Thursday, November 14, 2013

በቅድስቲቱ ኢትዮጵያ ልጆች ደም ሳዑዲዎች የነቢያቸውን ምድር አረከሷት (ሰይፉ ኣዳነች ብሻው)

     
NOV 14,2013 1463035_382815998518733_1008202532_n1422537_10201217801468025_236991770_n እና … ቁጣዬን ለመግለፅ ተነስቻለሁ!
“እንደ ሴት ቁጭ ብዬ እሸናለሁ፤ ወንድ አይደለሁም፣ እውነት ሱሪ አልታጠቅሁም” የሚሉ ወንዶች በጣሙን ይገርሙኝ ነበር ድሮ። ንግሥት ሳባን የመሰለች ንግሥት፤ ጣይቱን የመሰሉ እተጌ፤ ሸዋረገድ ገድሌ የመሰሉ ጀግና ዐርበኛ ኢትዮጵያዊያት እንደነበሩን እየታወቀ ወንዱ ከሴቷ እበልጣለሁ ብሎ ሲፎክር ይከፋኝ ነበር። አገራችን ኢትዮጵያ ተከብራ እንድትኖር ጀግኖችን ማፍራት ብቻ ሳይሆን በጀግንነት ለአገራቸው የተዋደቁና ሉዓላዊነቷን ያስከበሩ እንስቶቻችን ዛሬ የዐረብ መጫወቻ ሲሆኑ ቁጭ ብሎ የሚያይ፤ በዶላር አሽከርነታቸውን ለማሳየት መንግሥት የሌላት ሶማሊያ ውስጥ ሠራዊት የሚያሰማሩ የጦር ጄኔራል ግብስብሶች፤ የአገር ሉዓላዊነትና ፍትሕን ለመታደግ ሕግ አርቃቂው የፓርላማው ጥርቅሞች ዜጎቻችን እንደ ውሻ ተቆጥረው በየዐረቡ አደባባይ ሲገደሉ እያዩ ሱሪያቸውን አውልቀው ተቀምጠዋል። ሴት ለክብሯ ቁጭ ብላ ትሸናለች እነሱ ግን በቁማቸው ለቀውት ያታያሉ። በየትኛውም አገር የአገሩን ክብርና የራሱን ነፃነት ለማስጠበቅ የማይቆም መንግሥት የለም። በሳዑዲ በደል በሚፈፀምበት ዜጋችንና በጠቅላይ ሚኒስትሩ መካከል ምንም ልዩነት የለም። ኹለቱም ኢትዮጵያውያን ናቸውና። ሳዑዲ ያለው ኢትዮጵያዊ/ት ሲደፈር/ስትደፈር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተደፋሯል። ምክንያቱም ኢትዮጵያዊነት ተደፍሯልና። “ጌታውን ካልናቁ ውሻውን አይመቱ ወይን አጥር አይነቀንቁ” ይባል የለ። ሳዑዲ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ብታከብር ኖሮ ኢትዮጵያዊውን ለመግደልና ሰንደቅ ዓለማውን ለማዋረድ ባልሞከረች ነበር። ሳዑዲ እንደሆነ ፈረንሣይን የምታክል መሬት ከአገራችን ወስዳ በፔትሮ ዶላር ቀኝ ገዢነት ይሰማታል። የቅኝ አስተሳሰብ ያለው አገር ደግሞ ሌላውን ዜጋ ለርሱ ባርያው አድርጎ ነው የሚያየው። ዶላር ስላላቸው እንጂ እርቧቸው አይደለም? ኢትዮጵያ ድረስ መጥተው ለም መሬት የሚገዙት። ነዳጅ ባይኖራቸው የት ነበር መድረሻቸው?
ሳዑዲ ውስጥ ሰይጣን (ሸይጣን) ገብቷል። የነቢዩ መሐመድን ትምሕርት አርክሰዋል። ቅድስቲቱ ምድራቸውን የግፍ ምድር አድርገዋታል። ነቢዩ መሐመድ አትንኳት ያሏትን ዜጋ ሕይወት እየጨፈጠፉ ናቸው። እስልምና በዓለም ላይ እንዲንሰራፋ ከለላ የሆነችውን አገር ለቁጣ ጋብዛለች። እንዴት መካሪ አጣች?
መቼም ኢትዮጵያ ተምዘግዛጊ መሣሪያ ኖሯት በሳዑዲ ላይ ጦርነት ለመክፈት ገንዘቡም (ለግድብ፣ ለልማት እያለች ከስደተኛ ዜጎቿ ገንዘብ የምትጠይቅና በምዕራባውያን ምፅዋት ያለች በመሆኗ) አሜሪካም ከጎኗ የሏትም። ለፔትሮሏ ስትል አሜሪካ ሳዑዲን መክዳት አትፈልግምና። እኛ ግን ከምድራችን ላይ ንቅል አድርገን በ24 ሰዓት ማባረር እንችላለን። ደርግ እንኳን አሜሪካን መንጥሮ ነበር ያስወጣት። አንድ አገር ሉዓላዊነቱንና የዜጋውን መብት ለማስጠበቅ የትኛውም ኀያል መንግሥት ሊያቆመው አይችልም። ምኒልክን ማስታወስ ነው፤ የአውሮጳን ኀያል ወራሪ ድባቅ የመታውን። ፋሽስትንም ተዋግተው የዕድሜ ባለፀጋ የሆኑ ጥቂት ዐርበኞቻችንን መጎብኘት የጦር መሣሪያ ኀይል የማይበግረው የአገር ወዳድነት ወኔ መሆኑን ከነሱ ለማወቅ ይቻላል። ወኔ የሌላቸው ገዢዎቻችን ግን ሱሪያቸውን አውልቀው ሲያዋርዱን እናያለን። የእነሱ መደፈርና መናቅ ነው ዜጎቻችን ለጥቃት የተጋለጡት። ኢትዮጵያዊነት እንዲረክስ ያደረጉት።
ውሻ እየተባለ ዜጋው ሲረገጥ እያየ በለሆሣሣ የበታችነትን በሚያንፀባርቅ ዲፕሎማሲያዊ አቀራረብ ተቃውሟችንን አሰምተናልን የሚለውን የወያኔ ፕሮፖጋንዳ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚቀበለው አይደለም። ኢትዮጵያውያን አገራችንን መልሰን መረከብ አለብን። መሬታችንን ያስረከቡትንና የተረከቡትን ጠራርጎ ማስወጣት ያስፈልጋል። ሰላማዊ ሠልፍ በውጪ የምንገኘው ቁጣችንን ለዓለም ለማሳየት እንጂ በአገር ውስጥ ከዚህ የጠነከረ መልስ መስጠት አስፈላጊ ነው። ያዋረዱንን ገዚዎቻችን የዐይን ቀለማቸው ጠርቶ ይታወቃል። መሹለኪያ መንገድ እንዳይኖር ዘግቶ ለፍርድ ማቅረብ ያስፈልጋል። በስደት ቢሄድም እንኳን በዘረፈው ገንዘብ ተንደላቅቆ የሚኖርበት ምድር እንዳይኖር ማድረግ ፍትሓዊ ነው።
ገዢዎቻችንና አጋሮቻቸው ኹሉ ለስደት፣ ለሞት፣ ለርሃብ፣ ለጥማት፣ ለውርደትና ከሰብዓዊነት በወጣ መልኩ በአገርም ኾነ በባዕድ አገር የተዋረድክና ነፃነትህን ብቻ ሳይሆን አገርን ያጣህ አድርጎሃል። ቤተሰቤን ልርዳ ብላ ለግርድና ልጅህ ስትሸጥ መልካም ብለህ ተቀመጥክ። ሲደፍሯት መንግሥት እንደማይደርስ እያወቅህ ጥያቄ አላነሳ አልክ። የልጅህ መርዶ ሲመጣ የምትጮኸውን ጩኸት ያኽል አልጮህ አልክ። የትግሉ ሜዳ ሚናው የለየ ነው። ታጋዮችንህ ይገድሉብሃል። ለአገርና ለወገን ደራሽ ለመሆን የሚችል እንደ ሙሉቀን መስፍን ለአንተ አጋር የሆኑትን ታጋዮች እንዲገድል ኤርትራ ከሚልክ ይልቅ ዜጋን ከጥቃት ጠባቂ አድርጎ ሳዑዲ ቢልከው እንዴት ባኮራ ነበር። መንግሥት የሌላትን ሱማሊያ ከመውረርና ያልታጠቀ ሰላማዊ ኢትዮጵያውንን ከመጨፍጨፍ በቀር ወኔ የሌለው ጠላትን ተቀብለህ ትኖራለህ። ቅኝ ለማድረግ የሚመጣን ትኩስ ጠላት አይደለም የምንዋጋው፤ 22 ዓመታት በጭቆና እየገዛ ያለውን ዐምባገነን በመጣል ነፃነትን ለመጎናፀፍ ነው ፍልሚያው። መከራ የመከረህ ወገኔ ምክር አያስፈልግህም፤ የሚያስፈልግህ አንድነት ብቻ ነው። ያለብህ ቆርጠህ መነሳት ነው። ኀይሉ ካንተ ጋር ይሁን! አሜን!!!

Ethiopian woman in Saudi Arabia hangs herself, another badly beaten up (Warning: Graphic photo)

Ethiopian woman has committed suicide by hanging herself in the northern Saudi Arabia province of Tabarjal yesterday. The report says that the police is investigating the circumstances of her death, and has not released her name yet.
                 Ethiopian woman hangs herself in Saudi Arabia
Another Ethiopian woman, who was badly beaten up by her employer, went to get an assistance from the Ethiopian embassy and was turned away. Her friends took this photo and sent it to us. Some Ethiopian women resort to suicide after being subjected to such barbaric acts in the hands of their Saudi employers, and the so called “Ethiopian embassy” refuses to provide them with assistance. The women are trafficked to Saudi Arabia by agencies in Ethiopia that are affiliated with Saudi-Ethiopian billionaire Al Amoudi and his associates, in collaboration with the TPLF junta.
                        Ethiopian woman beaten up in Saudi Arabia

Source:-http://www.ethiopianreview.us/49798

ዳግማዊ ሆሎኮስት በኢትዮጵያውያን ላይ? ከዲያቆን ዓባይነህ ካሤ

ኢትዮጵያውያን ደማቸው የዐረብን አስፋልት አቀለመው፡፡ ባንዲራውን በራሱ ላይ ሸብ ያደረገው የእማማዬ ልጅ የእኔ ጀግና ማንነቱን እየተናገረ በአናቱ ላይ የወረደውን የድንጋዩን ናዳ በሀገሩ ፍቅር ተቋቁሞ በክብር አሸለበ፡፡ ለእርሱ ከዚህ በላይ ሌላ ድል አልነበረምና፡፡ ድንጋዩስ እርሱን አሳርፎታል፡፡ ነፍሱን ይማርልን እንጂ! ባንዲራችን ግን እንደተመታች እንደታመመች ናት፡፡ እውን ይኽ የሆነው በእኛ ላይ ነው?
 
ይህቺ ባንዲራ እኮ ጨርቅ አይደለችም፡፡ ያ በሳኡዲ መሬት ተወግሮ የሞተው ወንድሜ የኮራባት በሞቱ ጊዜ የለበሳት የክብሩ፣ የማንነቱ መገለጫ እንጂ፡፡ ማንም ባይደርስለት ባንዲራው ነበረችለት፡፡ በእርሷ ተጽናና፡፡ ሞተ አልለውም መሰከረ እንጂ፡፡ ባንዲራ ለብሶ መከራን መጋፈጥ የሰማእታት ወግ ነው፡፡
ዳግማዊ ሆሎኮስት በኢትዮጵያውያን ላይ? እንዴት እንዴት? ደግሞ በ ፳፩ኛው ክፍለ ዘመን፡፡ የሰውን ሕይወት የሚያስገብር ምን ጥፋት ተገኝቶ ነው ወይስ የሟርት መስዋእታቸው እኛ ነን፡፡ “ከሕግ አስከባሪው ፖሊስ” እስከ ዱርየው የእኅቶቻችን ክቡር ሰውነት እንደ ውሻ ሲጎተት ከማየት የሚዘገንን አረመኔነት ምን አለ? ይህ እኮ ንቀት ነው፡፡ ይህ እኮ ድፍረት ነው፡፡ ይህ እኮ የሀገርን ሉዐላዊነት መድፈር ነው፡፡
ምንም ዓይነት ወንጀል የሠራ ሰው የሚዳኝበት ሥርዓት አለው፡፡ ስንቶች አእምሯቸውን ስተው ተመለሱ…ዝም አልን፡፡ ስንቶች እንደ ከብት ከግመሎቻቸው እጅግ በተዋረደ ሁኔታ እንደ ሸቀጥ ተጠፍረው ተላኩልን…ያኔም ዝም አልን፡፡ ስንቶች ከፎቅ ራሳቸውን እየወረወሩ ተፈጠፈጡ… አሁንም ዝም አልን፡፡ ዛሬ ደግሞ በዚህ መጡ…ዝም እንዳልን እንቀጥል ይሆን? ስጋቴ ይህ ነው፡፡ አስኪ በማነህ ማነህ የተረፉትን እንድረስላቸው፡፡
 ለመጽሓፋቸው (ኢትዮጵያን አትንኩ ለሚለው) ያልተገዙ በቀላሉ ይተውናል ብሎ ማሰብ ከባድ ነው፡፡ ኢትዮጵያ እኮ ወንዝ እና ተራራዋን ማለት አይደለም፡፡ ከምንም በላይ ሕዝቧ እንጂ…ቀጥሎ ወንዝ እና ተራራዋ ሜዳ እና ሸለቆዋ…ወዘተ ይከተላሉ፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን ለማድረግ ብንተጋ፤
፩. በየቤቱ የተዘጋባቸውን እና በእንግልት ብዛት የሚቃስቱትን ፈልጎ ማግኘት እና አሰቸኳይ እርዳታ ማድረግ፣ መመለሻቸውን ማበጃጀት፣
፪. በየፖሊስ ጣቢያው ወይንም ወኅኒው የታሰሩትን ፈልጎ ማግኘት እና ወደሀገራቸው እንዲመለሱ ከሚመለከታቸው ጋር መነጋገር፣
፫. የተቃውሞ ድምጻችንን በሕጋዊ መንገድ በያለንበት ማሰማት፣
፬. ችግር የደረሰባቸው፣ ሰብአዊ መብቶቻቸው የተጣሱባቸው ወገኖቻችን ከሳኡዲ ሁሉ ካሣ የሚያገኙበትን ማፈላለግ፣
፭. ከተመለሱም በኋላ የሚያገግሙበትን እና መደበኛ ኑሮ የሚገፉበትን ሁኔታዎች ማመቻቸት፡፡
፮. እነዚህን እና ሌሎችንም ጉዳዮች የሚፈጽም ብሔራዊ ኮሚቴ ማቋቋም፡፡
ለዚህ አልተፈጠርንምና፡፡
source: danielkibret.com