Wednesday, January 15, 2014

ኢትዮጵያዊነታችን ከአማራ ና ከኦሮሞ የዘር ፖለቲካ የላቀ ነው መሆንም አለበት፣፣

    by Nathnael abate      
ሚኒልክን መሃል ያደረገ ፖለቲካዊ ጽንሰ ሃሳቦች በአማራዎች ዘንድ እንደጀብዱ እና በኦሮሞዎች ዘንድ እንደዉርደት፣ማንነት እንደማጣት ተደርጎ ሲያነታርክ፥ስነታረክበት ሰንብቷል፣፣የሃገራችን የፖለቲካ ፓርቲዎችና ፖለቲከኞችም ይህንን መሰረት ያደረገ ፖሌቲካዊ ሃሳብ ሲያራምዱ ይታያሉ፣፣
 ይህ በዘር የተመሰረተ ሃሳብ ኢትዮጵዊነታችንን ከዉስጣችን እያጠፋ ይገኛል፣፣ በመጀመርያ ኢትዮጵያዊነታችን የዉስጥ ደማችን ማንነትና የእኛነታችን መገለጫ እንጅ የዘርና ጎሳ ሃረጋችንን እየቆጠርን እርስበርስ የሚንበላላበት የጥላቻ መለያ ሥም ወይም መሳሪያ አይደለም፣፣
እግዲህ ስለሚኒልክ ካወራን እንደማንኛዉም መሪ መልካምና ክፉ ሰርቶ አልፏል፣፣ ነገር ግን አንድ መታወቅ ያለበት ነገር እሱን በሚያደቁና በሚከተሉ ሰዎች ዘንድ ተደጋግሞ የሚነሳዉ የአድዋ ድል የሚኒልክ ብቻ ተደርጎ የሚወስድበት ሁኔታ ይስተዋላል ሆኖም ድሉ የሚኒልክ ወይም የአማራ ብቻ ሳይሆን የኦሮሞ ፣የአማራ ፣የወላይታ ፣የሲዳማና የለሎች የኢትዮጲያ ህዝቦች ታርክ መሆኑ መታወስ ያለበት ጉዳይ ነዉ፣፣
ሚኒልክን ለምትጠሉና እንደሰይጣን የሚታዩ ወገኖች ያ ያለፈ ታርክ እያላዘናችሁ ልዩ ነ ት ለማስፋት አትጣሩ፥ ይልቁንስ ያ የትናንት ታርክ እኛን ይበልጥ ያቀራርበን፥አንድ የጋራ ታርክ እንዳለን አስባችሁ ወደፊት በአንድነት የተመሰረተ ጠንካራ ማህበራዊ፥ኢኮኖሚያዊና ፖሌቲካዊ ስርዓት ያለበት ሃገር ለመመስረት ስላለፈው ሳይሆን ስለወደፍት አስቡ፣፣
እንድሁም ሚኒልክን እንደመላአክ የሚታዩ ወገኖች የለሎችን ማንነት ባለመቀበልና የአጼዎችን ጉራ እየነዛችሁ፣ሃገርን ለማፈራረስ የሚትሞክሩን ነገር ከእንግድህ አብቁ፣፣ ባሁኑ ሰዓት ሁሉም ኢትዮጲያዊ ታርኩን ጠንቅቆ ያዉቃል ክፉ ና ደግ መች እንደደረሰበት፣፣
ስለዚህ፣ወደፊት በርግጥ የተሻለ ነገር ለሃገራችን የሚንመኝ ከሆንን፣ስላለፈዉ የአጼዎች ዝና በመጎረርና የአጼዎችን በደል በመዘርዘር፣ ዘረኝነትና ጎሴኝነት ከማራመድ ታቅበን በአንድነት ጠንካራ ሃገር ለመመስረት እንነሳ፣፣

ባሁኑ ሰዓት ለሃገራችን ጠላት፥ለህዝባችን ዉርደት ያለፈዉ ታርክ ሳይሆን ወያነ ነው፣፣ ወያነ የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊ ቀንደኛ ጠላት ነዉ፣፣ ወያነን በህብረት እንዋጋ!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!

በአገራችን እየከሰመ ያለው ሃሳብን በነፃ የመግልፅ እና መረጃ የማግኘት መብት በገዥው መንግስት መልካም ፍቃድ ላይ የተመሠረት ወደመሆን ደረጃ ተሸጋግሯል፡፡


የመረጃ ነፃነት ? …. (ይድነቃቸው ከበደ )
‹‹ ሕዝቡ እኔ ማን እንደሆንሁ ይላል ? ›› በማለት እየሱስ ክርስቶስ መረጃ ይጠይቃል ፤ ደቀመዛምርቶችም ስለሱ የተባለውን አንድም ሳያስቀሩ ይነግሩታል፡፡ እሱም መልሱ እንዲህ ይላቸዋል ‹‹ እናንተስ እኔ ማን እንደሆንሁ ትላላችሁ ? ››አላቸው ፡፡ እነሱም መለሱለት፡፡ ሙሉ ታሪኩ ሉቃስ 9ቁ 18 ላይ ይገኛል ፡፡Yidnekachew Kebede
መረጃ አይናቅም አይደነቅም ማለት እንዲህ ነው፡፡ በመሰረቱ ክርስቶስ ሰዎች ስለሱ ምን እንዳሉ ብቻ ሳይሆን ምን እያሰብ እንደነበር የሚያውቅ አምላክ ነው፡፡ ግን መጠየቅ እና መመለስ አሳብን መግለፅ የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ባህሪ ነው፡፡ ለዚህም ነው ክርስቶ እንደሰው በምድር በተመላለሰበት ወቅት መረጃ ይጠይቅ የነበረው እሱም ስለራሱ መረጃ ይሰጥ የነበረው፡፡ እርግጥ ነው ክርስቶስ ይህን ሲጠይቅ የራሱ ምክንያት አለው፡፡
በመሆኑም ሃሳብ መግለፅ ተፍጥራዊ መብት ነው ወደሚለው ዓለም አቀፍ ስምምነት በመደረሱ የመናገር ሃሳብን የመግለፅ ነፃነት የዲሞክራሲ ዋና የድም ስር ነው የተባለው፡፡ ስለዚህም ተሰባስቦ መቃወም እንዲሁም መደገፍ ፣ አንድ ሰው የሚመስለውን ሃሳብ በፈለገው መንገድ መግለፅ፣ የመምረጥና የመመረጥ፣ መንግስትን የመተቸት፣ በራስ ፍቃድ የመናገረ እና ያለመናገር ፣ በዓልንና አይማኖትን መከተልና ማስፋፋት እንዲሁም ህግ ለሁሉም የሚሰራ ስለመሆኑ መረጋገጥ እና የመሳሰሉት ሁሉ ተግባራዊ የሚሆነው ተአቅቦ ያልተደረገበት የመናገርና የመረጃ መብት ልውውጥ ተግባሪዊ ሲሆን ብቻ ነው፡፡
ለመደርደሪያነት የዚህን ያኸል ከተባለ ወደ ዋናው ጉዳይ አስፈቅደን ሳይሆን ፈቅደን እንገባለን፡፡ ያነሳነው አሳብ ‹‹ መረጃ ›› እንደመሆኑ መጠን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ተፍጥሯዊ መብታችን በፈለግነውና በፈቀድነው መንገድ እንገልፃለን፡፡ እኛ ስል ለመረጃ ነፃነት የቆምነው ሁላችንም ማለቴ ነው፡፡
ሰው በመናገሩ አና በመፃፉ ብቻ ለእስር እና ለስደት የሚዳረግበት አገር በዋነኝነት ከሚጠቀሱት ውስጥ ኢትዮጵያ አንዶ ናት፡፡ ነገር ግን ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት የአመለካከት እና ሐሳብን በነፃ የመያዝና በማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ የመግለፅ ነፃነት አለው፡፡የሚለው በኢትዮጵያ ህገመንግስቱ አንቀፅ 29 ተፅፎ ይገኛል፡፡ በእርግጥ ይህ መብት ገደብ ሊጣልበት እንደሚችል በህገ መንግስቱ ላይ ተገልፆ የተቀመጠ ሲሆን ገደብ ግን መሠረታዊ የሆነውን መረጃን የመስጠት እና የማግኘት እንዲሁም አስተሳሰብ ላይ ወይም አመለካከት ላይ ውጤት እንደማይኖረው በህገመንግስቱ ተገልፆ ይገኛል፡፡
ይሁን እንጂ አሳብን በነፃ ማሰብና ማንሸራሸር በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ እጅግ አዳጋች ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ አልፎ ተርፎ በአስተሳሰብ ወይም በአመለካከት ላይ ተፅኖ እስከመፍጠር ተደርሶኦል ፡፡ ነገር ግን እንዲህ አይነቱ ሁኔታ ለህግም ሆነ ለሞራል ተቃራኒ እንደመሆኑ መጠን የፈጀውን ፈጅቶ ወደነበረበት መመለሱ የማይቀር ሃቅ ነው፡፡ ነፃ አሳብ የሚንሸራሸርባቸው ነፃ ጋዜጦችና መፅሔቶች ምን ያህል አሉ ? ያሉት ጋዜጦች እና መፅሔቶች እየደረሰባቸው ያለው ማስፈራሪያና ዛቻ ደረጃው ምን ያኸል ደርሶአል የሚለውን መመልከት ተገቢ ነው፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በቅርቡ በወጣው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ አክራሪነትና ፅፈኝነት የሚያበረታቱና የሚያሰራጩ በማለት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለህዝቡ ተገቢውን መረጃ እያስተላለፉ ያሉ የእትመት ውጤቶችን ከገቢያ ለማውጣትና ፈርጆ ለመክሰስ እየተደረገ ያለው ዝግጅት ሌላው ማሳያ ነው፡፡ጋዜጠኞችን በማሰቃየት፣በማሰር እና እንዲሰደዱ በማደረግ ኢትዮጵያ በዓለም ላይ በሁለተኝነት ደረጃ ላይ ትገኛለች ፡፡መንግስትን ተችቶ የፃፈና ፁሁፉ የወጣበት ጋዜጣ ወይም መፅሔት ጨምሮ ሁሉም ለእስር የሚዳረግበት ወይም አደገኛ ዛቻና መስጠንቀቂያ የሚሰጥበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡
በዲሞክራሳዊ ሥርዓተ ዜጎች የሚኖሩት ግልፅ በሆነ የሃሳብ ልውውጥ ነው፡፡ የትኛውም አይነት ሃሳብ ከማንም ሊመጣ ይችላል ቁም ነገሩ መሆን ያለበት የሚመጣው ሃሳብ የሚመከተው በምንድነው የሚለው ነው፡፡ ለነፃ ንግግር ችግር የተሻለው መንገድ የበለጠ ነፃ ንግግር ነው፤ በመናገር መብት ላይ የሚደረግ ማናቸውም ተፅእኖ ሲውል ሲያድር በእያንዳንዱ ግለሰብ የመናገር መብት ላይ ስጋት ሊያስከትል ይችላል፡፡ለዚህም ነው ወደነበረበት መመለሱ የማይቀር ነው ለማለት የሚያስደፍረው፡፡ምክንያቱ ደግሞ ማንም ሰው በስጋት ውስጥ መኖርን ስለማይፈልግ ነው፡፡
በመሆኑም በአገራችን እየከሰመ ያለው ሃሳብን በነፃ የመግልፅ እና መረጃ የማግኘት መብት በገዥው መንግስት መልካም ፍቃድ ላይ የተመሠረት ወደመሆን ደረጃ ተሸጋግሯል፡፡ለዚህም እንደማሳያ ከሰሞኑ የህዝብ ሳይሆን የገዥው መንግስት አንደበት በሆነው በኢቲቪ በተላለፈው የዘጋቢ ፊልም ግለሰቦችም ሆነ በአገር ውስጥ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በተለይ ሰማያዊ እና አንድነት ፓርቲ ለኢሳት መረጃ ከመስጠት እንዲቆጠቡ ምክር መሰል ማስጠንቀቂያ ተላልፏል፡፡
ለዚህም እንደምክንያት የቀረበው ኢሳት የተባለው የመገናኛ ብዙሃን በሽብርተኛ ድርጅት የሚደገፍ ነው የሚል ምክንያት ነው፡፡ ኢቲቪ በኢህአዴግ እንደሚደገፍ ሁሉ ኢሳት በማንም ሊደገፍ ይችላል፤ ቁም ነገር ሆኖ መታየት ያለበት ኢቲቪ ሆነም ኢሳት የሚያስተላልፉት መልዕክት ምንድነው ፡፡ በተጨማሪ መልዕክቱ ለህግም ሆነ ለሞራል ምን ያኸል ተቃራኒ ነው የሚለውን ነው፡፡ በተጨማሪ ኢቲቪ እንዲሁም ኢሳት በህግ መደመጥ እንዲሁም መሰማት የተከለከሉ የመገናኛ ብዙሃን ናቸው ወይ ተብሎ መጠየቅና መልስ ሊሰጥባቸው የሚገባ አሳቦች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ወደ መልሱ ስናመራ ኢቲቪ እንዲሁም ኢሳት በህግ የተከለኩ አይደሉም ዋንኛው እና አስፈላጊው ነገር ይሄ ነው ሌላው የህጉ ደጋፊ ሃሳብ ነው፡፡
በመሆኑም ከዚህ በኋላ የህግ ጉዳይ ሳይሆን የፍላጎት ምርጫ ነው የሚሆነው፡፡ የፈለጉትን መስማት እና ማዳመጥ እንዲሁም በፈለጉት የመገናኛ ብዙሃን መንገድ ሃሳብን መግለፅ እና መረጃን ማግኘት ግለሰብ ከሆነ እንደግለሰቡ፣ ተቋም እንደተቋም እንዲሁም ፓርቲ እንደ ፓርቲ የመምረጥ የራስ መብት ነው፡፡ ይህ ደግሞ አንዱ የዲሞክራሲ መገለጫ ነው፡፡ በዚህም መሠረት ከኢቲቪ ኢሳት ከአዲስ ዘመን አዲስ አድማስ የዝወትር ፍላጎታቸው ለሆነ እንዲሁም በተመሳሳይ ከኢሳት ኢቲቪ ከአዲስ አድማስ አዲስ ዘመን ለመረጡ ምርጫቸውን ማክበረ ነው፡፡
ሌላው እና አሳሳቢ ሊሆን የሚገባው ሰው የመረጠውን መስማትና ማዳመጥ እንዲሁም ማንበብ መብቱ እንደጠጠበቀ ሆኖ ግለሰበ ወይም ተቋም ሃሳቡን እንዴት የመግለፅ መብት እና ግዴታ አለበት የሚለው ነው፡፡ ይህን በተመለከተ ተቋም ወይም ግለሰብ ሃሳብን ወይም መረጃን በማንኛውም መንገድ የመገልፅ ሙሉ መበት በህግ የተጠበቀ ነው ፡፡እንዲኹም የዚህ መብት ተቃራኒ የሆኑ ማናቸውም ነገሮች ተቀባይነት እንደሌላቸው በህገመንግስቱ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በዚህም መሰረት በኢሳት ሆነ በማናቸውም የመገናኛ ብዙሃን ሃሳብን መግለፅ እና መረጃን መስጠጥ በራሱ ወንጀል ወይም ጥፋት አይደለም ይህ የሆነው ደግሞ መብት ከመሆኑ አንፃር ነው፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ መታየት ያለበት ሃሳብን በመግለፅ እና መረጃን በመስጠት ዙሪያ ግዴታ ሊያመጣ የሚችለው ምንድነው የሚለው ነው፡፡ ግለሰቡ ወይንም ተቋሙ በግልፅ በህግ የተከለከለ መረጃ ወይም ሃሳብ የገለፀ እንደሆነ ግዴታው ተጠያቂነትን ስለሚያመጣ በህጉ መሠረት ተጠያቂ ይሆናል፡፡ ይህ የህግ ተጠያቂነት አዱላዊነት የሌለበት ለሁሉም በሁሉም ቦታ እኩል የሚሰራ ነው፡፡ ይህም ማለት በህግ የሚያስጠይቅ ንግግር በኢሳትም ሆነ በኢቲቪ እንዲሁም በቢቢሲ ያደረግ በህግ ከመጠየቅ ንግግር ያደረገበት የብዙሃን መገኛኛ ሊታደገው አይችልም እንደማለት ነው፡፡
በመሆኑም በኢሳት ሃሳብን መግለፅ እንዲሁም መረጃ መስጠት አልፈልግም ማለት መብት ነው፡፡ ነገር ግን በኢሳት አሳባችሁን አትግለፁ መረጃም አትስጡ ማለት ከፍላጎት የመነጨ ሃሳብ ብቻ ሳይሆን የለየለት የእብሪት ተግባር ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ አሰፋሪ ምኞት እና ተግባር የሕግና የዲሞክራሲያዊ መብት ካለማወቅ የሚመነጭ አስተሳሰብ ብቻ ሳይሆን ተምሮ ያለመለወጥ ልክፍትም ጭምር ነው! በተለይ በመንግስት ደረጃ ሲታሰብ እጅግ

Emerging Political differences between Oromo Organisations


by Dr Biri Yaya

SBS Amharic Radio

00:00
00:00

1. OLF that is led by Ato Daud Ibsa
The spokes-person for this group, more or less, repeated the long standing political stance of the OLF that the organisation’s objective is for the ‘freedom’ of the Oromo people through a self-determination with all options under consideration(autonomy to independence).
2. Oromo Democratic Front,ODF (Re: Lencho Leta, Dr Dima Negewo)
This group is yet to establish itself as a political party. Dr Dima Negewo is a seasoned and articulate politician.
In the interview with the Australian radio, Dima repeated what the group’s most articulate spokes-person, Lencho Bati, stated sometime ago. The group is keen to find a mid-point to re-engage and energise a discourse on the resolution of the conflict by some sort of negotiation with the current ruling clique in Ethiopia.
They would like to join in hands wih Ethiopian opposition groups for the ‘proper implementation’ of the provisions of the current federal constitution that the TPLf/Eprdf uses as a device to mislead the nation.
The ODF sees Oromos as a subject people of the empire while accepting the prospect of a democratic Ethiopian state when and if one emerges in the future.
3. OLF that General Kemal Gelchu is a chairman of
This group’s stance is the most clear:
* Full acceptance that Oromos are Ethiopians who are, nevertheless, being denied of their full citizenship rights due to the undemocratic nature of previous and current regimes in Ethiopia.
General Kemal has dismissed the other Oromo groups’ political stance which sees Oromos as non-Ethiopian. He ridiculed the assumption that oromos are not Ethiopians as a shallow thinking that was accidentally borrowed from comparisons with the status of the American slaves. He is right in that!
The crucial lines of emphasis and differences in this group to notice are:
* Oromos are not colonial subjects
* The Group does not believe that there is any mileage in trying to join the tested and failed attempt of working as a ‘legal’ opposition within the constraints of the TPPLF/EPLF’s domination.
However, what is common to all the three strands of the Oromo groupings is the realization that Oromos’ rights cannot be attained without some level of cooperation with other stakeholders in Ethiopia.