Sunday, March 30, 2014

Ethiopian Muslims peaceful protest in pictures (March 28, 2014)


Ethiopian Freedom Icon Andualem Araggie Remembers


On March 28th, 2014 Ethiopians in Washington D.C. area held an event to remember Ethiopian freedom Icon Andualem Araggie, another jailed journalist Eskinder Nega’s wife Serkalem Fasil and the well-known ESAT journalist Sisay Agena was guests in the event.Event Organized by Andinet North America
Eskinder Nega’s wife Serkalem Fasil and the well-known ESAT journalist Sisay Agena
From left Eskinder Nega’s wife Serkalem Fasil and ESAT journalist Sisay Agena

መሪን ልዩ የሚይደርገው በጨለማ ዘመን ከሩቅ ተስፋ አይቶ ማሳየት መቻሉ ነው!


Author and writer Tesfaye Zenebe from Norway
ከተስፋዬ ዘነበ (ኖርዌይ በርገን)
ሕዝባዊ ተቋም ለመመስረት ሕዘባዊ መሆን ያስፈልጋል፡፡ የተቋሙን ሕዘባዊነት ለማረጋግጥ ሕዝባዊ አወቃቀር ሊኖረው ግድ ነው፡፡ የሕዝብን  መሰረታዊ ጥያቄ ሊፈታ የሚችል ትልቅና ሁሉን አቀፍ አጀንዳ ወይም መርሃ-ግበር ሊኖሩት ይገባል፡፡
ተቋማት በተለይም የፖለቲካ ሕዝብን ማእከል አድርገው ካሉት ወይም በስልጣን ላይ ካለው የተሻለ እቅድና መርሃ-ግብር ነድፈው ሕዝብን ለለውጥ ማንቃት ሲችሉ እንዲሁም በሃገርና በሕዝብ ላይ የሚደርሱ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኤኮኖሚያዊ እንዲሁም አስተዳደራዊ ችግሮች በመንቀስ የተሻለ አማራጭ ማቅረብ የሚችሉና የትኛውንም የህብረተሰብ ክፍል መድረስ የሚችሉ መሆን ይጥበቅባቸዋል፡፡
በሃገራችን ውስጥ ባለው የይስሙላ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት በዘመነ ሕወሃት የተቋቋሙት ለቁጥር  የሚታከቱ የብሔርም ሆነ የሕብረብሔር የፖለቲካ ድርጅቶች የረባ የስማቸውን ያህል ትጋት ሳይታይባቸው ሲያሻቸው በቡድን አለያም በተናጠል መግባባት አቅቷቸው የእመቧይ ካብ እየሆኑ ሕዝብን ሲያቆስሉ ሁለት አስርተ አመታት ተቆጥረዋል፡፡
አምባገነኑን ስርዓት ለማስገደድ በእቢተኝነት ከእስከ አሁኑ የተሻለ የሰላማዊ ትግል ተግባራትን ያከናወኑ የአዲሱ ትውልድ አዳዲስ ታጋዮች ትግልን እንደ ተቀላቀሉት ሁሉ ከፓርቲ ፓረቲ እየተከለሱ እየወጡና እየወረዱ ይህ ነው የሚባል ለውጥ ሳያመጡ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን እርስት ያድረጉ አመራሮች ከአመት አመት መታየታቸው በትግሉ ላይ አሉታዊ ተፅኖ ማሳደሩ አይቀርም፡፡
ከዘረኛው የህውሃት ቡደን መሰሪ ተፈጥሮአዊ ባህሪ አንፃር በተናጠል ከሚደረግ ትግል ይልቅ በተደራጀ መልኩ ተቀራራቢ የፖለቲካ ፕሮግራም(መርሃ-ግብር) አላቸው ድርጅቶች ግንባር ፈጥረው እንዲታገሉና እንዲያታግሉ ከአንድነትና ከአብሮነት ጠላት  ከሆነው ወያኔ በስተቀር የሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጲያዊ ፍልጎት መሆኑ እሙን ነው፡፡ ይሁንና በድርጅቶች በኩል ተራ ልዩነቶችን እየፈጠሩ ለውህደት መዘጋጀታቸውን ነግረውን ሳይጨርሱ ስለ መለያየታቸው በየፊናቸው ውሃ የማየቋጥር ምክንያት ሲደረድሩ መስማት ሕዝብ በድርጅቶቹ ላይ ያለውን አመኔታ አጠያያቂ ያደርገዋል፡፡ እዚህ ላይ ማስተዋል የሚገባን በተቃዋሚው ጎራ በሚፈጠር ልዩነት ተጠቃሚው የሃገርና የሕዝብ ብቸኛ ጠላት የሆነው ዘረኛው የወያኔ ጉጅሌ ቡድን ነው፡፡ ለስርዓቱ እስኪከረፋ በሕዝብ ጫንቃ ላይ ለመንሰራፋት አሰተዋጾ ያደረጉት የሕዝብን ሃይል አስተባብረው በአንድነት ታግለው ማታገል ያልቻሉት ግለኛ የድርጅት መሪዎች መሆናቸው መዘንጋት የለበትም፡፡
ሕዝብና ሃገር በዘረኛው የህውሃት መዳፍ ከወደቀ ጀምሮ ይህ  ነው የማይባል ግፍና በደል አሳልፏል እያሳለፈም ነው፡፡ በዚህ ግዜ ውስጥ የሕዝብ ጥያቄ ይዘው የተነሱ ቁርጠኛ የሕዝብ ልጆችን የኸው አመባገነን ዘረኛ ቡድን እንደ ኢሎሰ ቢንጥቀንም የነሱን እራእይ ለማሰቀጥል መሰራት ያለበትን ያህል ለመሰራቱ እርግጠኛ መሆን አይቻልም፡፡ በአንፃሩ የጎላ እስቅስቃሴ ያደርጋሉ በስርዓቱም ላይ ተጽእኖ የፈጥራሉ የሚባሉት ድርጅቶች አንድም በስርዓቱ እኩይ ሴራ ሲፍተኑ አልያም በራሳቸው የውስጥ ችግር ከሃገርና ከሕዝብ ጥቅም ይልቅ በግለሰቦች ፍላጎት እይተዘወሩ የጋራ ጠላት የሆነውን ዘረኛውን ስርዓት ትተው እርሰ በእርሳቸው ሲላተሙ ማየትና መስማት የተልመደ ተግባር ሆኗል፡፡
ሕዝብ ድርሻውን በባለ ግዜዎች ተቀምቶ በርሃብና በእርዛት እንዲሁም የእንሰሳ ያህል ክብር ተነፍጎ ኢሰብአዊ ድርጊት እየተፈጸመበት እያለ፣ ሃገር በህውሃት ዘረኛ ቡድን ተበልታ በየአቅጣጫው ለባእዳን እጅ መንሻ በማትመተርበት በዚህ ወቅት ከመቼውም ግዜ በላይ አንድነታችንን አጠናክረን ልዩነታችንን አቻችለን ተከበራ የኖረች ሃገርን አስከብሮ ማቆየት ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም፡፡ በሰላማዊ ትግሉ ለውጥ መጣም አልመጣ ሕዝብ አደራጀቶና አንቅቶ ሃገር ለምትፈልገው ማንኛውም ጥሪ ማዘጋጀት አለን ከሚሉ ድርጅቶችና የድርጅት አመራሮች የሚጠበቅ ነው፡፡
መሪን ልዩ የሚያደርገው ሃገራችን እንዳለችበት ውስብስብ ጨለማ ዘመን ላይ ከሩቅ ተስፋን አሻግሮ አይቶ ማሳየት መቻሉ ነው፡፡ ሃገራችን አሁን ካለችበት ውስብስብ ጨለማ ዘመን የሚያስፈልጋት አሰተዋይና ጠንካራ ከራሱ ዝናና ክብር ይልቅ የሃገርና የሕዝብ ዘንን ክብር የሚያስቀድም መሪ ነው፡፡ አሁን ባለንበት አስቸጋሪ ወቅት ይህንን ክህሎት ተላበሰናል የምትሉ ሃገራችውን አስቀድሙ ሞክራችሁ ያልትሳካላችሁ ሳያስነውራችው አቅምና ብስለት ላለው አሳለፋችሁ ስጡ ሃገርና ሕዝብ መውደድ ማለት በእውር ድንብር ያለ ለውጥ መዳከር ሳይሆን ከራስ በላይ ለሃገርና ለሕዝብ ማሰብ ነው፡፡
ኢትዮጲያ በክብር ለዘላልም ትኑር!

ሥጋታችን “አክራሪ” ሃይማኖተኝነት ሳይሆን አክራሪ “አይማኖተኝነት” ነው


Adebabay blog
ይህንን ጽሑፍ ለመጀመር ትርጓሜ የሚያስፈልጋቸውን ሐሳቦች ብያኔ በመስጠት እነሣለኹ። ሃይማኖት እናአይማኖት። በጥሬ ትርጉሙ ከወሰድነው ሃይማኖት “አሚን፣ ማመን፣ እምነት፣ አምልኮ” ማለት እንደሆነ የግእዝ እና የአማርኛ ቀዳማውያት መዝገበ ቃላት ደራስያን ደስታ ተ/ወልድ እና ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ይነግሩናል። ከዚያም አልፎ በዕለት ተዕለት ቋንቋችንና አነጋገራችን ካየነው ደግሞ እያንዳንዳችን የምንከተለውን እምነት እና ሃይማኖት በየስሙ እየጠራን “እገሌ የተሰኘው ሃይማኖት ተከታይ ነን” እንላለን።For Ethiopian muslims and chrstians
“አይ” ደግሞ “የአሉታና የነቀፌታ ቃል ንኡስ አገባብ ሲኾን በቦታ፣ በኀላፊ፣ በትንቢት፣ ይገባል። ለምሳሌ “አይ ወዲያ፤ አይ በሉ” እንደሚባለው ነቀፌታን የሚያሳይ አገባብ ነው። “አይባልም፣ አይገባም፣አይደለም፣ አይኾንም” የምንለውን ማስታወስ ነው።
ያዲሳባ ሰው አይጦም አይበላ፤
አያርፍ አይሠራ”
 እንዲሉ አለቃ ደስታ ተ/ወልድ።
ከ“ሃይማኖት” አሉታን የሚያሳይ “አይማኖት” የሚል ቃል መፍጠሬን ይመለከቷል። ሃይማኖተኛ እንደሚለው እምነት አልባ፣ እግዜር የለሽ (Atheist) መሆን ብቻ ሳይሆን ለሃይማኖት ጥላቻ ያለውን ሰው “አይማኖተኛ” (Antitheist) ብንል ያስኬደናል። ቃሉ ለምን እንዳስፈለገን ወደ ጽሑፉ ገባ ስንል እንገነዘባለን። በፈጣሪ መኖር የማያምኑ (Atheist የሆኑ) ብዙ ሰዎች አሉ። ግን ሃይማኖትና አማኒውን ላይጠሉ ይችላሉ። ሃይማኖትን እና አማኙን ለሚጠሉ ግን አይማኖተኛ (አንቲቴይስት Antitheist) የሚለው ይህ ቅጽል ገላጭ ይሆናል። እናብዛው ካልን “አይማኖተኛ፣ አይማኖተኝነት” ልንለው እንችላለን።
++++
ሃይማኖት ሥር እንደ ሰደደባቸው እንደማንኛቸውም አገሮች ሁሉ ኢትዮጵያም ስለ ሃይማኖት፣ ሃይማኖት በሕብረተሰቡ የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይ ስላለውና ሊኖረው ስለሚገባው ድርሻ እና ከፖለቲካ ጋር ስላለው ግንኙነት ሰፊ ውይይት ይደረግበታል። ውይይቱ አዲስ የተጀመረ ባይሆንም በዚህ ዘመን ያለው የጉዳዩ አያያዝ ከሌሎቹ ዘመናት በተለየ ሰፋና ጠለቀ ያለ ትርጉም እየተሰጠው ነው።
አገራችን አዲስ መንግሥት እና አዲስ ሕገ መንግሥት ከተመሠረተባት ካለፈው 20 ዓመት ወዲህ በአገሪቱ ስላሉት እምነቶች፣ ከፖለቲካው ጋር ስላላቸውና ሊኖራቸው ስለሚገባው ግንኙነት ሰፊ መንግሥታዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው። ይኸው መንግሥታዊ እንቅስቃሴ በሁሉም ዘንድ ያለው መረዳት አንድ ዓይነት ነው ማለት አይቻልም።
በሕገ መንግሥቱ ላይ መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው፤ መንግሥታዊ ሃይማኖት አይኖርም፤ መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፤ ሃይማኖትም በመንግሥት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም” ይላል። (ሕገ መንግሥት አንቀጽ 11)።
አንዱ በአንዱ ተግባር ውስጥ “ጣልቃ አለመግባት” ማለት ምን ማለት ለመሆኑ በራሱ መፍታታት ይኖርበታል። መንግሥት በሃይማኖት ላይ የተመሠረተ፣ አንድን እምነት የመንግሥት እምነት አድርጎ የሚቀበል አይሆንም፤ ሃይማኖትም በራሱ ተነሳሽነት “ሃይማኖታዊ መንግሥት ለመመስረት አይንቀሳቀስም”። በሳዑዲ አረቢያ ወይም በሌሎች የእስልምና አገሮች “የአገሪቱ ብሄራዊ እምነት እስልምና” ሆኖ እንደታወጀው በኢትዮጵያም “ብሔራዊ እምነት የሚባል” አይኖርም ብለን እንውሰድ። በተጨማሪም እምነቶች እንደ ፖለቲካ ፓርቲዎች የራሳቸውን መንግሥት ለማቋቋም አይሞክሩም። በእምነት ስም ለፖለቲካ ማራመጃነት ማንኛውንም ፓርቲ (ሃይማኖታዊ ፓርቲ) ማቋቋም  አይፈቀድም።
ሕገ መንግሥቱ “የሃይማኖት፣ እምነትና አመለካከት ነጻነት” ባለው ክፍል ውስጥ ደግሞ ተጨማሪ እምነት ነክ መብቶች ዘርዝሯል (አንቀጽ 27)። ሲጠቃለል፦ መንግሥት በዜጎች እምነት ነክ ጉዳይ ጥልቃ የማይገባ፣ ከሃይማኖት የራቀ፣ “ሴኩላር” መሆኑን ያስረግጣል።
የመንግሥት ሴኩላርነት፣ ሃይማኖትን እና መንግሥትን የመለየት ፍልስፍና ከራሳችን ያነቃነው ሳይሆን ከሌሎቹ አገራት የቀዳነው እንደመሆኑ ፍልስፍናው እና አስተምህሮው በሌሎቹም ዘንድ ለረዥም ጊዜ ሲሰለቅ የኖረ ነው። አልፍሬድ ስቴፓን የተባሉ ፀሐፊ ዲሞክራሲ በፖለቲካ፣ በመንግሥታትና በሃይማኖቶች መካከል ስላለው ግንኙነት ሲናገሩ በአራት ከፍለው ያስቀምጣሉ።
1ኛ. ሴኩላር የሆነ ይሁን እንጂ ለሃይማኖት ጥላቻ የሌለው መንግሥት አለ፤
2ኛ. ሴኩላር ያልሆነ (እምነት ነክ የሆነ) ይሁን እንጂ ለዲሞክራሲ ጥላቻ የሌለው መንግሥት አለ፤
3ኛ. ሴኩላሪዝም ያቆጠቆጠበት እና ሃይማኖት ምንም ተጽዕኖ የሌለበት ፖለቲካ አለ፤
4ኛ. ሴኩላር የሆነ ነገር ግን ለሃይማኖት ጥላቻ ያለውና በሃይማኖቶች እና በመንግሥት መካከል ጤናማ ያልሆነ ግንኙነት እንዲመሠረት የሚያደርግ አስተዳደርና ፖለቲካ አለ። (RAY TARAS. “POLAND’S TRANSITION TO A DEMOCRATIC REPUBLIC: The Taming of the Sacred?”. THE SECULAR and THE SACRED NATION, RELIGION AND POLITICS. (2005: p. 143)።
+++
ፈረንሳይ “ሴኩላር” የመንግሥት አስተዳደር የምትከተል ብትሆንምና ባለ ብዙ እምነት አገር ብትሆንም ለብዙ ዘመናት በአገሪቱ የቆየውን የካቶሊክ እምነት እና ባህል ግን ከአገሪቱ ማንነት ላይ ቀርፋ መጣል አትችልም። የሌሎችን እምነቶች ባህል ለማክበር የፈረንሳይ-ካቶሊክ እምነትና ባህል መጥፋት የለበትም። በታሪክ አጋጣሚ ካቶሊካዊነት ያገኘው ሥፍራ አሁን ባለው የእምነት-እኩልነት ምክንያት ሊኮስስ አይችልም።
ብዙ እምነት ካላቸው እና “ሴኩላር” አስተዳደር እንከተላለን ከሚሉት መካከል ሕንድን በተጨማሪ ብናነሣ አገሪቱ የተለያዩ እምነቶች አገር ብትሆንም ሁሉንም አስማምታ በአንድነት ማኖር የቻለችው ግን ገና ከ50 ዓመት ወዲህ ነው። ፓኪስታንን እና ሕንድና ያለያያቸው የርስበርስ ጦርነት የተደረገውና አንዷ ሀገር ሁለት ለመሆን የበቃችው በእምነት ልዩነት መስመር ነው። ፓኪስታን እስልምናን፣ ሕንድ ደግሞ ሒንዱ እምነትን በዋናነት በመያዝ። ሒንዱ ዋነኛው እምነት ቢሆንም አሁን ሕንድ ባላት ለእምነቶች ሁሉ እኩል ዕይታ ምክንያት ባለ ብዙ እምነት አገር ተብላ ትወሰዳለች። ሕገ መንግሥታቸውም ይህንን ያሳያል።
ሕንድ ሌሎች እምነቶችን ትቀበላለች ማለት የሒንዱ እምነት በአገሪቱ ላይ የነበረውን የቆየ አሻራ ታራክሳለች ማለት አይደለም። የአገሪቱ ባህላዊ ማንነት በሒንዱነት ቢበየን የታሪክ አጋጣሚ መሆኑ እሙን ነው። የቆየ እምነት ነውና ታሪካዊ ድርሻው ከፍ ማለቱ የማይጠረጠር ነው። ማንኛውም ሕንዳዊ የፈቀደውን እምነት መከተል ይችላል። ሁሉም እምነት ግን በሕንድ ታሪክ ላይ እኩል ድርሻ የለውም።
ከስፔን እስከ ቱርክ፣ ከፖላንድ እስከ አሜሪካ፣ ሃይማኖት ትልቅ ሥፍራ በሚይዝባቸው ነገር ግን መንግሥታቱ “ሴኩላር” ናቸው በሚባሉባቸው አገሮች በመንግሥታት እና በሃይማኖቶች መካከል እኩያነት፣ መከባበር፣ መተጋገስ እና ሕጋዊነት አለ። መጠናቸው ግን አንዱ ከአንዱ ይለያል።
+++
ባለፉት አርባ ዓመታት በአገራችን ያለው የፖለቲካ እና የሃይማኖት ግንኙነት ብንመለከት “ሴኩላር” መሆኑንሁለቱም መንግሥ ቢገልጹም “ምን ዓይነት ሴኩላር መንግሥት?” የሚለውን ግን የምንገነዘበው ከድርጊታቸውና ከተግባራቸው ብቻ ነው። አልፍሬድ ስቴፓን  ሐሳቦች መነሻነት ከተመለከትናቸውመንግሥቶቻችን ሴኩላር ብቻ ሳይሆኑ ለሃይማኖት በጎ አመለካከት በሌለው ሴኩላር አስተሳሰብ ላይ የተገነባ ፍልስፍና  የሚከተሉ “አይማኖተኞች” መሆናቸውን መረዳት እንችላለን።
ይህ 40 ዓመት በትክክል ያሳየን አንድ ሐቅ ደግሞ አገራችንን ያጠፋው ይኸው አይማኖታዊ አመለካከት እንጂ ሃይማኖት አለመሆኑን ነው። በቀይ እና ነጭ ሽብር፣ በግራና በቀኝ አስተሳሰብ፣ በቋንቋና በዘር ፖለቲካ ወዘተ ተቆራቁሰን አገራችንን ከማጥፋታችን በስተቀር በሃይማኖት ሰበብ ድሆችና ኋላቀሮች አልሆንም። የእርበርስ ጦርነቶች ሕዝባችንን ያጎሳቆሉት ለአገራችን ችግር ዋነኛ ምክንያት ተደርጋ በምትፈረጀው በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰበብ አይደለም።
መንግሥት ሴኩላር መሆኑ ተገቢ ሊሆን ይችላል። ሃይማኖትን “ሴኩላር” ማድረግ ግን አይማኖተኝነትን በሃይማኖት ላይ መጫን ነው። ሰዎች በምርጫቸው እምነት አልባ መሆን መብታቸው ነው። በግድ እምነታቸውን ማስጣል እና ሃይማኖት ያላቸውን ሰዎች በጎ ባልሆነ አመለካከት መመዘን አይማኖተኝነት ነው። አክራሪነትን እቃወማለሁ። አይማኖታዊ አክራሪነትን ደግሞ የበለጠ እቃወማለሁ። አገራችንን ሲያጠፋ በደንብ አይቼዋለሁና። በተግባር የተገለጸ ሥጋታችን “አክራሪ ኦርቶዶክስ” ሃይማኖተኝነት ሳይሆን አክራሪ “አይማኖተኝነት” ነው።

ይቆየን – ያቆየን

ይህ ጽሑፍ አዲስ አበባ ለሚታተመው የአዲስ ጉዳይ መጽሔት የተጻፈና በዚያም ላይ ለሕትመት የበቃ ነው።

የጥላቻው እሳት ቆስቋሹን ያቃጥለው


ዳኛቸው ቢያድግልኝ
የትግል መሰረቱን ጎጥ ላይ ያደረገ፣ የእድገት ልኩን ዘረፋ ላይ ያዋለና የእውቀት ጥጉን ውሸት ላይ የመሰረተ እንዴትም ሆኖ የነጻነት ታጋይ አይሆንም። ይልቁንም በሕዝብ ጫንቃ ላይ ተንፈራጥጦ እንዲኖር የክፋት መርዙን ይረጫል እንጂ። ምንም በሁኔታዎች አስገዳጅነት ቢተጣጠፍ እንኳ ኢትዮጵያዊነትን ከፍ የማድረግ አቅም ስለሌለው ሕብረት ያስፈራዋል፣ ነጻነት ያጥወለውለዋል፣ አንድነትም ያስበረግገዋል። ኢትዮጵያ ለወያኔ ትርፍ እስካስገኘች ድረስ እንደምትታለብ ላም ነች። ከዚያ በላይ ወያኔዎች ሀገራዊ ራዕይ የሚባል ነገር የላቸውም።Tigray people liberation front, tplf
እንደ ሀገርና እንደ ሕዝብ ያለብንን ፈተና በጎጥ መነጽር አይተን በጥላቻ ክርክር ተጯጩኸን በግል ስምና ዝና ጦዘን ልንወጣው ፈጽሞ አይቻለንም። በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እለት በእለት የምንመለከተው ሁነት እያሳየን ያለው ተፋቅረንና  ተደጋገፈን መኖር የሚገባን ወገኖች ተናንቀን ስንነካከስ ነው። ጃስ እያሉ የሚያናክሱን ደግሞ እንግሊዝ በቀበረው የእርስ በእርስ መተላለቂያ ፈንጂ፣ ጣልያን በቀመመው የጎሳ ክልል መርዝና በየሃገሩ እሳት ጭረው በሚወጡት ለጥቅማቸው ሲሉ ምንም ከማድረግ በማይመለሱ ሀያላን እገዛ እየተጠቀሙ ወደ ጥፋት የሚነዱን ደናቁርቶች ናቸው። ሰሞኑን በወያኔዎችና ለወያኔ የጥላቻና ፕሮፖጋንዳ ሰለባ በሆኑ ቡድኖች ወገኖቻችንን በዘር ለማናከስ እንደ አበደ ውሻ የሚክለፈለፉ በዝተዋል። የሰከነ የአንድነት ድምጽ እንዳይደመጥ ወያኔ ከፍተኛ አፈና በሚያደርግባት ኢትዮጵያ ጎልቶ የሚደመጠው የደንቆሮ ጩኸት ነውና አማራጭ ድምጽ እንዲደመጥ ካላደርግን ህዝባችን ሊወናበድ ይችላል።
በከሃዲና ስግብግብ የአፍሪካ መሪ ተብዬዎች ውክልና የሀገርና አህጉር ሀብትና ቅርስ በንግድ ሽፋን ዘረፋ ላይ ለተሰማሩ ሀገር በቀልና የወጪ ከበርቴዎች እየተቸረ ነው። በዘመናዊ ትምህርት ስም የሀገር ፍቅርንና ለህዝብ የመቆም አስፈላጊነት ችላ እንድንል የተበረታታን ተልፈሰፈስንና የማንነት መሰረታችን ተናግቶብን ብዙ ዘመነኞች እኛንና ህዝባችንን ለብልቦ የሚፈጀንን የጥፋት እሳት እንደ ደመራ እያጨበጨብን ከበን እያየነው እንገኛለን።  ኢትዮጵያ በታሪክዋ አይታ የማታውቀው በሌላውም አለም ያልተለመደ አይነት አሳፋሪ የሀገር ጠላት የሆነ የዱርዬ ስብስብ መንግስት ነኝ እያለ አገሪቱን ለእቁብ ወይንም ለቤት ኪራይ ገንዘብ እንዳጠረው ነጋዴ ሃገራችንን በርካሽ ዋጋ እየቸበቸበ ይገኛል።
በሀገር ልማት ስም ከየአቅጣጫው የሚሰበሰበው የብድር መአት በኛ ዘመን ቀርቶ በልጅ ልጆቻችን ጊዜም ተከፍሎ አያልቅም። የተበደሩት ገንዘብ ግን ግማሹ ወደ መጣበት ሀገር ተመልሶ በሌቦቹ ባለስልጣናት ስም በተከፈቱ የባንክ ሂሳቦች ገቢ ተደርጎ የጨረቃ ሚሊየነሮችን መፍጠሪያ ሆኗል። ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ መሰረትዋና አብዛኛው ህዝቡዋ የሚተዳደርበት ሁኖ ሳለ የእርሻ መሬቶች ለውጪ መንግስታትና ግለሰቦች እየተቸበቸቡ ነው። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያውያንን ዛሬ መሬት አልባ ነገ ደግሞ አገር አልባ  ያደርጋቸዋል።
የዛሬዎቹ መሪ ተብዬዎች መሬትን መያዝ ሀገርን መቆጣጠር ነው ብለውም ነው መሬት የመንግስት ነው የሚሉት። አዎን ዛሬ መሬት የትግራይ ማፊያዎች ሀብት ነው። ያሻቸውን ለማድረግ የያዙት ታንክና ላውንቸር መብት አጎናጽፎአቸዋል። የተቀረው ኢትዮጵያዊ መሬትም መብትም የለውም! ሌላ ቀርቶ ነገና ከነገወዲያ ጤፍ፣ ስንዴና ገብስም የትላልቅ ‘ምርጥ ዘር’ አምራቾች ሸቀጥ እንጂ ለዘመናት መሬቱንና የሰብሉን ዘር ሲንከባከብ የኖረው ገበሬው ሀብት አይሆኑም። ገበሬው የዘርና ማዳበርያ ዋጋ መክፈል እያቃተው መሬቱን ጥሎ ለማኝና ስደተኛ እንዲሆን እያደረጉት ነው። ይህን አደገኛ አኪያሄድ አሁን ካልገደብነው ኢትዮጵያ የምትባል አገር መኖሩዋ አጠራጣሪ ይሆናል። ይህም ባይሆን እንኩዋን ህዝባችን በገዛ ሀገሩ ለጥቂት የውጭና የውስጥ ዘራፊ ባለሃብቶች ጪሰኛ ይሆናል። ወያኔዎች ያለመታከት ለዚህ መከራ እያሰናዱን ነው እኛም ዛሬ ለነሱ ደባ ተመቻችተንላቸው ለዘመናት በጎሳ በቁዋንቁዋም ይሁን በሀይማኖት ሳንለያይ አብረን መኖራችንን ችላ በማለት በጎጥ አንሰን  በመንደርም እየተከፋፈልን  አገርም ማንነትም ለሚያሳጡን አረመኔዎች በራችንን በርግደን እንዲያምሱን ልንፈቅድ አይገባም።
ዛሬ በራሱና በወገኖቹ ላይ በሚደርሰው ሰቆቃ በማዘን “ራሴን ጠላሁ” “በኢትዮጵያዊነቴ አፈርኩ” የሚለው የተቆጣ ሕዝብ ብዙ ነው። ይህን ቁጣውንና ዱላውን ለሰቆቃው ምንጭ በሆነው ወያኔ ላይ እንዳያሳርፍ እነ ስብሃትና በረከት ስምኦን ጸቡን በአማራና ኦሮሞ፣ በክርስትያንና ሙስሊም ወ.ዘ.ተ. መካከል ለማስቀረትና ለኛው የእልቂት ድግስ መደገስ ከጀመሩ ብዙ ቆዩ። ያለመንግስትና ያለፖሊስ ተከባብሮ የመኖር ድንቅ ባህልን ያዳበረውን ሕዝብ ዛሬ አናቁረውት ሌብነት ቅጥፈትና ዘረፋ የብልጥ መንገድ እንደሆነ እየሰበኩ ወደ ንቅዘት የሚመሩት እነዚሁ የወያኔ ወሮበሎች ናቸው። የማይሞላ ከርስና ባዶ ጭንቅላት ያላቸው የየብሄረሰቡ ተወካይ ተብዬዎች ደግሞ አንደ ተወጠረ ከበሮ አለቆቻቸው ትንሽ ኮርኮም ወይም ኮርኮር  ሲያደርጉዋቸው ይጮሀሉ። በጎሳና ሀይማኖት ህዝባችን አይነጣጠልም  ያልነው እውነት እንዲሆን እርስ በራሳችን እንዳንፋጅ ሁላችንም የወያኔን የጥላቻ ቅስቀሳ ልማክሰም የድርሻችንን የምናደርግበት  ጊዜ ዛሬ ነው። ይሄ አያገባኝም ወይም አይደርስብኝም ማለት ከሌሎች ተሞክሮ አለመማር  ይሆናል።
ሩዋንዳውያን አንድ ሚሊየን ያህል ወገኖቻቸው በግፍ ከተፈጁ በሁዋላ በህልማችንም በእውናችንም ጉዋደኛ ለጉዋደኛ ጎረቤት ለጎረቤት እየተራረድን እንዲህ ያለ ክፋት እኛው በኛው ላይ እንፈጸማለን ብለን አናስብም ነበር ሲሉ መስማት የተለመደ ነው። ከበርካታ አመታት በሁዋላ በሕዝብዋ ላይ የተፈጸመው ጭፍጨፋ አሁንም ድረስ ድባቡ አልጠፋም። አሁንም ድረስ እያስታወሱ የሚያለቅሱ አሉ። በዚሁ ግፍ ምክንያት በርካቶች አይምሮአቸውንም ስተዋል። በቁንጅናዋ ተማርኮ በጸባይዋ ተመስጦ አፍቅሮ ያገባትን ሚስቱንና የልጆቹን እናት የጥላቻ ቅስቀሳ ሰለባ በመሆን በቆንጨራ ጨፍጭፎ እንዲገድል የተደረገ ሰው በህይወት ቢኖርም ሰው መሆን አይችልም። ሺህ ይቅርታ ሺህ ሱባዔ ሺህ ቅጣት ያንን ጤና መልሶ ሊሰጠው አይችልም። የጥላቻውን መርዝ መጀመሪያ የረጩትና እሳቱን ያራገቡት ግን ለመግዛት እንዲመቻቸው አንዱን ከሌላው አሳንሰው እርስበርስ እንዲጠላላ በማድረግ የኖሩት ቅኝ ገዢዎቹ ናቸው። ከነጻነት  በሁዋላም ጎረቤት በጎረቤቱ ላይ በጥላቻ እንዲነሳሳና ያ ሁሉ እልቂት እንዲፈጸም እጃቸው አለበት የሚባሉት መስቀል ይዘው ክርስትና ሰባኪ ነን የሚሉ ነጮች መሆናቸው ይነገራል።
ኤርትራ “በነጻ አውጪዎቹ” ስትያዝ ለብዙ አመታት እዚያው ኑሮ መስርተው ሃብት አፍርተው የነበሩ ኢትዮጵያውያን “አያት ቅድም አያቶቻችሁ ከዚህ አይደሉም” እየተባሉ በጎሳ ጥላቻ ቤተሰባቸው እንዲፈርስ ተደርጎ ባዶ እጃቸውን በባዶ እግር እንዲባረሩ ወደባህርም እንዲገፉ የተደርጉትን ልናስብ ይገባል። ከመሀል አገርም ከሌላ ብሄረሰብ ተወላጆች ጋር ተጋብተው ይኖሩ የነበሩ ኤርትራውያን እራሱ ኤርትራው በሆነው በመለሰ ዜናዊ “የአይናቸው ቀለም ካላማረን እናባርራልን” የሚል የ እብሪት ፖለቲካ ቤተሰባቸውንና ንብረታቸውን በትነው ከሀገር እንዲወጡ እንደተደርጉ  ልናስታውስ ይገባል። ዛሬም ከየቦታው የሚፈናቀሉት ወገኖቻችንን  ቁጣ ልናስብና ይህ ቁጣም ወዴት ሊያመራ እንደሚችል ማሰቡ ከሚጠብቀን አደጋ እንድንጠነቀቅ ያመቻቻል።
አማራው ከኦሮሞው ቢጣላ ገላጋይ ሆነን እንቆማለን የሚሉት የትግራይ ተገንጣይ ቡድን አባላትና ደላሎቻቸው ሕዝብን ከሕዝብ ለማናከስ ደፋ ቀና የሚሉት እሳቱ ቢነሳ እነርሱ የሚተርፉ መስሏቸው ነው። የተገፋው የተጨቆነውና በደል በቃኝ የሚለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላቱን ለይቶ አውቆ የጥላቻ እሳት እየቆሰቆሱ ያሉትን በተባበረ ክንድ ሊደቁሳቸው እንደሚችል የተገነዘቡ አይመስልም። ለዚህም ነው ሕዝቡ ቁጣውን ወደነዚህ አረመኔዎች ሊያዞርና ሴራቸውን ሊያከሽፍ የሚገባው ዛሬ ነው ጊዜው እየረፈደም ነው የሚል ጥሪ ከየአቅጣጫው የሚስተጋባው። በርካቶች ወደ ጥላቻ ወጥመዳቸው እንዳይገቡ እነዚህን ክፉዎች መንጥሮ ማውጣት ለነገ የማይባል አስቸኩዋይ የህልውና ጥያቄ ነው። መሰረታዊው ልዩነት ሀገር በሚዘርፉ፣ በሚያፈርሱና እልቂት በሚደግሱት ወያኔዎችና በተቀሩት ኢትዮጵያውያን መካከል እንጂ በተለያዩ ብሄረሰቦችና ሃይማኖት ተከታዮች መሀከል አይደለም።
በምዕራቡ ሀገራት በሚሰበክው የመድብለ ፓርቲዎች አስፈላጊነት ምክንያት ኬንያ በርካታ ፓርቲዎች ማቋቋም ባሰበችበት ወቅት ፖለቲከኞቹ መራጮቻቸውን ፍለጋ በየጎጡ መሄዳቸው ያስከተለው ከባድ ቀውስ ዛሬ የሚታወስ ነው። አሜሪካ መድብለ ፓርቲ ብላ አስጨንቃ ከያዘችን ብለው እነዚያው የቀድሞ ፖለቲከኞች ወደየዘመዶቻቸው ሲሄዱ ይህ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ ያገናዘበ አገናዝቦም መፍትሄ የሰጠ አልነበረም። ብዙ ፓርቲዎችም ተፈጠሩ ግን የጎጥ ፓርቲዎች ሆኑ። ይህን በመከተልም አሰቃቂ የሆነ አደጋ ሰላማዊ ተብላ በምትታወቀው አገር ተከሰተ። የአንድ ሀገር ልጆች መሆናቸውን ከመቅጽበት ዘንገተው ኩኩዩ ሉዎ እየተባባሉ በገጀራና በቀስት እርስበርስ ይገዳደሉ ጀመር። ኬንያውያንም እኛ ሰላም ወዳዶችና የጎሳ ፖለቲካ ወደ ጽንፍ የማይወስደን ነን  የሚል ጽኑ እምነት የነበራችው ቢሆኑም የጥላቻው ቅስቀሳ ለጊዜያው የፖለቲካ ጥቅም ከተለኮሰ በሁዋላ በሀገራችን እናያለን ብለው ያልገመቱት የጥላቻ ግድያ ሲፈጸም ለመመልከትና ተሳታፊም ለመሆን ተገደዱ። ። የረገፉት ረገፉ የተፈናቀሉትና ከሞት የተረፉት ግን ዳግም የሰላም እንቅልፍ አይኖራቸውም። ኬንያ የበርካታ የውጭ መንገስታትና ድርጅቶች የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጥቅም የሚያገኙባት ሀገር በምሆኑዋ ዓለም ትኩረት ሰጥቶት እንደ ኮፊ አናን ያሉ መፍትሄ አፈላላጊዎች ሁሉ ተረባርበው እሳቱን ለጊዜውም ቢሆን አበረዱት።
የኛዋ ኢትዮጵያ ግን እኛው ካላዳንናት   በእሳቱ ላይ ነዳጅ የሚጨምር እንጂ እሳት የሚያበርድላት ብዙ እንደማይኖር ልብ ልንል ይገባል። ወራሪን በማሸነፍ የሚገኝ ነፃነት የሚያስከፍለውን መስዋትነት በኩራት ልንሸከም የሚገባን እኛው ኢትዮጵያውያን ነን። አዋሳኝ አገሮችም በአብዛኛው ለኛ መዳከምና መበታተን ተግተው የሚሰሩ ናቸው። የጎጠኞችና የባንዳዎች ብቸኛ ሕልም ደግሞ ምንም ያክል ትሁን ስልጣንና ሀብት ማጋበስ ብቻ ነው። በጎጥ የጀመረ ፀብ በእንጭጩ ካለተቀጨ መንደርና ቤተሰብ ድረስ ይዘልቃል። የትግራይ ተገንጣይ ቡድን ሚሊየኖችን አስፈጅቶ ስልጣኑና ሀብቱ ግን የተገደበው በጥቂት ቤተሰብና መንደር ላይ መሆኑ ሩቅ የማይወስድ ምሳሌ ነው። የትግራይ ሕዝብ በጥቅሉ ከሌላው በተለየ ደስተኛ እንዳልሆነ ማየት ትምህርት ነው። በመከባበርና በመተሳሰብ ለልጆቻችን ለልጅ ልጆቻችን ህልውናና ነፃነት ስንል የአቅማችንን እንስራ ኢትዮጵያንም እናድናት።
በጎጠኞች መርዘኛ ሴራ ኢትዮጵያዊነት አይረታም!
ኢትዮጵያ በነፃነትዋ ተከብራ ለዘለዓለም ትኑር!

Ethiopian Journalists Forum (EJF) warns leaders of three Journalists Associations


by Betre Yacob
Ethiopian Journalists Forum (EJF), the newly established journalists association in Ethiopia, warned leaders of three journalists associations operating in the country.Ethiopian Journalists Forum is a nonpartisan and independent professional association
In a statement issued yesterday, the association accused the officials of Ethiopian journalists Association (EJA), Ethiopian National Journalists Union (ENJU), and Ethiopian Free Journalists Association (EFJA) of fabricating false accusations against the association and members of media organizations.
Ethiopian Journalists Forum is a nonpartisan and independent professional association intended to defend the freedom of speech and of the press in Ethiopia.
The press statement says that the officials have been deliberately engaged in fabricating false accusations ranging from terrorism to conspiracy— aiming to intimidate journalists and members of the association. “They are trying to spoil the name of our association, which is getting a wider acceptance among journalists and media workers”, the statement explains.
“For instance, in an interview published at Addis Admass weekly newspaper issued on March 30, 2014 they said that journalists had been preparing to commit terrorism against the nation and its citizens. They also accused two unnamed countries of backing the journalists. In another article published at Reporter, a weekly newspaper, issued on March 9, 2014 they once again said the same thing accusing journalists”, it further explains.
The statement says the association doesn’t have a response for the groundless accusations of these depraved individuals—who are barking to retain their own cheep benefits. It says it only would like to warn them once and for all to refrain from their unlawful acts.
The EJF was established on 20 January, 2014 considering the harsh working conditions of journalists in Ethiopia; and the importance of a unified media workers and journalists’ voice. In a few months only, the association has been able to get acceptance among journalists and media institutions.
Particularly, the EJF has been welcomed by almost all journalists operating in the free press. Its formation has been good news to those who wish to see an independent institution—which is loyal only to the journalists.
The EJF is supposed by many to be a best framework to work against the deteriorating press freedom in the country and bring about change on the safety of journalists. It is, however, seen as a threat by EJA, ENJU, and EFJA. According to the association, it has begun to experience their accusation since its inception.
The EJF has a vision to become a leading professional association in Ethiopia, which defends the freedom of speech and of the press as well as the rights of journalists.
The Wake of Non-operational Associations
Ethiopian journalists Association (EJA), Ethiopian National Journalists Union (ENJU), and Ethiopian Free Journalists Association (EFJA) were in active for a long period. They came to the stage following the formation of EJF.
Both the associations are accused of being loyal to the regime and of failing to play their role. None of them have ever been seen doing anything to bring about change on the deteriorating press freedom and safety of journalists.
Despite the fact that journalists are still subjected to violence, EJA, ENJU, and EFJA believe freedom of speech and of the press is respected in Ethiopia, and accuse CPJ and other international organizations of defaming the name of the country.
They also accuse Ethiopian journalists of using their rights to incite violence in the country. They even don’t accept the journalists, who are currently behind the bar in the country, are prosecuted because of their job.

Welcome to Stasi-opia: The Stasi-zation of Ethiopia under TPLF/EPRDF rule


by Alem Mamo
Over the last two-decades the people of Ethiopia under the TPLF/EPRDF rule have endured the reign of terror, fear, and propaganda horrifyingly reminiscent of the notorious Ministry of State Security known as the Stasi in the former German Democratic Republic (GDR).1 It is within recent memory that the Stasi security and surveillance campaign kept citizens of East Germany under a constant reign of fear and terror until the fall of the Berlin Wall on November 9, 1989. Totalitarian control of citizens throughout history has left a tragic mark in the collective psyche of humanity. The Stasi, Gestapo, KGB, Benito Mussolini’s OVRA, and many others, all of these brutal institutions committed heinous act of terror against innocent citizens.Ethiopian government is spying on its citizens
The uncomfortable truth is that we are not even talking in past tense term about the horror and repression of citizens in our world. In fact, such organized and government-led criminal and terrorist enterprises continue to function in the 21st century world. Among several of such regimes in the world today, one in particular stands out on the spectrum of totalitarian index. With its full-fledged infrastructure of security and surveillance machinery, the TPLF/EPRDF-led regime in Ethiopia has time and again demonstrated that its league is not with those who envision freedom and justice but with those who rule by fear and terror.
The recent Human Right Watch report entitled: “They Know Everything We Do” –Telecom and Internet Surveillance in Ethiopia is a testament and live autopsy into the soul of the lawless regime in Addis Ababa. The title of the report “They Know What We Do”speaks volumes to the extent and the depth of the regime’s reach into the daily lives of the general population. Millions of Ethiopians, who continue to suffer under this regime, are grateful to HRW in compiling such a comprehensive report and exposing the true nature and identity of the TPLF/EPRDF regime. However, it is worth noting that there is nothing new or revealing that the people of Ethiopia didn’t already know. For far too long, citizens in Ethiopia used all available outlets to share with the rest of the world their long suffering under the regime and its institutions of state terror and violence. By in large their pleas and cries for help have fallen on deaf ears, while the regime continues its repression and torture of innocent citizens.
The Stasi-zation of Ethiopia under TPLF/ EPRDF is ironically a continuation of Mengistu Hailemariam’s military rule, which received considerable technical and logistical support from GDR’s Stasi to enhance its security and surveillance structure. This included the training of professional “interrogators,” i.e. torturers and “field workers”, who kept constant watch on citizens. The difference this time is that the regime in Addis Ababa is heavily relying on the expertise and support of Western and Chinese companies for tools and know-how on telephone and internet spying.
To ensure that the people would become and remain submissive, East German communist leaders saturated their realm with more spies than had any other totalitarian government in recent history. The Soviet Union’s KGB employed about 480,000 full-time agents to oversee a nation of 280 million, which means there was one agent per 5,830 citizens. Using Wiesenthal’s figures for the Nazi Gestapo, there was one officer for 2,000 people. The ratio for the Stasi was one secret policeman per 166 East Germans. When the regular informers are added, these ratios become much higher: In the Stasi’s case, there would have been at least one spy watching every 66 citizens! When one adds in the estimated numbers of part-time snoops, the result is nothing short of monstrous: one informer per 6.5 citizens. It would not have been unreasonable to assume that at least one Stasi informer was present in any party of ten or twelve dinner guests.
“Ethiopia’s government is deploying cutting-edge cyber and phone surveillance technologies from China and other nations to conduct widespread spying aimed at suppressing political dissent, according to a new report. Using modern technology from Chinese telecom giant ZTE, Ethiopia’s state telecom company has spent the last five years meshing that gear with additional spy software from European suppliers to create government surveillance tools spanning social media, phone, and Internet communications,” reported the Christian Science Monitor quoting the Human Right Watch report.
Typical of totalitarian regimes, the TPLF/EPRDF regime saturated cities, towns, and neighborhoods with spies and informants the same way Stasis and other totalitarian regimes have done. Furthermore, the regime’s control over the economy, such as through telecommunications networks, made it far easier to spy on citizens. The political, economic, and all major structures in Ethiopia are fully under the grip of a few select members of TPLF minority.
In today’s Ethiopia, let alone freedom of expression or assembly, citizens are thrown into jail for what they might be thinking or simply for having a particular name or for belonging to a particular ethnic group. And yet, western countries who claim to uphold the fundamental values of freedom and justice continue to lend support knowing too well the moral and material support they provide is being used to terrorize citizens of Ethiopia. During my recent visit to Ethiopia and elderly man told me “We understand Chinese support to this regime because the Chinese don’t claim to uphold the values of democracy and freedom. What we don’t understand is why western nations continue to betray the Ethiopian people by continuing their support to the most brutal regime in this country’s history.”
After two successive totalitarian regimes, starting in 1974 with the military junta and then with the baton of repression and surveillance picked up by TPLF/EPRDF in 1991, the people of Ethiopia still continue to struggle toward their long-awaited freedom. The difference between the military regime and TPLF/EPRDF are cosmetic, not substantial. The notorious Makelawi prison and all prison dungeons used by the military regime are still used by this regime. In fact, the number of prisons in Ethiopia has considerably increased under this regime. Obviously, the military regime garnered support from USSR and Eastern Block to advance its repression and state violence. On the other hand, TPLF/EPRDF won the support of China and western powers who claim to stand for democracy and freedom. The support of the western nations to the TPLF/EPRDF regime has baffled the Ethiopian people, confirming their suspension about the hypocrisy and moral inconsistency of the western powers.
Ultimately, the Ethiopian people will win their freedom as East German’s people freed themselves from the clutches of Stasi terror. In the end, the structures of violence will be dismantled and the structures of political and economic justice will be built. The question is not if, but when because freedom and justice has the last word. As history tells us, totalitarian regimes that demand their legitimacy by constituting security surveillance network to keep an eye on the public are brought down by the same public they thought they had a total control over. Fear has a shelf life because the people’ yearning for freedom and justice overrides the wall of fear. We have witnessed in East Germany citizens breaking down the physical and psychological barrier to claim their freedom. More recently, people of the Arab world rose up to dismantle structures of oppression. This is indeed a testament to the unflinching desire to be free, which is more powerful than the structures of the security and surveillance state.
———————–
1. To ensure that the people would become and remain submissive, East German communist leaders saturated their realm with more spies than had any other totalitarian government in recent history. The Soviet Union’s KGB employed about 480,000 full-time agents to oversee a nation of 280 million, which means there was one agent per 5,830 citizens. Using Wiesenthal’s figures for the Nazi Gestapo, there was one officer for 2,000 people. The ratio for the Stasi was one secret policeman per 166 East Germans. When the regular informers are added, these ratios become much higher: In the Stasi’s case, there would have been at least one spy watching every 66 citizens! When one adds in the estimated numbers of part-time snoops, the result is nothing short of monstrous: one informer per 6.5 citizens. It would not have been unreasonable to assume that at least one Stasi informer was present in any party of ten or twelve dinner guests.http://www.nytimes.com/books/first/k/koehler-stasi.html