Saturday, January 4, 2014

ዶ/ር ነጋሦ ጊዳዳ ከማንኛውም የፓርቲ ፖለቲካ ራሳቸውን አገለሉ – “አርጅቻለሁ፤ በቃኝ”


 
negaso gidada (ዘ-ሐበሻ) በቅርቡ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ባደረገው ምርጫ ስልጣናቸውን ለኢንጂነር ግዛቸው ያስረከቡት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ፓርቲያቸው አንድነት የመስራች ጉባኤውን በአዲስ ቪው ሆቴል እያደረገ ባለበት ወቅት ባደረጉት ንግግር ቀጣይ የፖለቲካ ህይወታቸውን አስመልክቶ የደረሱበትን ውሳኔ አሳወቁ።
የፓርቲውን የመመስረቻ ጉባዬ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቀድሞው የአንድነት ሊቀመንበር ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ ‹‹ከአሁን በኋላ ከየትኛውም የፓርቲ ፖለቲካ ራሴን አግልያለሁ፡፡ ለዚህ ምክንያቱ ዕድሜዬ 70 መድረሱ ነው፡፡ትግሉን ወጣቶች መምራት እንዳለባቸው አምናለሁ፡፡ስለዚህ በቀሪው ህይወቴ ገለልተኛ በመሆን አገሪን ለማገልገል እሰራለሁ፡፡በአንድነት አዲሱ ብሄራዊ ምክር ቤት ከ65ቱ ውስጥ 47 ወጣቶች መሆናቸው አስደሳች ነገር ነው፡፡አዲሱ ፕሬዘዳንት ስራ አስፈጻሚ ውስጥ ከ65% በላይ ወጣቶች እንደሚሆኑ መናገራቸውም ያስደስተኛል፡፡›› ማለታቸውን የአንድነት ፓርቲ ሚድያዎች ዘግበዋል።
ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ኢሕአዴግን ሲለቁ አቶ መለስ ዜናዊን “አሁንስ መንግስቱ ኃይለማርያም መሰልከኝ” በሚል በቃኝ ያሉ ሲሆን አሁን ደግሞ ከማንኛውም የፓርቲ ፖለቲካ በቃኝ ያሉት በእድሜ መግፋት ነው።
ዛሬ በአዲስ ቪው ሆቴል ኢንጂነር ግዛቸው በአብዛኛው በወጣት የተያዘውን ካቢኔያቸውን ይፋ አድርገዋል። ዝርዝራቸውም የሚከተሉት ናቸው፦
1) አቶ ተክሌ በቀለ ——- ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት 2) አቶ በላይ ፈቃዱ ——– ምክትል ፕሬዘዳንት 3) አቶ ስዩም መንገሻ ——– ዋና ጸሀፊ 4) አቶ ዳንኤል ተፈራ ——– የድርጅት ጉዳይ ሀላፊ 5)አቶ ሃብታሙ አያሌው ——- የህዝብ ግኑኝነት ሀላፊ 6)አቶ ዘለቀ ረዲ ——— የውጪ ጉዳይ ሀላፊ 7) አቶ አስቻለው ከተማ ——- የፋይናንስ ጉዳይ ሃላፊ 8)አቶ ሰለሞን ስዮም ——– የፖለቲካ ጉዳይ ሃላፊ 9) አቶ ዳዊት አስራደ ——– የኢኮኖሚ ጉዳይ ሃላፊ 10)አቶ አለነ ማህጸንቱ ——- የማህበራዊ ጉዳይ ሃላፊ 11) ወ/ሮ የትናየት ቱጂ ——- የህግና ሰብአዊ መብት ጉዳይ ሃላፊ 12) አቶ ትእግስቱ አወሉ ——- (የአዲስ አበባ ምክር ቤት ሃላፊ በመሆናቸው በቀጥታ የካቢኔ አባል ሆነዋል)

ኢህአዴግ በመንግስት ወጪ ለመጪው ዓመት ምርጫ ሕዝብ የማደራጀትና የመቀስቀስ ስራ ጀመረ

                    

ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ ከ2007 አገር አቀፍ ምርጫ ጋር በተያያዘ በተለይ በአዲስአበባ ከተማ ሕዝብ ቅሬታ የሚያቀርብባቸውን የመልካም አስተዳደር፣ የሙስናና የልማት ችግሮችን ለመፍታት ከፍተኛ በጀት መድቦ እየተንቀሳቀሰ ነው።

የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር የ2006-2007 ዕቅድ አካል እንዲሆን በተደረገው ይህ ከመጪው ዓመት ምርጫ ጋር በቀጥታ የተያያዘው ዘመቻን በብቃት እንዲያስፈጽሙ ለክፍለከተማና ወረዳ አመራሮች ግልጽ መመሪያ ከመተላለፉም ባሻገር በአቅም ግንባታ ስልጠና መወጠራቸው ታውቋል፡፡
በዚሁ መሰረት በከተማ አስተዳደር ውስጥ መልካም አስተዳደርን ሊያሰፍንና ልማትን ሊያፋጥን የሚችል የልማት ሠራዊት በመገንባት ፣የወረዳዎችን ሁለንተናዊ አቅም ማሳደግ፣ቀልጣፋ፣ውጤታማ ፍትሐዊ አስተዳደር በማስፈን የህዝቡን እርካታ ማረጋገጥ ዓቢይ ዕቅድ ሆኖ እየተሰራበት ይገኛል፡፡ ይህንንም ለማሳካት በአዲስአበባ በየደረጃው የሚገኙ የ3 ሺ 500 አመራሮች አቅምና ክህሎት በማሻሻል
ዕቅዱን የማስፈጸም ብቃትና ቁርጠኝነትን ለማሳደግ ስልጠናዎች እየተሰጡ ነው።
በአስተዳደሩ በተለያዩ ቢሮዎች የሚገኙ የመንግስት ሠራተኞችንም አመለካከትና የክህሎት ችግሮችን በመቅረፍና ልማታዊ አስተሳሰብ እንዲያዳብሩ ማድረግም የዕቅዱ አካል ሲሆን በመንግስት መዋቅሩ ካሉት ሰራተኞች 75 በመቶ የሚሆኑትን የለውጥ ኃይል ለማድረግ፣ከዚህ ውስጥ 60 በመቶው በያዝነው በ2006 በጀት ዓመት ለመፈጸም ታቅዶ እየተሰራበት መሆኑ ታውቋል፡፡
ኢህአዴግ ከዚህ ቀደም የፈጠራቸው የተለያየ አደረጃጀቶች ማለትም የወረዳና የክፍለከተማ እንዲሁም የከተማ የሕዝብ አማካሪ ምክርቤቶች ፣የሴቶች፣የወጣቶች የመሳሰሉ አደረጃጀቶችን በመጠቀም በመጪው ምርጫ ወሳኝ ሚና እንዲጫወቱ “ልማትና መልካም አስተዳደርን ለማፋጠን” በሚል ሽፋን የአስተዳደሩ የበጀትና የቴክኒክ ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ታውቋል፡፡
በዚሁ መሠረት 38ሺህ የከተማ፣የክፍለከተማና የወረዳ ምክርቤት አባላትን፣ 50ሺህ የተለያዩ የሕዝብ አደረጃጀቶችንና ልዩ ልዩ ተለጣፊ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የሲቪክ ማህበራት አቅም በዚህ ዓመት እንዲያድግ እንደሚደረግ ታቅዶአል፡፡
ገዥው ፓርቲ ከምንም በላይ አነስተኛ ጥቃቅን ተቋማትን በብዛት በማደራጀትና ያሉትንም በብድር በማጠናከር ለምርጫ ድጋፍ ለማሰባሰብ ከወዲሁ እየሠራ ነው፡፡ በዕቅዱ መሰረት ዘንድሮ እና በቀጣይ ኣመት በድምሩ ለ475 ሺህ ስራአጥ ወጣቶች ስራ እፈጥራለሁ ብሎአል፡፡ አዲስ ስራ ፈላጊ ዜጎች ፍላጎታቸው እየታየ በ16 ሺህ 500 ኢንተርፕራይዞች እንዲደራጁ እንደሚደረግ፣ ከዚህ ውስጥ 8 ሺህ 750 በዚህ ኣመት እንደሚደራጁ ተመልክቶአል፡፡በተጨማሪም ለአዲስ ስራ ፈላጊዎችና ለነባር ኢንትርፕራይዞች ብር 1 ቢሊዮን 700 ሚሊዮን እንዲቆጥቡና 2 ቢሊዮን 7 ሚሊዮን ብር ብድር እንዲመቻችላቸው ተወስኖ እየተሰራበት መሆኑን ለማወቅ ተችሎአል፡፡
ኢህአዴግ ለቀጣዩ ዓመት አገር አቀፍ ምርጫ ከወዲሁ በልማትና በመልካም አስተዳደር ሽፋን ሕዝብ የማራጀትና የመቀስቀስ ስራዎችን ማከናወኛ የሚውለውን በጀት በአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር የሚሸፈን መሆኑም የአስተዳደሩ ምንጭ ጠቁሟል፡፡

የጃዋር ተቃርኖዎች


ባለመንጫው መቼ ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳል?

በጌታቸው ሺፈራው
የዛሬን አያድርገውና ወጣቱ የፖለቲካ ተንታኝ ጃዋር መሃመድ በበርካቶች በተለይም በዲያስፖራው ዘንድ ተቀባይነት ነበረው፡፡ ጃዋር በተለያዩ ጊዜያት ሶማሊያና የኢትዮጵያ ሁኔታ ከሚሰጠው ትንተና ባሻገር ባገኛቸው አጋጣሚዎች ሁሉ የኢህአዴግን አስተዳደር ሲቃወም ተስተውሏል፡፡ ለአብነት ያህል በአንድ ወቅት ከቀድሞው የኮሚኒኬሽን ሚኒስተር አቶ በረከት ስሞኦን ጋር አልጀዚራ ቴሊቪዥን ላይ ቀርቦ ለኢትዮጵያውያንን ጠበቃ ሆኖ መከራከሩ አይዘነጋም፡፡ ይህ የጃዋር ጥረት ከኦሮሞ ብሄርተኝነትንና የፖለቲካ ተንታኝነት አልፎ የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሚል ክብር አጎናጸፈው፡፡ ጃዋር ራሱም ከጠባብ ብሄርተኝነት ይልቅ በኢትዮጵያዊነት ማዕቀፍ ውስጥ አብሮ መስራት እንደሚያስፈልግ መክሯል፡፡ ለአብነት ያህል የብአዴን ጀኔራሎች ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ ተለቅመው በታሰሩበት ወቅት ለአማርኛ ተናገሪ ኢትዮጵያውያን ተከራክሯል፡፡ እነዚህ ህዝቦች ላይ የሚደርሰውን በደል ለማስቆምም ኢትዮጵያውያን በአንድነት መስራት እንዳለባቸው መክሯል፡፡ በወቅቱ ‹‹Ethiopia: General Tadesse and General Asaminew›› በሚል መጣጥፉ ኢትዮጵያውያን በየ ብሄራቸው ከመታጠር ይልቅ አንድ መሆን እንዳለባቸው ለማሳሰብ ታዋቂውን ጸረ ናዚ አባባል ተቅሶ  እንዲህ መክሯል፡፡ ‹‹መጀመሪያ በኮሚኒስቶቹ ላይ መጡ፡፡ አልተናገርኩም፡፡ ምክንያቱም ኮሚኒስት አልነበርኩም፡፡ በመቀጠልም በማህበራቱ ላይ መጡ፡፡ አልተናገርኩም፡፡ ምክንያቱም ማህበራቱ ውስጥ አልነበርኩም፡፡ ከዚያም በቤተ እስራኤላዊያን ላይ መጡ፡፡ አልተናገርኩም፡፡ ምክንያቱም ቤተ እስራኤላዊ አልነበርኩም፡፡ ከዚያም በእኔ ላይ መጡ፡፡ (አሁን) ለእኔ የሚናገርልኝ ማንም አልቀረም፡፡›› ብሎ ኢትዮጵያውያንን አስጠንቅቆ ነበር፡፡
‹‹በኢትዮጵያውያን መካከል ጥላቻን እየዘራ ለምዕተ አመት ስልጣኑን እያራዘመ የቆየውን አምባገነንነት መበጠስ የግድ አስፈላጊ ነው፡፡ የተረጋጋ አገርና ዴሞክራሲ ለመመስረት ያስችል ዘንድ አንዱን ቡድን ከሌላው ቡድን እያጋጨ የመኖርን አዙሪት መበጠስ ይኖርብናል፡፡ ዜጎቻችን በሰላምና በተድላ ይኖሩ ዘንድ በአገራችን የህግ የበላይነት መስፈን ይኖርበታል፡፡›› ሲልም ኢትዮጵያውያን ዘንድ ከብሄር ድንበር ወጥቶ ለኢትዮጵያውያን መቆሙን እምነት ተጥሎበት ነበር፡፡ በወቅቱ በአማራነታቸው ታሰሩ ያላቸውንም ‹‹የፖለቲካ እስረኞቻችንን በዚህ በዓል ሰሞን እናስታውሳቸው፡፡ ገቢያችን የሚፈቀድልን ደግሞ ለሚወዱት (ለቤተሰቦቻቸው) እጃችንን መዘርጋት ይገባናል›› ሲል በኢትዮጵያውነት መንፈስ ጽፏል፡፡ በእርግጥ እነዚህን ተግባራት በሚያከናውንባቸው ጊዜያት ጃዋር በብሄር ጉዳይ ሰፊ እንቅስቃሴ ያደርግ እንደነበር ይታወቃል፡፡ አሁን ግን ጃዋር ባልታወቀ ምክንያት አቋሙን ቀያይሮ የማይታረቁ ተቃርኖዎች ውስጥ እየገባ ይገኛል፡፡
እንደገና ጠባብ ብሄርተኝነት (ተቃርኖ.1)
የኦሮሞ ህዝብ በኢትዮጵያ በብዛት፣ በኢኮኖሚ፣ በባህልና በሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች ትልቁን ቦታ የሚይዝና የሚያበረክት ህዝብ ነው፡፡ ይህን ጃዋርም በተደጋጋሚ ሲሟገትበት ተስተውላል፡፡ ኦነግ በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቅ ቦታ ያለውን ህዝብ ‹‹መገንጠል›› በሚል የአናሳ ጥያቄ ውስጥ አፍኖ ማግኘት የነበረበትን ስልጣንና ክብር አሳጥቶታል፡፡ ጃዋርም ኦነግ ለኦሮሚያ ህዝብ የሚገባውን እንዳልሰራና ህዝብም ተገቢውን ስልጣን አለማግኘቱን ባገኛቸው መድረኮች ይገልጻል፡፡ ከዚህም ባሻገር ጃዋር በሌሎች ብሄሮች ላይ ተፈጸመ የሚለውን ችግር ‹‹እኛ ኢትዮጵያውያን፣ ኢትዮጵያ አገራችን፣ ወንድሞቻችን›› በሚል በኢትዮጵያዊነት ማዕቀፍ ሲታገል ቆይቷል፡፡ አንድ ሆነን ብሄርን የሚያጋጨውን ስርዓት እናስወግድ፤ በራሳችን ብቻ ታጥረን ሌሎቹ ላይ የሚደርሰውን ችግር ዝም ብለን በማየታችን ችግሩ የሚደርሰው ‹‹እኛው›› ላይ ነው ብሎም ታዋቂውን ጸረ ናዚ አባባል ጠቅሶ መክሯል፡፡ በዚህ ሰናይ አቋሙም በተለያዩ ወቅቶች እንደ አንድነት ያሉ ህብረ ብሄር የአገር ውስጥ ፓርቲዎችና የዲያስፖራው አካላትም እየተጋበዘ ኢትዮጵያውያን በጋራ ችግራቸውን መቅረፍ እንዳለባቸው ትንታኔውንና አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡ ይህም ይበልጡን በኢትጵያውያን ዘንድ እንዲታወቅና ትልቅ ክብር እንዲያገኝ አድርጎታል፡፡
ሆኖም ህዝብን ተጠቃሚ ባለማድረጉ የሚተቸው ኦነግ በተሸነፈበት በአሁኑ ወቅት ብሄር ዘለል ትግል ጀምሮ የነበረው ጃዋርም እንደገና ወደ ኦነጋዊ ጠባብ ብሄርተኝነት ተመልሷል፡፡ በተለይ በቅርቡ ‹‹እኔ በቅድሚያ ኦሮሞነቴን ነው የማስቀደመው›› ብሎ አገራችን፣ ወንድሞቻችን እያለ ሲያነሳው ከነበረው ይልቅ ከኦሮሞ ጉዳይ ትኩረት እንደሚሰጥ ገልጻል፡፡ ምንም እንኳ ይህ የአቋም ለውጥ በጃዋር ያልተጀመረ ቢሆንም ‹‹አንዱን ብሄር ከሌላኛው ብሄር›› በማጋጨት ላይ ተመስርቷ ብሎ ይቀወመው ወደነበረው ያረጀ ያፈጀ ፖለቲካ መመለሱ ትልቅ ቦታ ይሰጡት በነበሩት ኢትዮጵያውያን ዘንድ ቅሬታን ፈጥሯል፡፡
ከኦሮሞነት ወደ ሙስሊም ኦሮሞነት (ተቃርኖ.2)
ጃዋር በኢትዮጵያውነት ማዕቀፍ ከሌሎች ጋር ጀምሮት የነበረውን ትግል ትቶ ‹‹ቅድሚያ›› ለኦሮሞ ማለቱ ያልተጠበቀ ቢሆንም መብቱ ነው ማለት ይቻል ይሆናል፡፡ በዚህ መንሸራተቱ አለመቆሙ ግን ተቃርኖውን ይበልጡን አጠናክሮታል፡ በተለይ አልጀዚራው ‹‹ስትሪም››  በኋላ ጃዋር ከኦሮሞም ወረድ ብሎ ለኦሮሞ ሙስሊም ቅድሚያ እንደሚሰጥ አሳውቋል፡፡ በአንድ መድረክ ባስተላለፈው መልዕክት እሱ የተወለደበት አካባቢ ‹‹99 በመቶው›› ሙስሊም በመሆኑ ቀና ብሎ ለመሄድ የሚሞክር ክርስቲያን ኦሮሞ አንገቱን በሜንጫ እንደሚቆረጥ በኩራት ተናግሯል፡፡ በመሆኑም በኢትዮጵያ ማዕቀፍ አምባገነንነትን መዋጋት አለብን ብሎ ጸረ ናዚውን አባባል ጠቅሶ ሲያስተምር የነበረው ጃዋር ወደ ኦሮም ማዕቀፍ መውረዱ ሳይበቃ አሁን ደግሞ ከኦሮሞነትም ወደ እምነት አጥብቦታል፡፡ ‹‹የተወለድኩበት አካባቢ አንገትክት ቀና ያደረክ ክርስቲያን ኦሮሞ አንገትክን በሜንጫ ትቆረጣለህ›› የሚል ‹‹ጃሃዲስት›› መልዕክት አስተላልፏል፡፡ በዚህም ጃዋር ‹‹የኦሮሞ መብት›› ይከበር ሲል የሙስሊም ኦሮሞዎች መሆኑ እንደሆነ አሳብቆበታል፡፡ ምክንያቱም ሙስሊም ኦሮሞዎች ክርሲቲያን ኦሮሞዎች አንገታቸውን ቀና አድርገው ሲሄዱ ሙስሊሞች በሜንጫ እንዲጨፈጭፏቸው እየሰበከ ለክርስቲያን ለኦሮሞ መብት መቆም ስለማይችል ነው፡፡
……ወደ ኢትዮጵያዊ ሙስሊምነት (የማይታረወቅ ተቃርኖ.3)
ስለ ሌሎች ብሄሮች ችግር፣ ስለ ሁሉም ኢትዮጵያዊነት ሰብአዊ መብት አብረን እንስራ በሚል ወደ ኢትዮጵያዊነት ማዕቀፍ እየገሰገሰ የነበረው ጃዋር ወደ ኦሮሞነት ከዚያም ለክርስቲያን ኦሮሞዎች ርህራሄ የሌለው ሙስሊም ኦሮሞነት ተንደርድሯል፡፡ በዚሁ አቋሙ ሳይወጣ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ለመሆንም ይጥራል፡፡ ኦሮሚያ ውስጥ ያሉት ክርስቲያኖች በሙስሊሙ አንገታቸው እንዲቀላ የሚያበረታታው ጃዋር የጎንደርና የአክሱም ሙስሊሞች ከኦሮሞ ሙስሊሞች ጋር አብረው እንዲሰሩ ሊመክር ሞክሯል፡፡ ከኢትዮጵያውነት ወደ ኦሮሞና ከዚያም ሲጠብ ወደ ኦሮሞ ሙስሊምነት የወረደው ጃዋር የብሄርን ድንበር ጥሶ የእምነት አንድነት ለመፍጠር ሲፍጨረጨር የማይታረቅ ሌላ ተቃርኖ ውስጥ መግባቱን የተረዳ አይመስልም፡፡
የዚህ ተቃርኖ በሁለት መንገድ የሚታይ ነው፡፡ አንደኛው ወደ ጠባብ የኦሮሞ ሙስሊምነት የተንደረደረው ጃዋር በብሄር ለማይመስሉት የትግራይና አማራ ሙስሊሞች መጨነቁ ነው፡፡ ሌላኛው ደግሞ እምነትና ብሄር አብረው የማይሄዱና የሚጋጩ ማንነቶች መሆናቸው ነው፡፡ የብሄር ደንበር የማይወስነው የእምነት ማንነት መገንባት ከተፈለገ ‹‹እኔ ቅድሚያ ኦሮሞ ነኝ፣ አማራ፣ ጉራጌ…›› ማለት አያስፈልገውም፡፡ ቅድሚያ ሙስሊም አሊያም ክርስቲያን መሆን ነው የሚችለው፡፡ ይህ ከሆነ ጃዋር በቅርቡ ‹‹እኔ ቅድሚያ ኦሮሞ ነኝ›› ያለው ማንነቱ ያበቃለታል ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ብሄርና እምነት በአገር ማዕቀፍ ሲታዩ የማይጣጣሙ ማንነቶች በመሆናቸው ነው፡፡ ጃዋር መጀመሪያ ሙስሊም ልሁን ካለ አርሲ ውስጥ ከሚገኘው ክርስቲያን ኦሮሞ ይልቅ አክሱምና ጎንደር ከሚገኙት ሙስሊሞች ጋር ዝምድና ይኖረዋል፡፡ በዚህ ወቅት ማንነቱ ኢትዮጵያዊ ነው የሚሆነው፡፡ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም! ሙስሊም ኦሮሞ ነኝ ብሎ ከክርስቲያን ኦሮሞው ይልቅ ሌላውን ሙስሊም ሊያስቀድም አይችልም፡፡ ‹‹ቅድሚያ ኦሮሞ ነኝ!›› ካለ ደግሞ ቀድሞ የሚመጣው የጎንደርና የአክሱሙ ሙስሊም ሳይሆን ኦሮሚያ ውስጥ ያለው ክርስቲያንና ዋቄ ፈታ ኦሮሞ ነው፡፡ ጃዋር ግን በሁለቱ መካከል ሲምታታ ቆይቷል፡፡
ጃዋር ከዚህም ባሻገር ኦሮሞ ማለት ሙስሊም ማለት ነው በሚል ሌላ የተምታታ ትርጓሜ ውስጥም ገብቷል፡፡ ኦነግና አንዳንዴ የዚሁን ተሸናፊ ፓርቲ አቋም የሚይዘው ጃዋር ኦሮሚያ ምድር ላይ አልደረሱም የሚሏቸው እነ አጼ ዮሃንስና አጼ ቴዎድሮስ በሰሜን ኢትዮጵያ ሙስሊም ማህበረሰብ ላይ አደረሱ ብሎ የሚያምነውን ጥቃት ኦሮሞን ለመጉዳት መሆኑን ሲገልጽ መታረቅ ወደማይችለው የተቃርኖ አዙሪት ውስጥ አስገብቶታል፡፡ በአንድ ወቅት ሌላኛው ሲጎዳ ዝም ማለት የለብንም በሚል ጸረ ናዚውን አባባል ተቅሶ ሲመክር የነበረው ጃዋር አሁን ወደ ብሄር ከዚያም ወደ እምነት ናዚያዊነት እየወረደ ነው፡፡
ከኦነግነት ወደ ‹‹ጎበናነት›› (ተቃርኖ 4)
ያኔ እንዲህ ሳይምታታበት ጃዋር ኦህዴድን ኦሮሞን የሚያስገዙ አዲሶቹ ‹‹ጎበናዎች›› ብሎ ይተች እንደነበር ይታወቃል፡፡ ያኔ ‹‹ከጎበናዎቹ›› ይልቅ ከእነ አንድነት ጋር በመስራት የበኩሉን አስተዋጽኦም አድርጓል፡፡ እያቆየ ግን ጃዋር ከኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች እየሸሸ አሁን አብሯቸው እየሰራ ከሚገኘው ኢህአዴጎች ጎን መሸጎጥ ጀምሯል፡፡ ጃዋር ‹‹እኔ መጀመሪያ ኦሮሞ ነኝ›› ከሚለው አንስቶ ከህወሓት ጋር እንዲተባበር ያስገደዱት የተለያዩ ምክንያቶችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ አንዱና የመጀመሪያው እሱ ‹‹ቀኝ ጽንፍ›› ብሎ የሚጠራቸው ፓርቲዎች ከሌሎቹ የተሻለ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው ነው፡፡ ጃዋርና አቶ ቡልቻ ይበልጡን መጥበብ የጀመሩት አንድነት አብሮት መሄድ ካልቻለው መድረክ ይልቅ ከሌሎች ህብረ ብሄራዊ ፓርቲዎች ጋር ትብብር ለመፍጠር ፍላጎት እንዳለው በተነገረበት ማግስት ነው፡፡ ሰማያዊና አንድነት በሰላማዊ ሰልፍና በሌሎች መንገዶች ጠንከር ያለ የፖለቲካ እንቅስቀሴ ሲያደርጉ ደግሞ እነ ጃዋር ‹‹የጠላቴ ጠላት›› ብልሹ ፖለቲካ ውስጥ ገቡ፡፡
ዶ/ር መረራ ጉዲያ በአዲሱ መጽሃፋቸው እንደሚገልጹት 97 ላይ ቅንጅት ጠንካራ እንቅስቀሴ ሲያደርግ ህወሓትም ሆነ ኦህዴድ ‹‹የጸረ ነፍጠኛ›› ግንባር ለቋቋም ጥሪ አድርገውላቸው ነበር፡፡ ዶክተሩ ‹‹አልፈልግም!›› ብለው ባይመልሷቸው እሳቸውም በነ ጃዋር ‹‹አዲስ ጎበና›› ሆነውት አርፈው ነበር፡፡ ይህ ለደ/ር መረራ የቀረበ ጥሪ አንድነትና ሰማያዊ ሲጠናከሩ፣ አሊያም ከአቶ መለስ ሞት በኋላ ኦህዴድ እራሱን ሊያጠናክር፣ ወይንም የዲያስፖራውን ጫና ለመቀነስ ጃዋርና የእነ ለንጮው ኦነግም ‹የጸረ ነፍጠኛው›› ጥሪ ደርሷቸዋል፡፡ ይህን ተከትሎም የእነ ለንጮ ለታው ኦነግ በ2007 ዓ/ም ምርጫ ለመድረስ እየተሰናዳ እንደሆነ እየተወራ ነው፡፡ ኦነግ ለ‹‹ጸረ ነፍጠኛ›› ትግሉ ያመቸው ዘንድ አገር ውስጥ የራሱን ጠባብ ሚዲያዎች ማቋቋም ጀምሯል፡፡ ለአብነት ያህል ከወራት በፊት ‹‹ሰፉ›› የተባለች በኦሮምኛና አማርኛ የምትታተም መጽሄት ገበያ ላይ አውሏል፡፡ ለዚህም የተደራዳሪዎቹ የኦህዴድም ሆነ ህወሓት ይሁንታ እንደሚያስፈልግ አጠያያቂ አይደለም፡፡ የመጽሄቷ ዋና አላማም ስለ አሁኑ ዘመን ጭቆናም ሆነ በደል ሳይሆን ‹‹አማራ በኦሮሞ ህዝብ ላይ ያደረሰውን በደል ማጋለጥ ነው››፡፡ ይህ እንግዲህ የድርድሩም ሆነ የኦነግ ስልት አንዱ አካል መሆኑ ነው፡፡ ህወሓትና ኦነግ የሚስማሙበት አላማ!
በእርግጥ ወደ አገር ውስጥ የሚመለሱት የኦነግ አመራሮች ብቻ አይደሉም፡፡ ጃዋር ሊመለስ እንደሚችልም አንዳንድ ጭምጭምታዎች እየተሰሙ ነው፡፡ ኢህአዴግ ከሌሎቹ ተቀናቃኞቹ ይልቅ ለጃዋር ርህራሄ ማሰየቱን ማሳየቱ አንድ ፍንጭ ነው፡፡ እነ አቡበክር፣ እስክንድር፣ ርዕዮት…. በእጃቸው ምንም ሳይገኝ፣ በፍጹም ሰላማዊነታቸው ‹‹አሸባሪ›› ተብለው ሲፈረድባቸውና ፊልም ሲሰራባቸው የሜንጫ ጀብድን ሲያስተምር የታየው ጃዋር ምንም አልተባለም፡፡ ከእሱ ይልቅ ኮፈሌ ውስጥ ለበቅ የያዙ ወጣቶችን ከቦኮሃራም፣ ከታሊባንና አልቃይዳ ጋር እያመሳሰሉ ‹‹አሸባሪዎች›› ብለው ፊልም ሰርተውባቸዋል፡፡
ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ደግሞ ኤሊያስ ክፍሌ ስለ ኤሌክትሪክ ገመድ ማቋረጥ ያወራው ‹‹የአሸባሪዎች ማንነት ማሳያ!›› ተደርጎ ሊቀርብ ነው፡፡ በምን መመዘኛ የኤሌክትሪክ መስመር መቁረጥ የሰው አንገት በሜንጫ ከመቁረጥ በልጦ ‹‹ሽብር›› ሊሆን ይችላል? የጃዋርን ‹‹ጀብድ›› እነ ዶ/ር መረራ፣ ዶ/ር ብርሃኑ፣ የኢሳት ጋዜጠኞች፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ አንዱዓለም አራጌ፣ በቀለ ገርባ….አውርተውት ቢሆን ኖሮ ስንት ፊልም ይሰራበት ነበር?  ኢህአዴግ ይህንን የጃዋር ጀብድ አሁን ባይጠቀምበትም መቼም አይጠቀምበትም ማለት አይደለም፡፡ ሌሎች እሱ ከእኛ በላይ የሚያውቃቸውንም ሚስጥሮች እንደተደራደረባቸው ሁሉ ወደ አብሯቸው እየሰራ እንዳያፈነግጥም በልጓምነት ይጠቀሙበታል፡፡ እግረ መንገዱን በርካታ ‹‹ፋኦሎችን›› ያሰሩታል፡፡
በእርግጥ ጃዋር በፖለቲካው ከስሮ ወደ አገር ቤት የገባ የመጀመሪያው ሰው አይደለም፡፡ በርካቶቹ ከእሱ በላይ ‹‹ጀግና›› ተብለው ከህወሓት/ኢህአዴግ ብብት ተሸጉጠዋል፡፡ እነ ሰለሞን ተካልኝ ኤርትራ በርሃ ድረስ ሄደው ‹‹በለው!›› እንዳላሉ ተመልሰው ‹‹ይቀጥል!›› ብለዋል፡፡ ሙዚቀኞች፣ ጋዜጠኞች ፖለቲከኞች፣ የእምነት ‹‹አባቶች›› ብቻ በርካቶች እየከሰሩ ተመልሰዋል፡፡ ሲወናበድ የኖረው ጃዋር ተደራድሮ ቢመለስ የሚገርም አይደለም፡፡
ኢትዮጵያ ለጃዋር አገሩ ናትና መመለሱን የሚጠላ የለም፡፡ ችግሩ በዚህ ስርዓት ምርጫ እንደሌለ ሲናገር እንዳልቆየ ለምርጫ ሊመለስ መሆኑ መነገሩ ነው፡፡ ለኦሮሞ ህዝብ ባለመቆማቸው ኦህዴዶችን ‹‹ጎበናዎች›› እንዳላለ ከህወሓት፣ ብአዴንና ደኢህዴን ስር የሴቶች፣ የትራንስፖርት……ሚኒስቴር ስር ለመስራት ከፈቀደ ነው፡፡

የማይመስል ነገር ለሚስትህ አትንገር! ኢቲቪ ስለ ኢሳት


ቢታኒያ አለማየሁ፣ አዲስ አበባ

ዶክመንታሪ ብሎ ዝም! አስቡት እስኪ ኢሃዲግን በሚያክል አፋኝ መንግስት በኢቲቪ ኢሳት ሲብጠለጠል፣’ኢሳት ማለት የኢትዮጵያ ህይዝብ እውነተኛ የመረጃ ወፍጮ ነው!’Ethiopian Satellite Television (ESAT)

ለምን ግን በዚህ ሰአት ስለ ኢሳት ዶክመንታሪ መስራት አስፈለገ?
-ኢሳት ከተመሰረተ አንስቶ እስካሁን ድረስ በእውነተኛ መረጃ ምንጭነት በመላው የኢትዮጵያ አንጀት ውስጥ ተደላድሎ መቀመጡን ስልሚያውቁ!
-ይከስማል ይጠፋል አቅሙ ይዳከማል ሲሉት እንደ ወይን ጠጅ ከለት እለት እየበሰለና እየጎመራ መምጣቱን ስላዩ!
-በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ተምልካቾች ለኢሳት በመደወል በሚሰጡት አስተያየት ህዝቡ በሚገባ እየተከታተለው መሆኑን ስላረጋገጡ!
-ከዚህ ቀደም ከሰባት ጊዜ በላይ ጃም በማደርግ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ኢሳት ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርገውን ስርጭት ቢያቛርጡም ኢሳት ግን የተለያዩ የሳተላይት አማራጮችን በመጠቀም ከአንድ አመት በላይ(እስካሁን) ያለ ምንም ችግር ወደ ኢትዮጵያ ማሰራጨ ስለቻለና አሁን ካለው የኢኮኖሚ ሁኔታ አንጻር ጃም ማድረግ ከፍተኛ ወጪ ስለሚጠይቅ!
-ህዝብን አደንቁሮ በኢቲቪ ፕሮፓጋንዳ ብቻ የህዝብን አምሮ ለማደደብ በሚደርገው ጥረት ኢሳት ነጻ ሃሳብ በማነሸራሸር እንቅፋት ስለሆነ!
ባጠቃላይ ኢሳት ለህዝብ እውነትን በመግለጽ ለስረአቱ የእግር እሳት መሆኑ ስለታመነበት:- የኢሳትን ይዘት ተንትኖ እና እውነቱ ይህ ሆኖ ሳለ ኢሳት ግን እንዲህ ይላል በሚል አመክኖዋዊ አስተሳሰብ ከመሞገት ይልቅ፣ ግንቦት ሰባት አሸባሪነው ኢሳት ደግሞ የግንቦት ሰባት ነው ስለዚህ ኢሳት አሸባሪ ነው ብለው ከደመደሙ በኋላ ህዝቡ አሳትን መከታተል እንደ ሽብርትኛነት አድርጎ ቆጥሮት መከታተሉን እንዲያቆም ለማግባባት ቀጥሎም ለማስገደድ ያመች ዘንድ የተሰራ ድራማ ነው! የዘፈን ዳር ዳሩ እስክሳ ነው ትል ነበር አያቴ! የሚገርመው ግን አቶ ሃይለማሪያም እንዳሉት “ግንቦት ሰባት በቅዠትላይ የተመሰረተ ድርጅት” ከሆነ ይህን ያክል ተከታታይ ድራማዎች በመስራት ምን አደከማቸው? በራሱ ጊዜ ከእንቅሉ ይባንንላቸው የለም እንዴ?
እናንት አሸባሪ ኢሳቶች ሆይ ህዝብን እልል እያስባላችሁ አንባገነኖችን እያሸበራችሁ ነውና በርቱ! በርቱ! በርቱ!
ቢታኒያ አለማየሁ

አይ ስብሐት ነጋ! (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)


ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
Prof. Mesfin Woldemariam
Prof. Mesfin Woldemariam
በኢትዮጵያ ውስጥ ሥልጣን ሳይኖረው ባለሙሉ ሥልጣን፣ እውቀት ሳይኖረው ባለሙሉ እውቀት የሆነ ሰው ስብሐት ነጋ ብቻ ነው፤ እንዲያውም ከዚያም አልፎ ራሱን የቻለ ሉዓላዊ ነጻነት ያለው ግለሰብ ነው ለማለት የሚቻል ይመስለኛል፤ በዚህ ግለሰብ ላይ የማደንቃቸው ሁለት ነገሮች ናቸው፤ በሉዓላዊነቱ የተጎናጸፈውን ሥልጣን ሙሉ በሙሉ ይጠቀምበታል፤ ይቆጣኛል ወይም ይቀጣኛል ብሎ የሚፈራው የለም፤ ስብሐት ነጋ የሚፈራው ምንም ነገር የለም፤ ሁለተኛ በሉዓላዊነቱ ያለውን ሙሉ ነጻነት በሙሉ ልብ ይጠቀምበታል፤ ናስ በላይ ከበደ እንዳለው ‹‹የቅብጠት መዘላበድ›› ሊሆን ይችላል፤ ስብሐት ነጋ የተናገረው ነገር ትክክል ይሁን አይሁን ጉዳዩ አይደለም፤ ዋናው ነገር መናገሩ ነው።
በቅርቡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከጋዜጠኛነት ተማሪዎች ጋር ባደረገው ውይይት ላይ ሁለት ሰዎች ጽፈው አይቻለሁ፤ ዶር. በድሉ ዋቅጅራ በፋክት ላይ፣ ናስ በላይ አበበ በኢትዮ-ምኅዳር ላይ፤ ሁለቱም ሰዎች አልወደዱለትም ማለት ያንሳል፤ የሚወዱለትና የሚያጨበጭቡለት መኖራቸውም ሳይታለም የተፈታ ነው፤ ነገር ግን ስብሐት ነጋም ሆነ ደጋፊዎቹ አደባባይ ወጥተው ለመከራከር አይችሉም፤ ናስ በላይ አበበ እንደሚነግረን ‹‹አቶ ስብሐት ነጋ የውጭ ሰው እንዳይገባ ከተማሪዎቹ ጋር ተደራድረው ነበር የመጡት፤ ስለሆነም ነበር ከፍተኛ ጥበቃ አልፈን የገባነው፤›› ብቻውን ተናግሮ በጭብጨባ የሚሸኝበት መድረክ በመፈለጉ በከባድ ጥያቄም ቢሆን የሚያጣድፉት ሰዎች እንዳይኖሩ ማረጋገጡ በተማሪዎቹም ቢሆን ውሎ አድሮ ትዝብት ላይ ይጥለዋል።TPLF power broker, Sibehat Nega
ዶር. በድሉ ዋቅጂራ ስለስብሐት ነጋ ከኢትዮጵያዊነት መውደቅ በሚል በጻፈው ላይ ዶር. ዳኛቸውን እንደሚከተለው ይጠቅሳል፤ ‹‹ከኢትዮጵያዊነት መውደቅ ማለት፤ በቃ በአጭሩ (ኢትዮጵያዊ ሆኖ) ኢትዮጵያዊ አለመሆን ነው፤›› በቅንፍ ውስጥ ያለው የኔ ነው፤ ልክ ነው፤ አንድ ግለሰብ በማናቸውም ምክንያት ከኢትዮጵያዊነት ቢወድቅ ኢትዮጵያዊነቱ የከሸፈ ነው ለማለት ይቻላል፤ ነገር ግን ከኢትዮጵያዊነት መውደቅንና ኢትዮጵያዊነትን መጣልን ለይተን ማየት ያስፈልጋል፤ አንድ ሰው በማናቸውም ምክንያት ከፍተኛውን የኢትዮጰያዊነት ባሕርይና ግዴታ መሸከም አቅቶት ቢወድቅ ለዚያ ሰው ኢትዮጵያዊነቱ ከሸፈ፤ ለስብሐት ነጋና ለጓደኞቹ ከከሸፈባቸው የቆየ ይመስለኛል፤ ከራሱ አልፎ የሌሎችን ኢትዮጵያዊነት ለማክሸፍ የሚሞክር ደሞ ከመክሸፍ አልፎአል፤ ከኢትዮጵያዊነት መውደቅ ማለት የከሸፈ ኢትዮጵያዊነት ነው ማለት ነው።
ስብሐት ነጋ ዋና ዓላማው በሙሉ ነጻነት የመጣለትን እንደመጣለት መናገር ነው፤ ምሳሌዎችን እንጥቀስ፤– ሀ) ‹‹ከኢትዮጵያ ሕዝብ በላይ የኤርትራ ሕዝብ ኢትዮጵያዊነት አለው፤›› ስብሐት ነጋ ስለኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ስለኤርትራ ሕዝብ፣ ስለኢትዮጵያዊነት ያለው እውቀት የሚባል ነገር እንዲህ ያለው መዘባረቅ ነው፤ ስብሐት ነጋ ጨረቃ ከጸሐይ የበለጠ ትሞቃለች ቢልም አይደንቀኝም፤ አልከራከረውም፤ ስብሐት ነጋም ብቻውን መናገር እንጂ መከራከር አይፈልግም፤ ለ) ‹‹የኢትዮጵያ ሕዝብ ከኤርትራ ሕዝብ የበለጠ የኤርትራን መሬት ይፈልጋል፤›› እንደምሳሌ ያነሣው አሰብን ነው፤ ባድመን አላነሣም!  እሱና ጓደኞቹ የኢትዮጵያን ወጣቶች በከሸፈ ጦርነት ውስጥ የማገዱት ባድመ ለሚባል መንደር ነው እንጂ አሰብ ለሚባል ወደብ አልነበረም፤ በዚያን ጊዜ ጦርነቱን በመቃወም ድምጼን ያሰማሁት ኢትዮጵያዊ ወይም ኤርትራዊ ሆኜ አልነበረም፤ ሰው ሆኜ ነው፤ ዛሬ ስብሐት ነጋ ሲዘላብድ ኢትዮጵያዊነት የማይታይበትን ያህል ኤርትራዊነትም አይታይበትም፤ በዚህም ጉዳይ ላይ መከራከር አይፈልግም፤ ሐ) ‹‹ለማንኛውም ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ መከልከላቸው የማውቀው ብዙ ነገር የለኝም፤ ይከልከሉም አልልም፤ አይከልከሉም አልልም፤ መብታቸው ነው፤›› ይህ መዘላበድ ካልሆነ ምንድን ነው? ምን ቁም-ነገር ይዞ ነው ይህንን የተናገረው? የገለባ ክምር ውስጥ አንድ ፍሬ መፈለግ ይቀላል።
አንድ ሌላ የስብሐት ነጋ ዘዴ (ዘዴ ካልነው!) ጉዳዩን በሚገባ ሳያጣራ እንደመጣለት ይናገርና ‹‹አላውቅም›› ይላል! የማያውቀውን መዘባረቅ ግን ይችላል፤ ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹የምን ፓርቲ እንደሆነ አይታወቅም፤ የእስላም ፓርቲ ነው?›› ስብሐት ነጋ እውቀትን የሚሻ ቢሆን ለፓርቲዎች እውቅናን የሚሰጠውን መሥሪያ ቤት ያውቀዋል፤ ለምን ብሎ ይጠይቅ? ለምን ብሎ እውነቱን በማወቅ ይታሰር? ትክክለኛ መረጃ ባለማወቅ እንደልብ የመናገርን ነጻነት ይገድባልና ‹‹አላውቅም›› ማለት ለመዘላበድ ይጠቅማል፤ ምንም እንኳን የሰላዮች ሠራዊት እንዳለው ብናውቅም ስለእስላሞችና ስለሰማያዊ ፓርቲ የተናገረውን እንደፖሊቲካ ከወሰደው ደረጃውን ከማሳየት አያልፍም፤ ሰማያዊ ፓርቲን በሁሉም ዘንድ ለማስጠላት የሚከተለውን ይላል፤ ‹‹እስላሞች ወንድሞቻችን የሚሉት ደግሞ የት ያውቁናል? ሲቀጠቅጡን የነበሩ፤ ተራ ሕዝቡም አይወዳቸውም፤›› የጤፍ ቅንጣት የምታህል የማሰብ ተግባር ቢኖርበት ስብሐት የተናገረው ያልተጠረነፉትን እስላሞች በሙሉ የሰማያዊ ፓርቲ ደጋፊ የሚያደርግ መሆኑን መረዳት ይችል ነበር።
ስብሐት ነጋ አንድ መቶ ሃያ ዓመታት ያህል ወደኋላ ቢሄድ ኤርትራ የሚባል አገር አያገኝም፤ በዚያ መሬት ያሉ ሰዎች ላላቸው ወይም ለሌላቸው የኢትዮጵያዊነት ስሜት የስብሐት ነጋን ምስክርነት እንደማይፈልጉ በጣም እርግጠኛ ሆኖ መናገር ይቻላል፤ ለሌሎቻችን ኢትዮጵያዊነትም ቢሆን የስብሐት ነጋ ምስክርነት አያሻንም፤ አሰብን አንሥቶ ብዙ ወጣቶች ያለቁበትን ባድመን ሳያነሣ መቅረቱ በአንድ በኩል፣ አሰብንም ሆነ ባድመን ከሚፈልጉ ወገኖች መሀል እሱ መውጣቱን በጣም ግልጽ አደረገ፤ ወዴት እንደገባ ግን ገና አልነገረንም!!!

The paradox in the Ethiopian Economy


by Mastewal Dessalew
It is a cliche from the Ethiopian government that the Ethiopian Economy has recorded a double digit growth in the past eight or nine years. Though there are many who questions the rate, the government is adamant to accept a rate less than double digit. It asserts its argument by citing the construction of roads, hydroelectric dams and sky scrapers in big cities as indicators of fast economic growth in the country. On the other hand, unbridled inflation is deteriorating the real income and the purchasing power of the people in the same period; for example according to index mundi inflation rate in the country in the past decade was increasing and in its climax it was 25 percent in 2008 and 36 percent in 2009. Why the living standard of the people is deteriorating amidst the presence of fast economic growth? The defunct Prime Minister Meles was asked this question 7 years ago and he responded “the inflation is caused by the economic growth itself and the growth itself will solve the problem in the long run”. Yet after seven years, the problem is getting worse than showing improvement. Thus, why the problem persists? Even though the problem has different sources, it can be broadly categorized in to two: first, the source of the economic growth and second the economic and political structure of the country.Ethiopia: Guerilla Economics - Hard to Understand
In short economic growth means creating additional wealth in the economy. If we closely scrutinize the additional wealth created in Ethiopia, it is mainly roads, hydroelectric dams and buildings in cities. On the other hand, if we see the source of the funding of this projects, it is mainly either from foreign aid, loan and printing of currency. Following the emergence of Islamic courts union in Somalia in 2006 and its heir Alshabab since then, Ethiopia has garnered billions of dollar every year from the west by making itself a strategic partner in the fight against terrorism. The influx of such huge amount of money to the Ethiopian economy could not bring significant structural change in the industry and agricultural sector of the economy, instead it lead to the bulging of the service sector. Lack of significant change in the industry and agricultural sector of the country while enormous amount of money is injected in the economy resulted in high inflation. The national bank of Ethiopia is also criticized for fueling the inflation by recklessly printing currency to finance projects.
Even though the money spent to finance infrastructural projects has brought inflation, it has also helped to decrease the cost of production and transportation cost by improving the infrastructure. In addition, based on the economic principle of money creates money, the money injected to the economy has created additional wealth mainly in the service sector. Yet the wealth created is not managed by strong political and economic institutes that resulted in most of the wealth to end up in the hand of few. Those few people who are able to amass the wealth do not want to invest it in relatively risky and competitive industry sector rather they create alliance with corrupt officials to easily get expensive urban land for the construction of buildings in urban areas to be used or rented for the burgeoning service sector.
On the other hand, rampant corruption in the urban land administration system of the country is impeding newly emerging potential entrepreneurs not to easily get land for their business. This makes the competition ground for new comers versus established businesses to be highly unleveled and then hinder the emergence of new innovative businesses. In addition, most of those wealthy people and big companies are in one way or another related to the ruling party and they are paying less than the amount of tax they are expected to pay. They are also wary of future political upheaval and change and then prepare for it by depositing their money in foreign banks; corrupt officials also do the same. Here it is worth mentioning that according to financial transparency international coalition Ethiopia had lost 11.7 billion dollar from 2000 to 2009 due to illicit financial flow.
To sum up, if the economy of Ethiopia has to grow healthy, the economic and political institutes that regulate and directly affect its economy shall be improved. Heavy dependence of the country on foreign aid and loan shall also be systematically decreased by offsetting the gap through improving internal revenue collection performance. Part of the money gained from aid and loan shall also be directed to improve the industrial and agricultural sectors side by side with infrastructural expansion. The national bank of Ethiopia shall also act responsibly based on economic principles when it mints currency. Most importantly the ever increasing trend of corruption in the country shall be halted by strengthening transparency and accountability through transition to multi-party system as well as establishing independent judiciary and mass media.
The writer can be reached at mast.dess@gmail.com

Ethiopia: Dark side of Oromo expansions and Menelik Conquests


by Abera Tola
Through out history; people have migrated and expanded seeking greener pastures and more land. Globally, most countries have endured and were created thru expansions, wars, assimilation, migration; slavery etc. Even the most developed countries in the world today have dark pasts. For example; millions of Native Americans were exterminated or removed from their homelands while millions more African-Americans underwent the most cruel slavery in world history before the great democracy; the USA; was born. If not for the gradual improvement of human rights in America and its military superiority triggering an economic powerhouse; United States would have been just another poor country facing fragmentation and internal division due to its dark history of conquest and slavery. While Ethiopia did not have as much a bloody history as America; it did experience some conflicts and small level of slavery. Considering how extremely diverse Ethiopia is ethnically, linguistically, politically and religiously, Ethiopia still has been a relatively peaceful country. And that has been one reason why, despite all its problems, its citizens are proud. Case in point: how many poor countries with over ninety native languages and a near 50/50 Islam/Christian population have managed to co-exist or live in relative peace for over thousand years? Not many. But still, Ethiopia has had its share of problems as well. As an Oromo; the two most violent and most important events that impacted my people are the Oromo expansion in the 1500s and the Shewan Menelik expansion of the 1880s. These two events represent the two stages of Ethiopia’s ethnolinguistic evolution.
Stage one: Oromo expansion
After the 1540s; the ethnolinguistic and political shape of the horn of Africa changed forever when the Oromo expanded north into territories dominated by the Amharic speaking people of Abyssinia/Ethiopia as well as the Sidama and the Adal kingdoms. Historians credit our unique Gadaa system for being suitable for warfare and for the successful conquest of present day central; west and eastern Ethiopia by the Oromo. According to Oromo oral accounts and historical records; the Oromo expansion into Abyssinia was disorganized but Oromo raids and attacks of the neighboring people lasted for many decades; leading to the killing of tens of thousands of Amharic speaking people. The powerful Oromo benefitted from its large population and better developed battle strategy. The Oromo expansions were also similar to that of the Ottoman Empire expansion because they both did not always change the religion of their new subjects. With the only exception of the Yejju Oromo imposing Afan Oromo on Amharas in Gondar; the Oromos also never enforced their language on other people. Nonetheless; many Somali, Amharic and Sidama speaking peoples became “tax-paying serfs” for the new Oromo rulers. And having already been weakened by the Adal/Somali conquest of southern Abyssinia; the Amharic & Tigrayan speaking population of Abyssinia lost more lands to the Oromo; including the Shawa and Dawaro regions (Arsi area) that have been Abyssinian territories since the days of their ancient Aksum empire. Today; the descendants of these Oromo settlers makeup the dominant population in Shewa and Arsi. Not only the eastern and southern edges of the Abyssinian highlands but; gradually; even some northern pockets of Abyssinia got conquered by Oromo warlords: which explains why small Oromo communities can still be found as far north as Tigray even today. Thus; in the late 1500s; having lost substantial territories to the Oromo; the Solomonic Dynasty/Abyssinia declined in power for decades. But that century also started the transformation of Abyssinia into a more multi-ethnic entity: one that was forced to incorporate Oromo as one of its citizens.
Stage Two: Menelik/Shewan expansion
Another significant event that greatly impacted the ethnic and political situation in Ethiopia and the region was the Shewan/Abyssinian expansion led by Emperor Menelik II during the late 1800s. Just like the Oromo expansion; the Abyssinian expansion was disorganized since many parts of Abyssinia were in conflict amongst each other. The Shewan part of Abyssinia have been in various small battles against Gondar and Gojjam parts. However; using relatively modern weapons purchased from European countries; the Shewan Abyssinians defeated other Abyssinian regions and then they continued on to re-conquer Oromo territories that were settled by the Oromos since the 1500s. Proportionally; about the same percentage of people might have perished during the Shewan expansion (stage 2) compared to the Oromo expansion (stage 1). However; seen in raw figures; many thousands more were killed during the bloody conquests by Menelik’s Shewan army. As the sign of the times, not many international laws of war exists to stop the atrocities during these wars, or for that matter during any wars around the globe. Yet one undeniable key fact of this war was that the Shewan army was ethnically diverse, even if Amharas were the militarily dominant group in it. Because Oromos settled in Shewa since their 1500s expansion; Shewa was already a melting pot of Amhara and Oromo by the late 1800s. Therefore; the multi-ethnic Shewan army of Emperor Menelik was able to easily defeat various Oromo and southern areas of present day Ethiopia.
Both of these historical events of the 1500s and the 1800s shaped the ethnolinguistic identity of the new Ethiopia.
Conclusion
The most glaring difference between the two events is that one happened in a recent memory and thus it influences the current politics of the region more powerfully. Otherwise; both events are dark and equally violent parts of our history. De-emphasizing or ignoring one event over the other only creates confusion and bitterness among the new generation. An Oromo should not ignore “stage one” and only talk about “stage two.” Similarly; an Amhara should not ignore “stage two” and only talk about “stage one.” The blame game by bringing a biased version of the past only poisons the present. No one side should play the victim game or live in the past, instead of working for a better future; otherwise everyone will fall together.
References
-US Library of Congress Country study: Ethiopia history
- Pankhurst; Richard K.P. The Ethiopian Borderlands: Essays in Regional History from Ancient Times to the End of the 18th Century. The Red Sea Press; Asmara.
- Oromo Oral history