለት ኣስርታት የሰማነው ጉድ ተቆጥሮ ኣያልቅም።
እንዴው የሆድ የሆዳችንን ኣወራን እንጂ ልማትን ኣምጥቶ ህይወት ለማሻሻል የሚቻለው በመጀመሪያ ደረጃ የህዝብ ችግር የሚያሳስበው መንግስት ሲኖር ነው። ኣለበለዚያ ዶክተር ኣክሎግ ቢራራ ኣዘውትረው እንደሚሉት ብልጭልጭ ነገረን እያሳዩን ብዙ ሊሰራ የሚችልን ሪሶርስ በብልጭልጭ ጉዳይ ላይ እያፈሰሱ እንዲሁ ኣብዛኛው ህብረተሰብ ከችግር ሳይወጣ ይቆያል። በመሆኑም በኢትዮጵያ ውስጥ ካለብን ሰፊ ችግር መላቀቅ የምንችለው ኣገር ወዳድ፣ የህዝብ ችግር የሚገባው መንግስትን መፍጠር ስንችል ነውና ሁላችን ለለውጥ መነሳት ይኖርብናል።ለውጡ ደግሞ ሁለንተናዊ ቢሆን መልካም ነው። ኣዲስ የኣስተሳሰብ ለውጥ ውስጥ መግባት ኣለብን። ያለፍንባቸውን የህይወት ልምዶቻችንን፣ ታሪካችንን፣ ኣሁን ያለንበትን ሁኔታ የወደፊቱን የሃገራችንን እጣ ፈንታ በሚመለከት የምንተነትንበትንና የምንገመግምበትን መንግድ እንለውጥ። ኣስተሳሰባችንን በመቀየር ነው ኣገራችንን የምንቀይረው።
እግዚኣብሄር ኢትዮጵያን ይባርካት
ገለታው ዘለቀ
geletawzeleke@gmail.com

ሦስተኛዋን ‹‹እሁድ››- በአራዳ ምድብ ችሎት (ጽዮን ግርማ)



የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ስድስቱን ጦማሪያንና ሦስቱን ጋዜጠኞች በሰንበት ቀን ለሚሰየም ተረኛ ችሎት መቅጠሩን የተለመደ አድርጎታል፡፡ ከቀናት በፊት በሦስቱ ብሎገሮች አቤል ዋበላ፣በፍቃዱ ኃይሉና ማኅሌት ፋንታሁን ላይ በተሰጠው የዐሥራ አራት ቀናት የጊዜ ቀጠሮ መሠረት የቀጠሮው ቀን ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2006 ዓ.ም ነበር፡፡ ዛሬ በዚህ ፍርድ ቤት ተገኝቼ የነበረውን ሁኔታ መከታተል ባልችልም ምንጮቼ የነገሩኝን ዝርዝር እንዲህ ጽፌዋለሁ፡፡
ጠዋት
እንደተለመደው ኹሉ የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰቦች፣ጓደኞች፣የአገር ውስጥና የውጭ ጋዜጠኞች የአራዳውን ምድብ ችሎት የጓሮ በር እያለፉ ወደ አሮጌው ፍርድ ቤት ግቢ መግባት የጀመሩት ጠዋት ሦስት ሰዓት ከመሙላቱ አስቀድሞ ነበር፡፡ አብዛኞቹ ከፍርድ ቤቱ ከፍ ብሎ በሚገኘው ማዕከላዊ ለሚገኙት እስረኛ ልጆቻቸው ቁርስ የማድረሻ ሰዓት ስለኾነ የፍርድ ቤት ቀጠሮ ሲኖር ከማዕከላዊ በቀጥታ ወደ ፍርድ ቤት ይመጣሉ፡፡ በዛሬው ችሎት ላይ ለመገኘትም ከቁርስ መልስ ሰብሰብ ብለው ነበር ወደ ፍርድ ቤት ግቢ የደረሱት፡፡
ፍርድ ቤቱ ሲደርሱ ግቢው በጸጥታ የተሞላ ነበር፡፡ አንድም የተከፈተ የችሎት በር አልነበረም፣ግቢውን ከሚጠብቀው አንድ ፖሊስ በስተቀር ሌላ ሰው የለም፡፡ ጠባቂው ፖሊስ ‹‹ዋናዎቹ ፖሊሶች›› ሲመጡ አንድ ላይ መሰብሰባቸው አይቀርም በሚል ይመስላል ወደ ፍርድ ቤቱ የሚገባውን ሰው በሙሉ አንድ ላይ ተሰብስቦ እንዲቆም ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ ሰዓቱ ረፈድ እያለ ሲመጣና ጸሐዩ ሲበረታ ግን ግቢው ውስጥ የቆመው ሰው ተበታትኖም ቢሆን ጥላ ፈልጎ እንዲቀመጥ ፈቀደ፡፡ የቀጠሮው ሰዓት እስኪደርስ ድረስ ሁሉም አመጣጡ እንደገጠመለት እየተቧደነ ባገኘው ነገር ላይ ተቀምጦ ፖሊስ ሊጠይቅ ይችላል ያሉትንና ፍርደ ቤቱ ሊሰጠው ስለሚችለው ትእዛዝ ግምታዊ መላምቱን እያስቀመጠ ጭንቀቱን በተስፋ ለማራገፍ ውይይቱን ቀጥሏል፡፡‹‹ተጨማሪ ዐስራ አራት ቀን ሊጠይቁባቸው ይችሉ ይኾን?›› አንዱ ይጠይቃል፡፡ ‹‹የሽብር ተግባሩን ጠቅሰው ሃያ ስምንት ቀን ይጠይቁባቸዋል›› ሌላኛው ሰው አስተያየቱን ይሰጣል፡፡ ከተሰበሰቡት ሰዎች መካከል በፍርድ ቤት ጉዳዮች በቂ ልምድ ያለው አንድ የሕግ ባለሞያ፤‹‹መዝገቡ በጊዜ ቀጠሮ ላይ የሚገኝ ቢኾንም ባለፈው ቀጠሮ ፍርድ ቤቱ የፖሊስን የሽብር ተግባርና የሃያ ስምንት ቀን የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ ውድቅ ስላደረገው ዛሬ መልሶ እሱን ማንሳት አይቻልም ፖሊስ ጥያቄውን እንደገና ማቅረብ ቢፈልግ እንኳን በይግባኝ እንጂ መልሶ በዚህ ችሎት የሚያቀርብበት ሥርዓት አይኖርም፡፡›› በማለት ሞያዊ አስተያየቱን ሰጠ፡፡ የሕግ ባለሞያው የተቀመጠበትን ዙሪያ ከበው የተቀመጡት ወዳጅ ቤተሰቦች አስተያየቱን ሰምተው ‹‹ቢበዛ ፖሊስ ሊጠይቅ የሚችለው ዐሥራ አራት ቀን ነው፤እሱንም ቢኾን የሽብር ተግባሩን ሳያካትት በማለት›› ተስፋን ለራሳቸው ሰነቁ፡፡
ከዚህ ቀደም በነበሩት ቀጠሮዎች ችሎቱ ሲሰየምበት ከነበረው ሰዓት እያለፈ ሲሄድ ሁሉም ሰው ግራ ተጋብቶ የነበረ ቢኾንም አምስት ሰዓት ሊሞላ ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩት አንድ ዕድሜው ከሃያ አራት የማይዘለው ጎርመስ ያለ ወጣት ወደ ፍርድ ቤቱ ግቢ ገብቶ ተረኛ ኾኖ መመደቡንና ነገር ግን ችሎቱም አለመከፈቱን የጽፈት ቤት ኃላፊም አለማግኘቱን በመግለጽ የፍርድ ቤቱ ሠራተኛ የሚመስለውን አንድ ሰው ጠየቀ፡፡ ለችሎት ጸሐፊዋ ስልክ ተደወለላት፡፡ እርሷ እስክትመጣም አስቀድሞ ተጠርጣሪዎቹን ይዞ ሊቀርብ ከመጣው መርማሪ ፖሊስ ጋር ወደ ውስጥ ዘለቀ፡፡
ሠላሳ ያህል ደቂቃዎች እንደተቆጠሩ እስረኞቹን ይዘው የመጡት ቁጡ (ከሌላው ጊዜ በእጅጉ የባሱ) የፌደራል ፖሊሶች ወደ ግቢው ገብተው ተበታትኖ የቆመውን ቤተሰብ እንደተለመደው ሰብስበው በአንድ መስመር አቆሙት፡፡ ማንም ሰው ፎቶ ማንሳት እንደማይችል፣ስልክን መነካካት ክልክል እንደኾነ በመግለጽ ማስጠንቀቂያ ሰጡ፡፡ ከፍርድ ቤቱ ግቢ ጀርባ ባለው መኪና ማቆሚያ ቦታ ለረጅም ሰዓት ተቀምጠው የቆዩትን ተጠርጣሪዎቹንም ይዘዋቸው ወደ ግቢው ገቡ፡፡ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች አቤል ዋበላና በፍቃዱ ኃይሉ እንደተለመደው በሰንሰለት ታስረው ገቡ፡፡ ማኅሌት ፋንታሁን እጆቿ በሰንሰለት ባይታሰሩም አንገቷን በሐዘን ቀብራ ነበር ወደ ግቢው የገባችው፡፡ በአቤል ፊት ላይ የጥንካሬ መንፈስ ቢታይም የበፍቃዱ ዐይኖች መቅላት ለሊቱን በምርመራ ሳያድር እንዳልቀረ ይጠቁማሉ፡፡
የእጆቻቸው ሰንሰለት ተፈቶ ችሎት ከገቡ በኋላ፤ከችሎት ውስጥ የሚወጣውን ምላሽ ለመጠበቅ ቤተሰብ ትንፋሹን ውጦ በቆመበት መጠባበቅ ጀመረ፡፡እንደሌላው ጊዜ ከአንድ ተጠርጣሪ አንድ ቤተሰብ እንዲገባ እንኳን አልተፈቀደለትም ነበር፡፡ ችሎቱ ከተሰየመ ዐሥር ደቂቃ እንኳን በቅጡ ሳይሞላው ለዘለፋ እና ለቁጣ የተዘጋጁ የሚመስሉ የፌደራል ፖሊሶች ወደ ተሰበሰበው ሰው ቀርበው ‹‹ግቢውን ለቃችሁ ውጡ እዚህ መቆም አይቻልም›› በማለት ማመናጨቅና መገፈታተር ጀመሩ፡፡ ‹‹ጠበቃው እስኪወጣ እንኳን እንጠብቅ የሚባለውን ከእርሱ ነው የምንሰማው›› ሲል ቤተሰብ ተማጸነ፡፡ፖሊሶቹ ጆሮ አልነበራቸውም፡፡ ኾን ብለው ሰዎችን ለማዋረድ የሰለጠኑ ይመስላሉ፡፡ ግፊያና ዘለፋውን ቀጠሉበት፡፡
አንዲት ሴት ፌደራል ፖሊስ እየተንደረደረች ወደ ተሰበሰበው ሰው ቀርባ ከፊት ያለውን ሰው መገፈታተር ጀመረች፡፡ ግፍተራው የበዛባት የበፍቃዱ ኃይሉ እህት ልቧ ወደ ታሰረው ወንድሟ ሄዶባት ቢያንስ ከችሎት ሲወጣ ለማየት እንድትችል ግፍተራውን እየተከላከለች ፍርድ ቤት ግቢው ውስጥ ቆሞ የመጠበቅ መብት እንዳላት በመግለጽ ለፖሊሷ ልታስረዳት ሞከረች፡፡ ፖሊሷ ግን ተቆጣች እጅግም ተናደደች፤‹‹የምን መብት ነው ያለሽ፤ውጪ ብዬሻለሁ ውጪ፤አንተ ዱላውን አቀብለኝ›› የሥራ ባልደረባዋ ዱላውን እንዲያመጣላት አዘዘችች፡፡ ያሁሉ ሰው በተሰበሰበበት ዱላ ተቀብላ ለመማታት ተጋበዘች፡፡ የበፍቃዱ እናት ግን አላስቻላቸውምና ልጃቸውን ለመከላከል ለመሃል ገቡ፡፡
ፖሊሷ ማንን ፈርታ እርሳቸውንም አብራ ገፈተረቻቸው ግቢውን ለቀው እንዲወጡ እያመናጨቀች ገፋቻቸው፡፡ የበፍቃዱ እናት የታሰረው ልጃቸውን ከኋላ ትተው ያልታሰሩትን ከፖሊስ ዱላ ለማስጣል እንባቸውን አረገፉት፡፡‹‹ዛሬ እናንተ ባለጊዜ ሆናችሁ ነው፤ፈጣሪ ፍርዱን ይሰጠናል›› በማለት ፍርዱን ከፈጣሪ ጠየቁ ፡፡ ሌሎችም አገዟቸው፡፡የእርሳቸው ለቅሶ ሌሎችን አስለቀሰ፡፡ ፖሊሷ ግን ዱላዋን ተቀብላ እያስፈራራች ይበልጥ ወደ ተጠጋች ሰዉ ግቢውን ለቆ የማይወጣ ከኾነ ዱላው የማይቀርለት መኾኑን በሚገልጽ አኳኋን እያመናጨቀች አባረረች፡፡ ራሳቸውን ከፖሊሷ ዱላ መከላከል እንደማይችሉ የገባቸው እናት በሁለቱ ልጆቻቸው ተደግፈው እየተላቀሱ ግቢውን ለቀው ወጡ ሌሎቹም ተከተሏቸው፡፡
ጠበቃው አቶ አመሐም ከችሎት ከወጡ በኋላ እንዳስረዱት ፖሊስ፤‹‹ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ በወንጀል በሥነ ሥርዓት ሕጉ አንቀጽ 59/2 መሰረት የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቀን በምርመራ ላይ ነበሩ፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ተጠርጣሪዎች ሚስጥራዊ በኾነ መንገድ በሕቡዕ በመደራጀት በሕጋዊ መንገድ ሥልጣን የያዘውን መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ ከሥልጣን ለማውረድ በማሰብ፣ ይህንንም ሐሳብ በውጭ አገር ከሚገኙ አሸባሪ ድርጅቶች ጋራ በመስማማትና አገሪቱን ለማተራመስ ትእዛዝ በመቀበል፣ትእዛዙን ለማሳካት የሚያስችላቸውን ገንዘብ በመቀበል፣እንዲሁም ስልጠና በመውሰድ በአገሪቱ ላይ ብጥብጥ ለማነሳሳትና ብጥብጡንም ለመምራት በመንቀሳቀስ የሽብር ተግባር ፈፅመዋል፡፡ በመኾኑም ይህን የሽብር ተግባር ለማጣራት እንዲረዳን በፀረ-ሽብር ዐዋጁ ቁጥር 652/2001 አንቀፅ 28 መሰረት ተጨማሪ 28 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠን እንጠይቃለን›› የሚለውን ቀደም ሲል አቅርቦት የነበረውን ማመልከቻ መልሶ አቀረበ፡፡
ጠበቃው በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል በነበረው ቀጠሮ ፖሊስ የተጠርጣሪዎቹን የቀጠሮ መዝገብ ወደ ፀረ-ሽብርተኝነት ለመቀየር አመልክቶ ውድቅ ተደርጎበታል፣ ፖሊስ ቀድሞ በተሰጠው የፍርድ ቤት ውሳኔ ቅር ከተሰኘ ይግባኝ ሊጠይቅ ይገባል እንጂ በተመሳሳይ ችሎት እና ጉዳይ ላይ በፍርድ ቤት ውድቅ የተደረገን ማመልከቻ መልሶ ማቅረቡ ከሕግ አኳያ ተገቢ አይደለም ሲሉ መከራከሪያ አቀረቡ፡፡ ነገር ግን የፖሊስ ጥያቄ ተቀባይነት በማግኘቱ ተጨማሪ የ28 ቀናት የምርመራ ጊዜ ተፈቅዷል፡፡
በመጨረሻ ከዐሥራ አራት ቀናት በፊት በነበረው ቀጠሮ ችሎቱ ከተጠናቀቀ በኋላ ችሎቱን ለመታደም የመጣውን ሰው ፖሊስ ከግቢው ውጪ አቁሞት ነበር፡፡ ኾኖም ተጠርጣሪዎቹ በመኪና ተጭነው ሲወጡ ከበር ላይም ቢኾን እጁን እያውለበለበ፣ስማቸውን እየጠራና እያጨበጨበ ሸኝቷቸው ነበር፡፡ ዛሬ ግን ይህም አልነበረም ማንም ሰው የውጭው በር ላይ እንኳን እንዲቆም አልተፈቀደለትም፡፡ ሁሉም በሐዘን እንዳቀረቀረ ወደ የመንገዱ ተበታተነ፡፡
ምራቂ ወሬ
‹‹መዝገቡ በጊዜ ቀጠሮ ላይ የሚገኝ ቢኾንም ባለፈው ቀጠሮ ፍርድ ቤቱ የፖሊስን የሽብር ተግባርና የሃያ ስምንት ቀን የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ ውድቅ ስላደረገው ዛሬ መልሶ እሱን ማንሳት አይቻልም ፖሊስ ጥያቄውን እንደገና ማቅረብ ቢፈልግ እንኳን በይግባኝ እንጂ መልሶ በዚህ ችሎት የሚያቀርብበት ሥርዓት አይኖርም፡፡›› በማለት ችሎቱ ከመሰየሙ አስቀድሞ ሞያዊ አስተያየት ሰጥተው የነበሩት የሕግ ባለሞያ ችሎቱ ከተጠናቀቀ በኋላ የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ ሲሰሙ ‹‹የፍርድ ቤቶቹ አሠራር በግልጽ ከሕጉ ጋር እየተጣረሰ ስለኾነ ከዚህ በኋላ የሕግ ባለሞያዎች ትንታኔ ዋጋ የሚያጡበት ጊዜ በጣም እየቀረበም ነው፡፡››ብለዋል፡፡
tsiongir@gmail.com
የበፍቃዱ ኃይሉ እናት በልጆቻቸው ተደግፈው ከዋናው ግቢ ከተባረሩ በኋላ የፍርድ ቤቱ ግቢ ጀርባ ካለው ጤና ጣቢያ በር በኩል ሲወጡ፡፡
Zone 9
ችሎቱን ለመከታተል የመጡት ወጣቶች ከበፍቃዱ ኃይሉ ቤተሰቦች ጋራ እየተላቀሱ በጤና ጣቢያው በር በኩል ሲወጡ ፡፡
Zone9

የሕዳሴ አብዮት! (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ )



የዛሬይቱ ኢትዮጵያችን ‹‹አብዮታዊ ሁኔታ›› ላይ ለመድረሷ በብዙሃን ዜጐች ዕይታም ሆነ፤ ሂደቱን በተከታተሉ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ምሁራን ምልከታ የማይታበል ሐቅ ሊሆን መቃረቡ በዚህ ተጠየቅ ለማነሳው አጀንዳ ገፊ-ምክንያት ነው፡፡ በአናቱም ባለፈው ሳምንት ‹‹የ‹ቀለም› አብዮት ናፍቆት›› በሚለው መጣጥፍ ላይ ለማሳያነት የጠቀስኳቸው ፖለቲካዊ፣ ማሕበራዊ እና ነገረ-ንዋያዊ ችግሮች ተደማምረው፣ ሀገሪቷን በርቀት እንደታዘብናት ሶቪየት ሕብረት፣ አሊያም በቅርበት እንዳስተዋልናት ሶማሊያ በመጪዎቹ ጥቂት ጊዜያት የመፈራረሷን አይቀሬነት ማስረገጣቸውን ልብ እንላለን፡፡ ከዚህ ክፉ የታሪክ ዕጣ ለመታደግም ከሁለት አስርታት በላይ ያስቆጠረውን ይሄን አሮጌ ሥርዓት መቀየር ብቻውን ዘላቂ መፍትሔ ሊያመጣ እንደማይችል ዛሬ ግልፅ እውነታ ሆኗል፤ ምክንያቱ ደግሞ ለዘመናት በገዥነት የተንሰራፋው የፖለቲካ ባሕልም አብሮ ካልታደሰ ነገሩ-ሁሉ ‹‹ታጥቦ ጭቃ…›› ከመሆን አለመዝለሉ ነው፡፡Temesgen Desalegn "Fact" Ethiopian Amharic newspaper editor
እናም ወደዚህ ከፍታ ለመሻገር ሶስተኛው አብዮት ብቸኛ መፍትሔ የመሆኑ ጉዳይ አከራካሪ አይደለም፤ ይህ ታላቅ ንቅናቄ ‹‹የሕዳሴ አብዮት›› በሚል ስያሜ ቢጠቃለል፣ ሂደቱ አንድም ኢህአዴግን ከክፉ ስራዎቹ ከመግታት ባለፈ፣ ኢትዮጵያን በሁለንተናዊ መልኩ የማደስና የተረጋጋ የፖለቲካ ማሕበረሰብ መፍጠርን የመሳሰሉ ተልዕኮዎችን በቀላሉ ወደ መሬት ለማውረድ ያስችላል፤ ሁለትም ከለውጡ ጋር የተያያዙ መሰረታዊ ጥያቄዎችን ከስያሜው አንድምታ አንፃር እየቃኙ በቀላል መንገድ ለመተንተን ጠቀሜታ ይኖረዋል ብዬ አምናለሁ፡፡ አምኜም በአዲስ መስመር የሕዳሴን ታሪካዊ ዳራ፣ አተገባበር እና ተያያዥ ጉዳዮችን እየጠቃቀስኩ ለማብራራት እሞክራለሁ፡፡
‹‹ህዳሴ›› ሲባል…
በ5ኛው ክፍለ ዘመን ከጀርመን የተነሱ ጎዝ፣ ቫንዳልና ቡርጉንዲያኖችን ጨምሮ ሰባት ጎሳዎች፣ በወቅቱ ከፊል አውሮፓን ያስተዳድር የነበረውን ልዕለ-ኃያል የምዕራብ ሮማ ኢምፓየር አንኮታኩተው ግብዓተ-ፍፃሜውን ዕውን አደረጉት፡፡ ይህም የኃያሉ አገዛዝ ፍፃሜ ፕላኔታችን በአዲስ የፖለቲካ ባሕል እንድትዋጅ ሌላ የታሪክ ምዕራፍ ከፈተ፡፡ የዚህ መነሾም አሸናፊዎቹ ጀርመናውያን ጎሳዎች የአስተዳዳሪነት ችሎታም ሆነ ልምዱ ስላልነበራቸው የተፈጠረውን ክፍተት በመጠቀም የሮማ ቤተ-ክርስቲያን እና ፊውዳሎቹ ሥልጣኑን ሙሉ በሙሉ በመቀራመታቸው ነበር፡፡ መላ ግዛቱም ሥልጣኔ-ጠል (Barbarism) እየተባለ የሚጠራውንና እስከ 15ኛው ክፍለ ጊዜ ድረስ በዘለቀው ‹‹የጨለማው ዘመን›› ውስጥ ያልፍ ዘንድ ተገደደ፡፡ ይህን ተከትሎ ትምህርትም ሆነ መንግስታዊው አስተዳደር በኃይማኖታዊ ቀኖና እንዲበየን ተፈረደበት፡፡ በወቅቱ አብያተ-ክርስቲያናት በብዛት ከመታነፃቸው ባለፈ አይን የሚሞላ መሰረታዊ ልማት ባለመዘርጋቱ፣ ከተሞች እጅጉን ቆርቁዘው የገጠሩን ገፅታ እስከመላበስ ደርሰው ነበር፡፡ ከሁሉም የከፋው ደግሞ መመራመር፣ መጠየቅና አለማዊ እውቀትን መፈለግ ከደመ-ቀዝቃዛዎቹ ‹‹መንፈሳዊያን›› አስተዳዳሪዎች ዘንድ ምድራዊ ፍዳን ለመቀበል መዳረጉ ነበር፡፡
በዚህ መልኩ ክፍለ-አህጉሩ ሰባትና ስምንት መቶ የመከራ ዓመታት ካሳለፈ በኋላ፣ የጣሊያኖቹ ፍሎረንስ፣ ቬነስ እና ሮማ ከተሞች ከዘመኑ በተለየ እውቀት ፈላጊና አንሰላሳይ ልጆቻቸው መናጥ ጀመሩ፡፡ ይህንን የመነቃቃት መንፈስ በሥራዎቹ በማካተት የዘመኑ ዝነኛ ባለቅኔ ዳንቴ አሊጋሪ በቀዳሚነት ይታወሳል፡፡ በ15ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ አካባቢ ደግሞ መነቃቃቱ መላ ጣሊያንን በማዳረስ በምርምር ውጤት (በሳይንስ) መቃብር ላይ ተንሰራፍቶ የነበረውን ኃይማኖታዊ አስተዳደር ዳግም እንዳያንሰራራ አድርጎ አፈራረሰው፡፡ ይህ አይነቱ የለውጥ መንፈስ ከጣሊያን ባሻገር ከአልፕስ ተራሮች ጀርባ ባሉ የአውሮፓ ሀገራት ድረስ በመዛመቱም ታሪክ ይቀየር ዘንድ ግድ ሆነ፡፡ ለሁነቱም ዋናው ተዋናይ ሕዝባቸውን ከተዋጠበት የጨለማ ዳዋ ለማላቀቅ ሲሉ የጥንታዊያኑ ግሪክ እና ሮማ የተዘነጉ የአሰላሳዮችን የአእምሮ ውጤት መመርመር ቀዳሚ ስራዎቻቸው ያደረጉት የጊዜው ጠቢባን እንደነበሩ አይዘነጋም፡፡ ታሪክ፣ ፍልስፍና፣ ባህል፣ ስነ-ጽሁፍ፣ ሞራል እና መሰል ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ እውቀቶችን መልሶ በመመርመር ጠቃሜታውን ለይቶ ማሰራጨትን የቀን ተቀን ሥራ ማድረጋቸው የማታ ማታ ለስኬት አብቅቷቸዋል፡፡ እነሆም የታሪክ ምሁራን ‹‹ሕዳሴ›› (Renaissance) ብለው የሚጠሩት ይህንን ሁነት ነው፡፡
በርግጥም ሕዳሴ የታሪክ ሀዲድን ተከትሎ የኋሊት በመመለስ የማንፃት (የመታደስ) ተግባር የሚያከናውን የሳይንስ ዘርፍ ነው፡፡ ይህም ጥንታዊውን ዘመን ዛሬ ላይ እንዳለ ማንበር ሳይሆን፤ የቀደመውን ሥልጣኔ የወደቀበትን ህፀፅ መርምሮ ለዘመኑ የሚበጀውን አንጥሮ በማውጣት፣ ያረበበውን ማሕበራዊ ፍዝነት እና ኋላቀርነት አንገዋሎ በመጣል ላይ የሚያተኩር ፍልስፍና መሆኑ አፅንኦት ሊሰጠው ይገባል፡፡ ምዕራባውያን ለደረሱበት የሥልጣኔ ከፍታ ዋናው መሰረት የተጣለው በሕዳሴው ዘመን ስለመሆኑ ራሳቸው ይመሰክራሉ፡፡ ኮፖርኒከስ፣ ጋሊሊዮ፣ ቦይል፣ ሀአርቬይ፣ አይዛክ ኒውተን፣ ሊዎናርዶ ዳ ቪንቺ፣ ሚካኤል አንጀሎን የመሳሰሉ ጉምቱ ጠቢባን የሥራ ውጤትም አብርሆት (ኢንላይትመንት) የሚባለውን ዘመን ወልዷል፤ ይህም ወደ ኢንዱስትሪ አብዮት አሸጋግሮ ለዛሬው ዘመናዊነት መደላድልን ስለማመቻቸቱ የታሪክ ድርሳናት ያትታሉ፡፡
በወቅቱ የሕዳሴው መንገድ ቀያሽ ተደርጎ የሚጠቀሰው ገዥ-ሃሳብ፣ የሰውን ልጅ በቀዳሚነት በሚያጠናውና ሰዋዊነት (Humanism) ተብሎ በሚጠራው ዘርፍ ላይ የተመሰረተ ሲሆን፤ ይህ አስተሳሰብ በሀገረ-እንግሊዝ በተስፋፋበት በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተነሳው ፀሐፌ-ተውኔት ዊሊያም ሼክስፒር፣ ኃይማኖታዊ ክብረ በዓላትን፣ ስሜት-ተኮር እንቅስቃሴዎችንና ሥነ-ምግባር ላይ ብቻ ያውጠነጥን የነበረውን የድራማ ዘውግ፣ ወደ አለማዊ ይዘትነት በመቀየር ለሀገራዊ ፍቅር መነቃቃት እና የአርበኝነት መንፈስን በማስረፅ ረገድ ወደር የማይገኝለት ሚና ለመጫወቱ ዘመን ተሻጋሪ ስራዎቹ ግንባር ቀደም ምስክሮች ናቸው፡፡ በጥቅሉ የ‹‹ሕዳሴ›› (Renaissance) ፅንሰ-ሀሳብ የግሪክና የላቲን ብሉይ መድብሎች ላይ ቆሞ ፍልስፍናን እና መሰል የእውቀት ዘርፎችን መተርጎምን የያዘ የብርሃን ንቅናቄ በመሆኑ፤ የግለሰብን አለማዊ ከፍታ ለማስረገጥ፤ የሰውን ልጅ ምክንያታዊነት፣ የምርምር ክሂልና የኪነ-ውበት ፈጠራ ማሳደግን ዋነኛ ማዕከሉ ያደረገ ብርቱ የለውጥ መንፈስ ነው ተብሎ ቢደመደም ማጋነን አይሆንም፡፡
የኢትዮጵያ ህዳሴ
በሚሊኒየሙ አከባበር ዋዜማ ይህንን ቃል በጥራዝ ነጠቅነት የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ መጠቀሙን ተከትሎ፣ ከክቡራን ሚንስትሮች እስከ የቀበሌ ካድሬዎች የንግግር መክፈቻና መዝጊያ ሆኖ ዛሬም ድረስ በማጭበርበሪያነት እያገለገለ ይገኛል፡፡ በአባይ ወንዝ ላይ እየተሰራ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫንም «የሕዳሴ ግድብ›› ሲሉ ሰይመውታል፤ ምንም እንኳ የትኛውን ያለፈ ታሪካችንን እንደሚያድስ አፍታተው ባይነግሩንም፡፡ ሰሞኑን የተከበረውን የግንቦት ሃያ በዓል በማስመልከት በቴሌቪዥን መስኮት ቀርቦ በወሬ ደረጃ የሚያውቀውን ገድል እየተደነቃቀፈ የተረከልን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝም ቢሆን ‹‹የግንቦት ሃያ ድል ኢትዮጵያ ወደ ቀድሞ ገናናነቷ እንድትመለስ /እንድትታደስ/ የጠቀመ ነው›› ከሚል መታበይ አልፎ፣ የትኛውን የገናናነት ዘመናችንን ለመመለስ እንደተቻለ ለይቶ አላስቀመጠልንም፡፡ በርግጥ እርሱ እያወራ የነበረው የአክሱም ስልጣኔን በተመለከተ ከሆነ፣ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ታላቁ ስላቅ ተብሎ በታሪክ ማህደር ሊመዘገብ ይገባል፤ በተለይም የአቶ መለስ ዜናዊን ‹‹የአክሱም ሀውልት ለወላይታው ምኑ ነው?!›› ሽርደዳን ስናስታውስ፡፡ በተቀረ ‹‹ሕዳሴ›› ብሎ ለመሰየም በቅድሚያ መታደስ የሚገባው ጥንታዊ ሥልጣኔ ስለመኖሩ ማመን እንደሚጠይቅ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ፕሬዚዳንት ለነበረ ሰው ይጠፋዋል ብዬ አላስብም፡፡
በአናቱም ጀግናው ኢህአዴግ ከምንሊክ በፊት የነበረችዋን ኢትዮጵያ እንደማያውቃት ሲለፍፍ እና የኢትዮጵያ ታሪክን በ100 ዓመት ገድቦ፣ የቀደመው የሥልጣኔ አሻራ የአንድ ወይም የሁለት ቋንቋ ተናጋሪ ማሕበረሰብ ግንጥል ውበት እንደሆነ ለሃያ ሶስት አመት ሙሉ ሲሰብክ ኖሮ፣ ዛሬ ‹የጥንቱን ገናናነት እንመልሳለን› ማለቱ፤ ራሱ ካነበረው የሥርዓት አወቃቀር ጋር ፊት ለፊት እንደሚያላትመው የዘነጋው ይመስለኛል፡፡ ይህም ሆኖ ‹‹ስለሕዳሴ የማወራው ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ አይደለም!›› ካለን ደግሞ፣ የኢትዮጵያን የ3ሺህ ዘመን ቀደምት ታሪክ በይፋ አምኖ መቀበሉን ያወጀ ያህል አድርገን ልንወስደው እንችላለን፤ ግና፣ ይህ አይነቱ አቋም ድንገት በሞቅታ የሚለወጥ ሳይሆን፣ ብዙ ማብራሪያዎችን እና ደም ያፋሰሱ ጠማማ ታሪኮችን የማቃናት ከባድ ሥራ የሚጠይቅ ነው፡፡ በተረፈ የሕዳሴው ልፈፋ በታሪክ ብያኔው ያኮረፉትንና ‹ቅድሚያ ኢትዮጵያዊነት› የሚሉትን ስብስብ በሀሳዊ የፕሮፓጋንዳ ማግኔት ወደፓርቲው ለመጎተት የሚጠቀምበት ተራ የማጭበርበሪያ ስልት ከመሆን የሚዘል አይመስለኝም፡፡
የሆነው ሆኖ በዚህ አውድ መከረኛይቷን ኢትዮጵያ ከአደገኛው ማዕበል የሚታደጋት ቀጣዩ ሕዝባዊ ንቅናቄ ‹‹የሕዳሴ አብዮት›› በሚል ማዕቀፍ ስር ይወድቅ ዘንድ ገፊ-ምክንያቱ፣ የሥርዓት ለውጥ ብቻውን ለሀገሪቱ ትንሳኤ በቂ አለመሆኑን አፅንኦት ለመስጠት ነው፡፡ ስለምን? ቢሉ፣ በተለይም ከ1983ቱ የመንግስት ቅያሬ በኋላ የተከሰቱ አስጨናቂ ችግሮች መፍትሄ ያገኙ ዘንድ ዳግም የመታደስ (እንደገና የመወለድ) አስፈላጊነትን አማራጭ አልባ ምርጫ በማድረጋቸው ነው፡፡ በተለይም የብሔር ፖለቲካው የወለደው የጎሳ ክፍፍል፣ ከባህላዊ እሴቶች ማፈንገጥ፣ የትምህርት ጥራት ማሽቆልቆል፣ የኃይማኖት መቻቻል ወደ ታሪክነት መቀየር፣ የህሊና ታማኝነት መደብዘዝ እና ከሰው ልጅ ይልቅ ቁስ መከበሩ… ከሞላ ጎደል አብዮቱን በታሪክ ማንፃት መካከል የማለፍ ተልዕኮ እንዲያነግብ ገፍቶታል፡፡ በተጨማሪም የቀድሞ የታላቅነት መገለጫችን የሆነው የአክሱም ሥልጣኔ ክቡድ መንፈስ ለዚህ ዘመን መዋጀት የሚበቃ ሽራፊ ምስጢረ-ጥበብን ሸሽጎ ስለመያዙ ከቶም ቢሆን ቅንጣት ታህል የማንጠራጠር መሆናችን ሕዳሴን አጀንዳ እንድናደርገው ያስገድደናል፡፡
ከላይ እንዳየነው የአውሮፓን ሥልጣኔ በፅኑ መሰረት ላይ ያስረገጡት አሰላሳዮቻቸው እንደሆኑ ሁሉ፤ በእኛም አውድ ሀሳቦቻቸውን ወደ አደባባዩ ተዋስኦ አብዝተን ልናካትትላቸውና የሕዳሴያችን ምሁራን ሊሆኑ ይገባል ብዬ የማምንባቸው ሶስት መምህራን አሉ፡፡ መስፍን ወልደማርያም፣ መሳይ ከበደና ተከስተ ነጋሽ፡፡ አዛውንቱ ጠቢብ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በተለይም ‹‹መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ›› በሚለው መጽሐፋቸው፣ የኋላው መዘንጋቱ የችግሮቻችን ምንጭ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው አሳስበዋል፡፡ በገፅ 12 ላይም እንዲህ በማለት በቁጭት ይጠይቃሉ፡-
‹‹ከአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዓመታት በፊት ሰረገላ ነበር፣ የመስኖ እርሻ ነበር፣ የግንብ ቤት ነበር፣ ሕዝብ የሚገበያየው በገንዘብ ነበር፤ ከአራት መቶ ዓመታት በፊት ጋሪ ነበር፣ ድልድይና የግንብ ቤቶች ተሰርተው ነበር፤ የዚህ ሁሉ የሥራ ጥበብ ለምን ከሸፈ? የአክሱም ሀውልቶችን የመስራት ጥበብ ለምን ከሽፎ ቀረ? የላሊበላን ከድንጋይ የተፈለፈሉ አብያተ ክርስቲያናት የመስራት ጥበብ ለምን ከሸፈ? የጎንደርን ቤተ-መንግስቶች የመስራት ጥበብ ምን አክሽፎ አስቀረው? እነዚህ ሁሉ የድንጋይ ስራ ጥበቦች በሚታዩበት አገር በደሳሳ ጎጆ ውስጥ መኖር ከትውልድ ወደትውልድ የሚተላለፍ ባሕል መሆኑ በምን ምክንያት ነው?››
ቀድሞ ግራ-ዘመም የነበሩት የፍልስፍና መምህር ፕ/ር መሳይ ከበደ ደግሞ ሌላኛው የሕዳሴው ምሁር ይሆናሉ ብዬ አስባለሁ፤ በተለይም ከ40ዎቹ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህራን ጋር በተባረሩ ማግስት ባሳተሟቸው መጻሓፍት፣ የቀደሙ ሀገር-በቀል የኢትዮጵያ ሊቃውንትን ሙግቶች በማብራራት ይታወቃሉ፡፡ ‹ወደ ምንጫችን የመመለስን› ጥሪ የሚያስተጋቡት ፕሮፌሰሩ፣ ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ማጥ ለመውጣትም ሆነ ወደፊት እንድትገፋ፣ ለረዥም ዘመን ካስተናገደቻቸው ዕሴቶች መካከል ረብ ያላቸውን መመለስ እንደሚገባት አብዝተው ተከራክረዋል፡፡
አስመራ የተወለዱት የታሪክ አጥኚው ፕ/ር ተከስተ ነጋሽም ሌላው ተጠቃሽ ናቸው፡፡ የትምህርት ስርዓቱ ላይ ባደረጉት አበርክቶ በዚህ አውድ የማነሳቸው እኚህ ምሁር፣ እንደ ፕ/ር መሳይ ሁሉ፣ ዘመናዊው የትምህርት ስርዓት አውሮፓ ተኮር እና ኢትዮጵያ-ጠል በመሆኑ ወደፊት መራመድ እንዳላስቻለን ደጋግመው ከመናገር ባለፈ፤ ቋንቋ የሚሸከመውን ሀገራዊ ማንነት ከመረዳት አኳያ አማርኛን እና ኦሮምኛን የስርዓተ-ትምህርቱ ቋንቋዎች ማድረግ ብቸኛው ከውድቀታችን መውጫ መንገድ መሆኑን ያምናሉ፡፡ …በጥቅሉ እነዚህ አንጋፋ ጠቢባን (ያልጠቀስኳቸው ሌሎችም እንደሚኖሩ ሳልዘነጋ) አውሮፓውያን ከአምስት መቶ ዓመታት በፊት ከጨለማ የወጡበትን ብልሃት መመርመርን ይበልጥ አጠንክረው በመከተል፣ ሀገር የመታደግ ተልዕኮዎቻቸውን ከዳር ያደርሳሉ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ የኢትዮጵያ አምላክ ይሁናቸውና!
መጪው የሕዳሴ አብዮት በዋናነት የሚያተኩርበት ሌላው ጉዳይ፣ ከአራት አስርታት በፊት በያ ትውልድ ፈታኝ የትግል ጉዞ ላይ ትልቅ ተሳትፎ የነበራቸውን እንስቶች የተኳቸው የዛሬዎቹ የፆታ አቻዎቻቸው ለምን ከእንቅልፍ በከበደ አርምሞ ውስጥ ሰጠሙ? የሚለው ነው፡፡ ከአውሮፕላን ጠላፊዋ ማርታ መብራቱና ታደለች ኪዳነማርያም እስከ የመኢሶኗ ወሳኝ መሪ ንግስት አዳነ፤ እንዲሁም ከእልፎቹ የኢህአፓ ትንታግ ጓዲቶች እስከ ወያኔዎቹ አረጋሽ አዳነ እና ቀሺ ገብሩ ያሉ ተዘርዝረው የማያልቁ የዚያ ዘመን የአናብስት እንስቶች እንቅስቃሴ እንደዋዛ አክትሞ፣ በብርቱካን ሚደቅሳ፣ ርዕዮት አለሙና ፈቲያ መሀመድን በመሰሉ ጥቂት ጀግኖች ተገድቦ መታየቱ፣ በቀድሞው ታሪክ መታደስን አማራጭ የለሽ ያደርገዋል፡፡ በርግጥ የእንስቶቻችንን ፊኒክስነት ለመመለስ ከጥንቱ ይልቅ የትላንቱ የእናቶቻችን ጊዜ በተምሳሌነቱ ተስተካካይ የለውም፡፡ እነርሱ በያ ትውልድ ተጋድሎ የጊዜውን ጎታች የፆታ አመለካከት በመጋፋትና የወንዶችን ትምክህታዊ ዓለም በመነቅነቅ ታሪክ ለመስራት የታደሉ ፈርጦች እንደሆኑ አስመስክረዋል፡፡
የእኔ ዘመን አብዮተኛ ሴቶችም፣ በኮታ ሳይሆን በእውነተኛው እኩልነት እንዲገለጡ ግዴታቸውን ከወዲሁ መወጣት ይኖርባቸዋል፡፡ ከወቅታዊው የሀገሪቱ ሕዝብ ቁጥር እኩሌታውን የሚይዙት እንስቶቻችን በነቂስ ያልተሳተፉበት አብዮት በየትኛውም መስፈርት ውጤታማ ይሆናል ተብሎ አይታሰብም፡፡ በግልባጩ እነርሱን በዕኩልነት ማካተቱ ካልተሳካ ለውጡ ሊዘገይም ሆነ ክፉ ጠባሳ ሊኖረው ስለሚችል፣ ‹‹ያለሴቶች ተሳትፎ የኢትዮጵያ ሕዳሴ እውን አይሆንም!›› ከሚለው ዘመነኛ ኢህአዴጋዊ ቧልት እና ፕሮፓጋንዳ በተለየ መልኩ ተግባራዊ የሚሆን የንቃት ሕዳሴ ትኩረት ሊሰጠው ይገባዋል ብዬ አምናለሁ፡፡
ሌላው ጉዳይ ኢትዮጵያ በ66ቱ እና በ83ቱ የአብዮት ሀዲድ ላይ የመጣችበትን የማሕበረ-ፖለቲካ ታሪኳን ግድፈቶችና ስኬቶች በምክንያታዊነት መመርመር ለሁለንተናዊ ዳግም ልደት (ሕዳሴ) እንድንዘጋጅ መደላድል የመፍጠሩ እውነታ ነው፡፡ ይህ የዳግም ልደት አብዮታዊ ጉዞ ደግሞ በዋነኝነት የሁለት ማሕበረሰቦችን ቅሬታ የሚያቅፍ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይኽን የምለው የሌሎቹን ዋጋ በመዘንጋት ሳይሆን፣ በቀዳሚነቱ ስለማምን ነው፡፡
የብሔር ጥያቄ የኢትዮጵያን ማዕከላዊ መንግስት ለመናድ ቅርብ የነበረባቸው ዘመኖችን ተመልክተናል፡፡ በዚህ መንገድ አልፈንም በዋናነት በአግባቡ መመለስ ካቃቱን ጥያቄዎች መካከል በኦሮሚኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች የሚነሳው ዋነኛው መሆኑ አያከራክርም፡፡ ይህ ጥያቄ ጠርዘኛ ልሂቃኑ በሚያቀርቡት ልክ ባይሆንም፤ መሬት የረገጡ ማንነታዊ ቅሬታዎችን ተንተርሶ መነሳቱ ግን መካድ የለበትም፡፡ እናም ኢትዮጵያችንን በማደስ ጉዞ፤ ኦሮሞነት ከሀገሪቱ ምንነት ብያኔ የተነጠለ ሆኖ የመጣበትን የታሪክ አጋጣሚ ሂደት በመግታት፣ የብሔሩን መለዮዎች የኢትዮጵያዊነት ብያኔ ገዢ መተርጎሚያና መዳረሻ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
ሌላኛው ጭብጥ ደግሞ የኢትዮጵያን እስልምና ነባራዊነት ማፅናት ነው፡፡ ኃይማኖቱም ሆነ ተከታዮቹ በአፄያዊዎቹ አፈና ውስጥ ለሺ ዓመታት የመቆየታቸውን እውነታ ተቀብለን፤ በኢትዮጵያዊነት ትእምርታዊ ገፆች ውስጥ ቀዳሚ አዋጭነታቸውን መቀበል የመታደሳችን ግብ ሊሆን ይገባል፡፡
ለነዚህና ለሌሎች መዘርዘር ለማይቻሉን የሀገሪቷ መከራዎች፣ መውጫው ኢትዮጵያን በማደስ የሚደመደም አብዮት ከሆነ ዘንዳ፣ የብሔራዊ ዕርቅ ጉዳይ ከዋነኛ የሽግግር ሂደቶች መካከል ከፊት የሚቆም እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ በእርግጥ ርዕሰ-ጉዳዩ በተነሳ ቁጥር፣ ‹ማን ከማን ጋር ነው የሚታረቀው?› እያለ የሚቀልድ ኢህአዴግ መራሹን መንግስት የመሰለ ቢኖርም፤ እየመጣ ካለው መዓት ሀገሪቷን ለማዳን፣ ብሔራዊ እርቅ ምቹ ድልድያችን መሆኑን ማመን ያስፈልጋል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያን ፖለቲካ በበላይነት የሚዘውሩት ልሂቃንን በአንድ የጋራ መድረክ ላይ ማሰባሰብ፣ በቀጣይ እንድትኖረን በምንሻት ሀገር ምንነት ማዕቀፍ ውስጥ የሚያርፉ ተመጋጋቢ አመለካከቶችን ለመቅረፅ አይነተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡
የሆነው ሆኖ ይህን ተምኔት የመሰለ፣ ነገር ግን ሊከወን የሚችል የሕዳሴ አብዮት ያለእንቅፋት ለማሳለጥ፣ በቅድሚያ ገዥዎቻችን ‹በአንድ ክፉ አጋጣሚ ስልጣኑን ብናጣ ያበቃልናል› ከሚለው ነቢባዊም ሆነ ተጨባጭ ስጋት እንዲላቀቁ ዋስትና መስጠት ላይ መግባባት የግድ ይላል፡፡ በመገዳደል ከተበከለው የግራ-ቀኝ ፖለቲካ ለመንፃት፤ ከነነውረኝነታቸው ሀገሪቷ የእነርሱም እንደሆነች አምነው እንዲቀበሉ ማድረግ ብቸኛው መፍትሔ ነው፡፡ በመጪዋ ኢትዮጵያ አንዱ ልዩ ቀናዒ፣ ሌላኛው ደግሞ ተጠርጣሪ እንደማይሆንባት መተማመን፣ ለሕዳሴው የሚኖረንን ተስፋ ያጎለብታል የሚል ፅኑ እምነት አለኝ፡፡
(የሕዳሴው አብዮትን ማስፈፀሚያ ሃሳብን በተመለከተ ሳምንት እመለስበታለሁ)
Source Ethiomedia

Light at the end of the tunnel for the “Dark Continent”?



(Author’s note: This commentary appeared on  Pambazuka.org  on May 29, 2014 as part of a mid-century outlook on possible scenarios in Africa. I make my “predictions” debating myself as a political scientist and a defense lawyer.)
by Alemayehu G. Mariam

Is there light at the end of the tunnel for the “Dark Continent”?

“Making predictions is hard. Especially about the future”, said the famous American baseball player, Lawrence “Yogi” Berra facetiously. Likewise, predicting whether there is light at the end of the tunnel in 2050 and beyond is hard. Especially about the Dark Continent. Making predictions about Africa based on the facts of the last half century will surely make one a doomsayer. Not looking in the rear view mirror would make one a soothsayer. I am neither.
As a political scientist, I am grudgingly guided by the reputed “founding father” of “modern” political science, Nicolo Machiavelli, who instructed that “Whoever wishes to foresee the future must consult the past; for human events ever resemble those of preceding times.” Machiavelli took a dim view of the human capacity to learn from mistakes. He must have believed man is doomed to incorrigibility.
As a lawyer, I take cue from Jean Paul Sartre who unabashedly declared, “Man is condemned to be free; because once thrown into the world, he is responsible for everything he does.” Sartre was preempted by his intellectual forbearer Jean Jacques Rousseau who proclaimed, “Man is born free, and everywhere he is in chains. Those who think themselves the masters of others are indeed greater slaves than they.” Are Africans condemned to be free and live under the rule of fair and just laws; or are they damned to perpetual slavery in the service of African tyrants who are themselves enslaved by their former colonial and neocolonial masters?Is there light at the end of the tunnel for the “Dark Continent”? (Africa)
In making “predictions” about the future of Africa mid-century, I am guided by two questions: Is Africa’s “future history” determined by its “past history”, or is it yet to be written by free Africans yet unborn? Will the cradle of mankind become the graveyard of freedom and human rights in 2050 and beyond?
I shall use neither a rear view mirror, a crystal ball nor mathematical models to predict Africa’s future. I will leave that to the professional futurists and turbaned seers. I choose to look into Africa’s future as a “political lawyer”, a human rights advocate looking through the opaque prism of justice, freedom, rule of law, equality and other such sublime virtues. The question for me is not whether demographics, economics, sociopolitical change, the environment, and human development factors will shape and determine Africa’s future in 2050 and beyond. These factors are unquestionably decisive. My concern is how the rule of law and good governance in Africa can avert the doomsday scenarios of socioeconomic, political and ecological collapse in Africa.
There is an old Ugandan saying which cautions, “If you don’t know where you’re going, any road will take you there.” Where is Africa going in the next 50 years? Will Africans take Mandela’s long walk to freedom and prosperity as they march to 2050 and beyond, or find themselves caged in a poverty and tyranny trap and self-destruct in an Armageddon of ethnic strife, sectarian warfare, corruption and uncontrolled population growth? Will Africa be the Promised Land for Africans in 2050 and beyond or remain a newer unkinder and un-gentler version of the “beggar continent” that it is today? Will there even be an Africa as we know it today in 2050 and beyond? Is it an exercise in futility to even venture to make predictions about Africa?
The (Machiavellian) political scientist in me whispers prophetic words of doom and gloom in my ears. “Africa emerged from the colonial tyranny of the white man only to be trampled by the tyranny of the black man. Over 50 years of independence, Africa has fallen into a bottomless vortex of dictatorship, corruption, poverty, war, ethnic strife, famine and disease. It will be Apocalypse Africa in 2050. Africa will remain chained in Plato’s Cave where she can see only shadows but never light. It will be the end of times. Africa has no future.”
The defense lawyer in me whispers prophetic words of optimism and exuberance. “Africa’s future is bright as the sun. Tyranny will be swept into the dustbin of history in the inexorable march of freedom across Africa. Dictatorship will inevitably be replaced by genuine multiparty democracy; injustice and inequality vanquished by the rule of law; corruption will evaporate in the sunlight of transparency and accountability; prosperity will grind down poverty; peace will prevail over war; ethnic strife will be overcome by ethnic harmony; famine will be consigned to oblivion by plenty; and ignorance will be banished by enlightenment. The rule of law will replace the rule of evil men. There is bright sunlight at the end of the tunnel. It will be the beginning of times, a new epoch in African history.”
So here are a few audacious “predictions” for Africa in 2050 and beyond as “calculated” by the political scientist and the lawyer.
The Political Scientist: Africa’s principal problem in 2050 and beyond will be famine and starvation, or “food insecurity” as the international poverty pimps conveniently call it. By 2050, Africa’s current population of 1.1 billion is estimated to increase to at least 2.4 billion. Nigeria’s population of 174 million will increase to 440 million. According to the U.S. Bureau of the Census, “Ethiopia, in particular, with an estimated fertility rate of 6.0 children per woman in 2011, is projected to vault from 13th to seventh on the list of most populous countries by 2050, tripling in total population from 91 million to 278 million.” In 2050, Africa will find herself in a “poverty trap”(intergenerational poverty perpetuated by bad governance and economic mismanagement) and a “Malthusian cage” (population growth will outstrip food supply). Africa will be unable to increase food production and will implode from runaway population growth. The “population bomb” will finish off Africa by mid-century.
The Lawyer: An estimated 70 percent of Africa’s population today is under 35 years of age. The youth bulge will likely persist through the middle of the century. Improved education for Africa’s youth and changing youth aspirations and values will reduce the traditional large family size. The younger generation will adopt effective family planning practices and birth control measures and delay child bearing. Africa’s youth will take advantage of innovation and entrepreneurship opportunities. They will take control of the helm of government and practice good governance as part of their value system. Africa will have genuine multiparty democracies with functioning independent judiciaries and legislatures, a free and independent press and civil society institutions and regular free and fair elections. Africa will be the breadbasket for the world with abundant fertile land and water on the continent. Africa’s best days are yet to come!
The Political Scientist: George Ayittey observed, “Africa is poor because she is not free.” In fact, Africa is not poor. Africa is the richest continent in terms of natural resources. Africa is poor because her leadership is morally bankrupt. Africa’s leaders are scraped from the bottom of the barrel. Despite alleged runaway economic growth in Africa (‘seven out of the ten fastest growing economies in the last decade are African’), often trumpeted by the international poverty pimps and indolent Western media parrots, poverty shall persist as an inescapable fact of life for the descendants of the 85 percent of Africans who today live on less that USD1 per day. In 2050, poverty and disease will reduce the average African life expectancy to no more than 37 years. Africa will remain shackled in a poverty and tyranny trap.
The Lawyer: The coming generations of Africans will rescue Africa from the poverty and tyranny trap. They will not be addicted to Western aid. They will forswear the culture of beggary. They will use their knowledge and technological sophistication to solve problems and liberate Africa from the poverty trap. They will take responsibility for their own failures. They will not blame colonialism, imperialism, communism and all of the other ‘isms’ for Africa’s failure. They will stand proud and self-confident. They may not be able to solve all of Africa’s poverty problems but they will surely solve Africa’s bankruptcy of leadership. They will pull up Africa out of its poverty and tyranny trap by its bootstraps.
The Political Scientist: It is written that ‘Where there is no vision, the people perish.’ Africans today are perishing by the millions in South Sudan, the Central African Republic, Mali, Chad, Somalia and elsewhere. Africa is cursed by visionless (benighted and blind) leaders. The Mo Ibrahim Prize for African Leadership, the largest annually awarded prize in the world (USD5 million over 10 years, and a lifetime endowment of USD200,000 per year), has been given out only three times since it was established in 2007. The awardees have come from Mozambique, Botswana and Cape Verde. None of the “new breed of African leaders” sanctified by Bill Clinton and Tony Blair made the cut. The leadership bankruptcy in Africa will economically bankrupt Africa in 2050 and beyond.
The Lawyer: By 2050, Africa’s leaders will be proactive and not as reactive as their forbearers. They will be well-educated and trained (in contrast to the benighted and corrupt ignoramuses who hold the reins of power today). They will plan to avoid problems instead of muddling through problems after the problems have become insoluble. They will be flexible and adopt to new circumstances. They will listen to their young population and act to meet the needs and desires of their generation. They will be open-minded, open to change and resourceful in solving and anticipating problems. Africa’s leaders in 2050 and beyond will be honest, transparent, accountable, self-confident, creative and inspirational. They will be guided by Mandela’s prescription: “It is better to lead from behind and to put others in front, especially when you celebrate victory when nice things occur. You take the front line when there is danger. Then people will appreciate your leadership.”
The Political Scientist: “Africa is a continent of failed states. Africa is a failed continent.” So say many in the Western media. The euphemism of failed and fragile states is used to hide the truth that African states are actually thugtatorships, kleptocracies and corruptocracies. The African state is a glorified criminal racketeering organization for the elites to rip off the national treasury and resources. Nowhere on the planet does one find more corruption, political and economic mismanagement and human rights violations than on the African continent. By 2050, nearly all African states will be failed states or “thugistans” ruled by thugtators. Few African states will be able to deliver the most basic political goods to their citizens. Few African states will have legitimacy in the eyes of their citizens; almost all African states will be held in contempt by their citizens and others.
The African state will be an object of contempt and derision throughout the world. Recently, US Senator John McCain giving advice to President Obama said, “I wouldn’t be waiting for some kind of permission from some guy named Goodluck Jonathan to go into Nigeria to search and rescue some 300 girls abducted by the terrorist group Boko Haram.” Goodluck Johnathan has yet to deploy significant military assets in a mission to search and rescue the girls. The US has sent troops and drones to “help” the Nigerian military rescue the girls since Nigeria cannot do it on her own. Such has been the fate of the “Giant of Africa”. Likewise, when the Central African Republic, Cote d’Ivoire and Mali faced internal strife, they called in their former colonial masters to save them from themselves. By mid-century, Africa will be fragmented into bite size ‘thugistans’ (more than one hundred bite size countries under the rule of thugtators, warring warlords and mercenaries). Africa will be transformed from a continent of failed and fragile states to completely flopped states by mid-century.
The Lawyer: Africa will complete her transition from dictatorship to democracy by mid-century because she is condemned to be free. Much of Africa in 2050 and beyond will be like today’s Botswana (I deplore and condemn the displacement and “resettlement’ of the “San” people (“Bushmen”) by the Botswana government). They will have free and fair multiparty elections. African countries will take the democratic path like Ghana and South Africa, led by the cheetah (young) generation. There will be robust institutions including independent courts, professional civil servants and civil society institutions. The rule of law will be institutionalized and human and property rights respected. Africa’s newer generations will be raised in a culture of openness and tolerance. They will condemn the culture of impunity and corruption that has kept the continent at the tail end of the community of nations.
As Africa’s enlightened youth begin to control the destiny of the continent, they will reject the benighted ways of the preceding generations. By mid-century, Africa will have made up for its democratic deficit by greater and more effective and widespread use of communication technologies. Africa’s youth will join with the worldwide youth community and spearhead unprecedented change throughout Africa. They will have the knowledge, wisdom and technological sophistication to solve Africa’s problems not only with borrowed ideas but also original ideas rooted in African cultures and societies and dreams. Africa’s long, cold and hard winter of tyranny, poverty and discontent will be made glorious by a bright and gleaming African Spring by mid-century.
Looking through a glass darkly at the Dark Continent, it is impossible to see light at the end of the tunnel. The fog of tyranny, corruption and abuse of power that shrouds the continent is impregnable to light. The miasma of uncontrolled population growth, unmanaged urbanization, endemic corruption, cataclysmic income inequality, catastrophic climate change, ceaseless brain drain and cyclical conflict and strife is blinding. Yet, I am certain as the sun will rise tomorrow that there is a bright future for the Dark Continent in 2050 and beyond. I, free from the trappings of profession and occupation, am a die-hard optimist about Africa’s future. It is in my nature; after all, I am a utopian Ethiopian.
There is not light at the end of the tunnel for the Dark Continent. There is a bright African sun!
Professor Alemayehu G. Mariam teaches political science at California State University, San Bernardino and is a practicing defense lawyer.  
Previous commentaries by the author are available at:
Amharic translations of recent commentaries by the author may be found at:

Ethiopians submitted thank you letter to Embassy of Switzerland



by Kebadu Belachew
Mon June 2nd 2014 – Ethiopians in Washington DC delivered letter of appreciation to the Government of Switzerland for allowing Co-pilot Hailemedehin Abera Tegegn to stay in Switzerland considering the suffering and abuse he will be subjected to should he be extradited to Ethiopia where widespread Human Rights violations is taking place by the authoritarian regime of TPLF.
Ethiopians for Switzerland