Friday, August 30, 2013

ምስጢር ያልሆኑ ምስጢራት” ‑ ድንበር ተሻጋሪው የኢሕአዴግ ዕኩይ ፕሮፖጋንዳ


ከኢትዮጵያዊ ሙስሊም
እዚህ አሜሪካ ከዋሽንግተን ዲሲ ከተማ የሚሰራጨው የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ራዲዮ ጣቢያ በቅርቡ የሙስሊም ኢትዮጵያውያን የሃይማኖት ነፃነትና መብትን የማስከበር ሰላማዊ ትግልን ከ‹ፖለቲካዊ እስልምና› ጋር ለማያያዝ የሚቃጣ “የራዲዮ ዝግጅት” አቅርቧል፡፡ ዝግጅቱ ዊኪሊክስ በተሰኘው ድረ‑ገፅ አምና ይፋ የተደረጉ የስቴት ዲፓርትመንት ምሥጢራዊ ሰነዶችንና ከጥቂት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ከተከሰቱ ግጭቶች ጋር የተያያዙ የድምፅ ግብዓቶችን በመጠቀም ወቅታዊውን የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሃይማኖት ነፃነትን የማስከበር ሰላማዊ ትግል ከ‹ፖለቲካዊ እስልምና› ጋር በማያያዝ ጭቃ ለመቀባት፣ ብሎም ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖችን ግንዛቤ ለማዛባት ይሞክራል፡፡
ይህ ጽሑፍ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን እየተነዛና እየተሰበከ ባለው ጥላቻና ግጭትን የመቀስቀስ ዓላማ ያዘለ ፕሮፖጋንዳ አኳያ፣ ወቅታዊውን የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሃይማኖት ነፃነትን የማስከበር ሰላማዊ ትግል በአጭሩ በማስቃኘትና፣ በአሁኑ ወቅት መንግሥትና አጫፋሪዎቹ እያካሄዱ ያሉትን ህዝብን ከህዝብ ለማጋጨት ያለመ ዕኩይ ዘመቻ አደገኛነት በማመላከት ዓላማ የተዘጋጀ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ራዲዮ ያቀረበውን ዝግጅት አሉታዊነት በድፍኑ ከመተቸት ይልቅ፣ በዝግጅቱ ይዘት ላይ ያተኮረ ሰፋ ያለ ሒስ ማቅረብ አስፈላጊ ይመስለናል፡፡ እናም በዚህ ጽሑፍ የራዲዮ ጣቢያው ባቀረበው ዝግጅት ይዘት ጥቂት አንኳር ጉዳዮች ላይ በማተኮር የጣብያውን አሳዛኝና አሳፋሪ ሥራ ለማስቃኘት እንሞክራለን፡፡
ምሥጢራዊ ሰነዶችና ይፋ የመውጣታቸው ፖለቲካዊ አንድምታ
የዳያስፖራው ራዲዮ “በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እስልምና እየተስፋፋ ነው” የሚል ክስ ያቀርባል፡፡ ለዚህ ክሱ ካቀረባቸው ማስረጃዎች መካከል ‹ዊኪሊክስ› የተሰኘው የዊሊያም አሳንጅ ድረ‑ገፅ ይፋ ያደረጋቸውን ከስቴት ዲፓርትመንት ያፈተለኩ ምሥጢራዊ ሰነዶች ይገኙበታል፡፡ እንደ ማስረጃ በተጠቀሱት ‹ዊኪሊክስ› ይፋ ያደረጋቸው ሰነዶች ይዘት ላይ ከማተታችን በፊት ግን፣ የእነዚህ ሰነዶች ከስቴት ዲፓርትመንት ዳታቤዝ ተሠርቆ በ‹ዊኪሊክስ› ድረ‑ገፅ ይፋ የመደረጉን ፖለቲካዊ አንድምታዎች መመልከት ተገቢ ይመስለናል፡፡
እንደሚታወቀው፣ ማንኛውም መንግሥት በ“ጥብቅ ምስጢር”ነት የሚይዛቸው ጉዳዮች ይኖሩታል፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰነዶች “ጥብቅ ምስጢር” (CLASSIFIED) በሚል ተፈርጀው በጥንቃቄ ይቀመጣሉ፡፡ በመንግሥት ሥራ ላይ አንድን ጉዳይ “ጥብቅ ምስጢር” የሚያደርጉ ተቀባይነት ያላቸው ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ በሌላ በኩል አንዳንድ ጉዳዮች/ሰነዶች በ“ጥብቅ ምስጢር”ነት የሚይያዙት ይፋ ቢሆኑ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተቃውሞን ሊያስነሱ፣ ጠንካራ ትችትና ውግዘት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ ስለሚታወቅ ነው፡፡ በ“ጥብቅ ምስጢር”ነት የሚያዙ ጉዳዮች/ሰነዶች ይፋ መውጣት ብሄራዊ እና/ወይም ዓለምአቀፍ ሕግን መሠረት ያደረገ ተጠያቂነትን ሊያስከትል፣ ወይም ደግሞ እንደ ይዘቱ በአገራት ግንኙነት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊያሳድር ይችላል፡፡ ከጉዳዩ ጋር ተያያዥ የሆኑ ኦፊሴላዊ የ“ጥብቅ ምስጢር” ሰነዶች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ጋር ከደረሱ፣ እንደሁኔታው በምሥጢር ሊካሄዱ የታቀዱ መርኃ‑ግብሮችን ሊያሰናክሉም ይችላሉ፡፡
በብዙ አጋጣሚዎች መንግሥታት፣ ይበልጡኑም በከፍተኛ የሥልጣን እርከን ላይ ያሉ ፖለቲከኞች ዕውን ሊያደርጉ የሚሹትና በአደባባይ ለህዝብ የሚናገሩት ፍፁም ለየቅል ሊሆን ይችላል፡፡ በእንዲህ ዓይነት ጉዳዮች ላይ የአንድን መንግሥት ተግባራት እውነተኛ መግፍዔ (Motive) ለማወቅ፣ አልያም የቅርብ ግምት ለመስጠት የሚቻለው በጥልቅ ፖለቲካዊ ትንተና ነው፡፡ … በዓለምአቀፍ የቴሌቪዥን ኔትወርኮች ዘወትር እንደምናየው፣ የአንድን መንግሥት እርምጃዎች፣ ውሳኔዎች ወይ የአቋም ለውጦች ከተለያዩ ማዕዘናት በመዳሰስ በይፋ ያልተነገሩ ብዙ መረጃዎችን የሚሰጡት የፖለቲካ ተንታኞች ናቸው፡፡ ግና ከጉዳዩ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው በ“ጥብቅ ምስጢር”ነት የተያዘ የመንግሥት ሰነድ ድንገት ሾልኮ ቢወጣስ? ይህ ሲሆን፣ የፖለቲካ ተንታኙን የዙርያ‑ገብ ትንተና ድካም በመቀነስ፣ በቀላሉ ወደ እውነተኛው የጉዳዩ ምንነት ያደርሳል፡፡ በ“ጥብቅ ምስጢር”ነት የተያዘ የመንግሥት ሰነድ ይፋ መውጣት እንደ ጉዳዩ የክብደት ደረጃ አንድን መንግሥት በከፍተኛ ኃፍረት አልያም ቅሌት ውስጥ ሊከተውም ይችላል፡፡
በዚህ ማዕቀፍ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ራዲዮ ጣቢያ ባቀረበው ዝግጅት በስፋት ያጣቀሳቸውን በ‹ዊኪሊክስ› ይፋ የተደረጉ የስቴት ዲፓርትመንት “ምስጢራዊ ሰነዶች” በምን መልኩ ለዕኩይ ዓላማ እንደዋሉ ስናይ በጣም እንገረማለን፡፡ … እናዝናለንም፡፡
ዊኪሊክስማንን እና ምንን ነው ያጋለጠው?
በመሠረቱ፣ ዊኪሊክስ ይፋ ያደረጋቸው የስቴት ዲፓርትመንት “ምሥጢራዊ ሰነዶች” በአሁኑ ወቅት ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እያካሄዱ ከሚገኙት ሕገ‑መንግሥታዊ የሃይማኖት ነፃነትን የማስከበር ትግል ጋር ምንም ዓይነት ቀጥተኛ ግንኙነት የላቸውም፡፡ በአንጻሩ ግን “ምሥጢራዊ ሰነዶቹ” የኢሕአዴግ መንግሥት ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሃይማኖት ነፃነት ላይ የከፈተው ግብታዊነት የሚታይበት “የጥሰት ዘመቻ”፣ የአሜሪካ መንግሥት “አሳስቦኛል” ከሚለው አንድ ጉዳይ ጋር ተያያዥነት ሳይኖረው እንዳልቀረ ይጠቁማሉ፡፡ ሰነዶቹ ከምንም በላይ ዛሬ የኢሕአዴግ መንግሥት ከህዝበ‑ሙስሊሙ ጋር የተፋጠጠበት ጉዳይ፣ በኢትዮጵያዊ ዓይን የታየ ሳይሆን፣ በአሜሪካ መንግሥት ዓይን የታየ፣ በአሜሪካዊኛ የተተነተነ፣ በአሜሪካ ልዩ ፍላጎት ላይ ተመሥርቶ የተቃኘ መሆኑን ነው በግልፅ የሚያሳዩት፡፡ … ይህ ሆኖ ሳለ፣ የዳያስፖራ ራዲዮ ጣቢያ፣ የአሜሪካ መንግሥት በራሱ ምክንያት ምሥጢር አድርጎ ሊይዝ ይፈልገው የነበረውን ይህን ሰነድ በማጣቀስ፣ ወቅታዊውን የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሃይማኖት መብትን የማስከበር ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማጠልሸት ዓላማ አውሎታል፡፡ ይህ በአንድ በኩል በጣም የሚያስቅና የጣቢያውን ብስለት-የለሽነት የሚያሳይ ሲኾን፣ በሌላ በኩል ሙስሊም ኢትዮጵያውያን የፍትኅና የነፃነት ተሟጋቾች (አክቲቪስቶች) ከአንድ ዓመት በፊት በፌስቡክ ላይ እንደነገሩ ነካክተው ያለፉትን ነገር ዛሬ ጠበቅ አድርገን እንድንመለስበት የጋበዘ በመሆኑ የሚመሰገን ነው፡፡
እስከምናውቀው ድረስ፣ ዊኪሊክስ ይፋ ያደረጋቸው አዲስ አበባ ከሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ወደ ስቴት ዲፓርትመንት የተላለፉ “ምሥጢራዊ ሰነዶች” በቁጥር ሦስት ሲኾኑ፣ ሦስቱም እ.አ.አ በኦገስት 2009 (በኢት. አቆጣጠር በነሐሤ 2001) የተዘጋጁ ናቸው፡፡ እነዚህ ሰነዶች፣ የኢሕአዴግ መንግሥት በኢት. አቆጣጠር በሐምሌ 2003 በይፋ የጀመረው የአህባሽ አስተምህሮን በህዝበ‑ሙስሊሙ ላይ የመጫን መርኃ‑ግብር፣ ከዚያ ሁለት ዓመታት ቀደም ብሎ የአሜሪካ መንግሥት በዊኪሊክስ ላይ ባንፀባረቀው በጥልቀት ያልተተነተነ ስጋት ላይ የተመሠረተ መሆኑን ነው ያጋለጡት፡፡ … እነዚህ “ምሥጢራዊ” የነበሩ ሰነዶች በይዘታቸው በአሁኑ ወቅት የኢህአዴግ መንግሥት በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ እያካሄደ የሚገኘው የአገሪቱን ሕገ‑መንግሥት የሚጻረር (የሃይማኖት ነፃነትን የመገደብ) መርኃ‑ግብር በእውነትና በእውቀት ላይ የተመሠረተ ከመሆን ይልቅ፣ የአሜሪካ መንግሥት ከራሱ ዕይታ ያንፀባረቀው፣ ኢሕአዴግ በጥልቀት ሳያጠናውና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ሙስሊም ዜጎቹ (ቢያንስ ከሚያምናቸው ሙስሊም ምሁራን) ጋር ሳይማከርበት ዓይኑን ጨፍኖ በግብታዊነት ሊያስፈጽም የተቀበለው የቤት ሥራ መሆኑን ነው በግልፅ የሚያሳዩት፡፡ ዊኪሊክስ ምሥጢራዊ ሰነዱን ይፋ ባያደርግ ኖሮ፣ የአሜሪካ መንግሥት እ.አ.አ እስከ 2019 (በኢት. አቆጣጠር እስከ ነሐሤ 2011) ድረስ ይህንን ሐቅ በምሥጢር ሊይዘው ነበር የፈለገው፡፡ ምናልባት ሰነዱን ምሥጢር ማድረግ የተፈለገው ተግባሩ በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ እንደመግባት ሊቆጠር ይችላል ከሚል ስጋት በመነጨ ሊሆን ይችላል፡፡
የኢትዮጵያ ዳያስፖራው ራዲዮ “እኛ” በተሰኘ ፕሮግራሙ፣ በዊኪሊክስ ይፋ በመደረጋቸው የአሜሪካ መንግሥትና ኢሕአዴግ የተጋለጡባቸውን እኒህኑ በምሥጢር ተይዘው የነበሩ ሰነዶች ዋቢ በማድረግ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በሃይማኖታዊ ነፃነታቸው ላይ የተቃጣውን ጥሰት በመቃወም የሚያካሂዱትን ሰላማዊ ትግል ሊያጠለሽ ይሟሟታል፡፡ የራዲዮ ጣቢያው ዝግጅት ከአገረ‑አሜሪካ ለሚገኝ ዳረጎት ሲሉ የ“አክራሪነት”ን ነጋሪት እየጎሰሙ ሙስሊሙን ዜጋ ቁም ስቅል የሚያሳዩት ገዢዎቻችን የተጋለጡበትን “የአደባባይ ምሥጢር” እየተረከ፣ በአገሪቱ ሕገ‑መንግሥት ስለተደነገገው የሃይማኖት ነፃነታቸው መከበር የሚጮሁ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን በ‘ፖለቲካዊ እስልምና’ አስፋፊነት በመወንጀል ሊያሸማቅቅ ይሞክራል፡፡ በሌላም በኩል፣ የሙስሊም ኢትዮጵያውያንን ሕጋዊ፣ ፍትኃዊና ሰላማዊ ጥያቄ ደግፈው የቆሙ ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖቻችንን ግንዛቤ ለማዛባትና የሙስሊም ወገኖቻቸውን ሰላማዊና ሕጋዊ ትግል በጥርጣሬ እንዲመለከቱት ለማድረግ ይተጋል፡፡ በዚህ ብቻ ግን አያበቃም፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት በአገራችን አንድ ክፍል በተከሰተ የማንም አዕምሮ የማይቀበለው ግጭት ላይ የደረሱ ጥፋቶችን፣ ስሜት በሚኮረኩሩ የድምፅ ግብዓቶች አጅቦ በማቅረብ፣ ሙስሊም ያልሆኑ ኢትዮጵያውያን በሙስሊም ወገኖቻቸው ላይ ጥላቻና ጥርጣሬ እንዲያድርባቸው የሚገፋፋ መሠሪ ፕሮፖጋንዳ ይነዛል፡፡ እግረ መንገዱንም፣ ወቅታዊውን የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ሰላማዊ የመብት ትግል ስውር ዓላማ ያለው ለማስመሰል ዳር ዳር ይላል፡፡
በቀድሞው የአሜሪካ አምባሳደር ዶናልድ ያማሞቶ አማካይነት የተዘጋጀውና ዊኪሊክስ ይፋ ያደረገው የመጀመርያው ሰነድ ‹‹GROWING WAHABI INFLUENCE IN ETHIOPIA: AMHARA›› የሚል ርዕስ አለው፡፡ ሰነዱ አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ የህዝብ ጉዳዮች ክፍል (Public Affairs Section) ኃላፊዎች በአማራ ክልል፣ ደሴ አቅራቢያ በሚገኙ የገጠር ወረዳዎች (እ.አ.አ. ከጁን 3‑5፣ 2010) ባካሄዱት የሦስት ቀናት ቅኝት ላይ ተመሥርቶ የተዘጋጀ ነው፡፡ የኤምባሲው ባልደረቦች ይህን ቅኝት ያካሄዱት ከአንድ የዞን መሥተዳድር ኃላፊ ጋር መሆኑም በሰነዱ ላይ ተጠቁሟል፡፡ …
ሰነዱ በአማራ ክልል ‹ወሃቢያ› የተባለው የእስልምና አስተምህሮት እየተስፋፋ መሆኑን፣ በገጠር ከተሞች በርካታ መስጊዶች ከኩዌት መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በተገኘ ፈንድ መታነፃቸውን፣ የኤምባሲው ኃላፊዎች በጎበኟቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ሙስሊም ሴቶች ሃይማኖታዊ አለባበስ በመከተል ፊታቸውን እንደሚሸፍኑ፣ ወንዶች ደግሞ ሱሬያቸውን እንደሚያሳጥሩ፣ ፂማቸውን ግን እንደማያሳድጉ ወዘተ. ይጠቃቅሳል፡፡ በተጨማሪም፣ የወሃቢያ አስተምህሮ የነቢዩ ሙሐመድን ልደት (መውሊድ) ማክበርን ስለሚቃወም፣ በዚህ ረገድ በወሃቢ አስተምህሮና በሱፊ አስተምሀሮ ተከታዮች መካከል፣ በተለይ የሱፊ እስልምና ተከታዮች መውሊድን በሚያከብሩበት የጀማ ንጉስ መስጂድ አካባቢ ከዚያ ቀደም ባለ ጊዜ ሁኔታው ወደ ግጭት አምርቶ እንደነበረ ይገልፃል፡፡ አክሎም የሱፊ እስልምና ተከታዮች የመውሊድ በአልን ለሚያከብሩበት የጀማ ንጉስ መስጂድ እድሳት በማድረግ ባህላዊ ቅርሱን ስለመጠበቅ አስፈላጊነት ያወሳል፡፡ ለዚህም አሜሪካ ከአምባሳደሩ የባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ ፈንድ ድጋፍ የማድረግ ፍላጎት እንዳላት ይጠቁማል፡፡ [http://wikileaks.org/cable/2009/07/09ADDISABABA1672.html#]
ሰነዱ የኤምባሲው የስራ ኃላፊዎች ለሦስት ቀናት ባካሄዱት ቅኝት፣ ከአካባቢው መስተዳድር የሥራ ኃላፊ እንዲሁም ከወቅቱ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) በተገኘ መረጃ ላይ ተመሥርቶ፣ በኢትዮጵያ የወሃቢ አስተምህሮ መስፋፋት ለዘመናት የቆየው የተለያዩ ሃይማኖት ተከታዮች የመቻቻል ዕሴት አደጋ እንደተደቀነበት ይጠቅሳል፡፡ ሰነዱ በገፅ 3 [8.(C)] በዚህ ጉዳይ ላይ ጠቅላይ ምክር ቤቱን ሲጠቅስ እንዲህ ይላል፡‑
the IASC continues to be very concerned about growing Wahabi influence in Ethiopia. The newly appointed Council is decidedly anti-Wahabi and speaks openly of their concern about Wahabi missionaries and their destabilizing influence in Ethiopia.
ሰነዱ በገፅ 4 (13.(C)) ላይ ደግሞ የመጅሊሱን ኃላፊዎች ዋቢ በማድረግ በወቅቱ (እ.አ.አ. በ2010) መጅሊሱ ከወሃቢ አስተምህሮ ተከታዮች እንደፀዳ ይጠቅሳል፡፡
13. (C) In a shift from past practice, the IASC is now completely purged of Wahabi members. […] the Council members acknowledged that the Council is now all Sufi and in their public statements they repeatedly make reference to Ethiopia’s tradition of religious tolerance and co-existence with the Christian communities.
በተጨማሪም በዚሁ ገፅ ላይ፣ የእስልምና ምክር ቤቱ [የአመራር] አባላት በመንግሥት እንደሚሾሙ በግልፅ ይናገራል፡‑
As the Ethiopian government appoints the members of the Islamic Council, it is clear that the GoE shares this concern about growing Wahabi influence and is supporting moderate Muslim leaders in trying to counter that influence.
እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ቁም ነገር የመላው ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የጋራ ተቋም እንደሆነ በሚታሰበውና ለረዥም ጊዜያት የሱፊና የሰለፊ አስተምህሮ ተከታዮች በጋራ ሲያስተዳድሩት በኖረው መጅሊስ ላይ፣ በዚህ ወቅት (እ.አ.አ. በ2010) መንግሥት ሙሉ በሙሉ የአህባሽ አስተምህሮ ተከታዮችን የሾመ መሆኑ ነው፡፡ የአህባሽ አስተምህሮ፣ ከሰለፊ አስተምህሮ ጋር የከረረ ተቃርኖ እንዳለው የሚታወቅ ሲኾን፣ በሰለፊ አስተምህሮ ተከታዮች ላይም እጅግ የመረረ ጥላቻ ያንፀባርቃል፡፡ ከዚህ በላይ በጠቀስነው የዊኪሊክስ ሰነድ ላይ እንደተመለከተው፣ መንግሥት በጠቅላይ ምክር ቤቱ ላይ የአህባሽ አስምህሮ ተከታዮችን የሾመው ለዘብተኛ ሙስሊሞችን በመደገፍና የወሃቢን ተፅዕኖ ለመቋቋም ነው ተብሏል፡፡ ይህም ‹‹እርምጃው የወሃቢ አስተምህሮ በሃይማኖቶች የመቻቻል እሴት ላይ ደቅኖታል የሚባለውን ስጋት የማስወገድ ዓላማ ያለው ነው›› የሚል አንድምታ አለው፡፡ ነገር ግን እውን ሐቁ ያ ነዉን? የወሃቢ አስተምህሮ ደቅኖታል የተባለውን ስጋት የማስወገጃው መንገድስ ይህ ነውን? ብለን ስንጠይቅና … መሬት ላይ ያለውን ሐቅ ስንፈትሽ የምናገኘው ምላሽ ይህንን አያረጋግጥልንም፡፡ [ለዚህ አባባላችን ዋቢ የሚሆኑ ተግባራዊ ምሳሌዎችን ወደኋላ ላይ እናቀርባለን፡፡]
ዊኪሊክስ ይፋ ባደረጋቸው ሰነዶች ላይ፣ የአሜሪካ መንግሥት የሱፊ ስርዓተ‑አምልኮ የሚከናወንባቸውን ጥንታዊ መስጂዶችና የቅዱሳን የመቃብር ሥፍራዎችን ጠብቆ በማቆየት ዓላማ መሠራት አለባቸው ብሎ የሚያምናቸው ተግባራት ተጠቅሰዋል፡፡ … የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያ በተለያዩ ሃይማኖት ተከታዮች መካከል ፀንቶ የኖረው የመቻቻል ባህል በዘላቂነት ይቀጥል ዘንድ የራሱን ጥረት ለማድረግ በመሻቱ ሊመሰገን እንጂ ሊወቀስ አይገባውም፡፡ ነገር ግን፣ እንዲህ ዓይነቱ ጥረት፣ የቱንም ያህል ቀና ቢሆን እንኳ፣ ጉዳዩን እጅግ በቅርበትና በጥልቀት መመርመር የሚጠይቅ መሆኑ አይካድም፡፡ ከዚያም በላይ ግን፣ የጉዳዩ ባለቤት የሆነውን ማኅበረሰብ፣ ከማኅበረሰቡም ተደማጭነት ያላቸውን የእምነቱ መሪዎች ወይም የሃይማኖቱን ሊቃውንት ባላካተተ መልኩ ሲካሄድ የሚፈለገውን አዎንታዊ ውጤት ያመጣል የሚል እምነት የለንም፡፡ በየትኛውም የሃይማኖት ማኅበረሰብ ውስጥ ከእምነት‑ተኮር አስተሳሰብ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ልዩነቶች ሊፈጥሩ የሚችሉትን አላስፈላጊ ፍጥጫና ይህም ሊያስከትል የሚችለውን አሉታዊ ውጤት በማስቀረት ጥረት ውስጥ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የሃይማኖት ማኅበረሰብ እና ተደማጭ መሪዎቹ ያላቸው ሚና በምንም የሚተካ አለመሆኑ ሊሰመርበት ይገባል፡፡ የወሃቢያ መስፋፋትም ሆነ ከሱፊያ አስተሳሰብ ተከታዮች ጋር ያሉ ልዩነቶችንና ከልዩነቶቹ ሊመነጩ ይችላሉ ተብለው የሚታሰቡ ውጥረቶችን በዘላቂነት ለመፍታትም የጉዳዩ ባለቤቶችን የመፍትኄ አካል በማድረግ ፈንታ የችግር ምንጭ አድርጎ ማሰብ ትክክለኛ ነው ብለን አናምንም፡፡
ወሃቢያ እንደ ስጋት
ለመሆኑ የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያ እየተስፋፋ ነው የሚለውን የ‹ወሃቢ› አስተምህሮ ከምን አኳያ ነው እንደ ስጋት የተመለከተው? … ይህ ስጋት በመሬት ላይ ያለ ነውን? ካለስ ስጋቱን የማስወገጃው መንገድ ምንድን ነው? … ሙስሊም ኢትዮጵያውያንስ ይህን ስጋት በማስወገድ ረገድ ያላቸው አቋምና አስተሳሰብ ምን ይመስላል? … በተግባርስ ይህን ስጋት ለማስወገድ ምን አድርገዋል? … ‘ዊኪሊክስ’ ይፋ ያደረጋቸውን “ምስጢራዊ ሰነዶች” መነሻ አድርጎ ስለ ‘ፖለቲካዊ እስልምና በኢትዮጵያ’ ሀተታ ያቀረበው የዳያስፖራ ራዲዮ እነዚህን ቁልፍ ጥያቄዎች አልጠየቀም፡፡ ባለመጠየቁም በኢትዮጵያ መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ አላየም፡፡ ከዚያ ይልቅ፣ ሰነዱን ላለፉት ሁለት ዓመታት ገደማ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እያካሄዱ ያሉትን ሃይማኖታዊ ነፃነትን የማስከበር ሰላማዊ ትግል ጥላሸት ለመቀባት ዓላማ አውሎታል፡፡
በእኛ እምነት በየትኛውም ሃይማኖት ውስጥ የሚንፀባረቁ የጽንፈኝነት ዝንባሌዎችን ማረቅ የሚቻለው ትምህርትና እውቀትን በማስፋፋት ብቻ ነው፡፡ በዚህም መንፈስ በኢትዮጵያ ሙስሊም ማኅበረሰብ ውስጥ የአገሪቱ ሙስሊሞች የጋራ ተቋም ከሚሰኘው መጅሊስ ይልቅ የሃይማኖቱ ምሁራን በርካታ አዎንታዊ ተግባራትን ሲያከናውኑ ቆይተዋል፡፡ ከአስተምህሮ ልዩነቶች የሚመነጩ ውጥረቶችን ከማስወገድ አኳያም አንዱን ወገን በጽንፈኝነት ፈርጆ የማሳደድን አማራጭ ከሚያራምደው የመንግሥትና የመንግሥታዊው መጅሊስ መንገድ ይልቅ፣ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ አንጋፋ የሃይማኖት ሊቃውንት በጥልቅና በሳል ውይይቶች አማካይነት ኅብረተሰቡን ወደጋራ መግባባት ለማምጣት በርካታ አዎንታዊ ሥራዎችን አከናውነዋል፡፡ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ2000/2001 የተለያዩ አስተምህሮ የሚከተሉ አንጋፋ የሙስሊም ሊቃውንት፣ በሱፊው በኩል በሸኽ ዑመር ኢድሪስ መሪነት፣ በሰለፊ በኩል ደግሞ በዶ/ር ጀይላን መሪነት፣ ይህን በመሰሉ ጉዳዮች ላይ ተከታታይ የሆኑ በሳል ውይይቶችን በማድረግ ከመግባባት ላይ ደርሰው፣ የአንድነት ጉባዔ ለማካሄድ የመጨረሻ ዝግጅት እያካሄዱ ነበር፡፡ ይህን መሰል ታላቅ አዎንታዊ እርምጃ ከኢትዮጵያ በቀር በሌሎች ሙስሊሞች በሚበዙባቸው አገራት እንኳ መካሄዱ ያጠራጥራል፡፡ ግና ይህ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የተለየ አዎንታዊ ተግባር በህዝብ ባልተመረጠው የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮችም ሆነ በመንግሥት ዘንድ በበጎ ዓይን አልታየም፡፡ እናም መንግሥት እና ምክር ቤቱ ይህንን ሰላምና አንድነትን የማምጣት ዓላማ የነበረውን ሂደት ሆን ብለው አስተጓጉለውታል፡፡ ከቶ ይህ ለአገር እና ለህዝቦች ሰላም የማሰብ ተግባር ነውን? መልሱን ቅን ልቦና ላላቸው ወገኖች ኅሊና ትተነዋል፡፡
በሙስሊሙ ኅብረተሰብ መካከል የሚፈጠሩ የሃይማኖት አስተምህሮን መሠረት ያደረጉ ማናቸውም ችግሮች ሙስሊሙ ኅብረተሰብ በራሱ ሊፈታቸው የሚገባ፣ የውስጥ ጉዳዮቹ ናቸው፡፡ የጋራ ተቋማችን በምንለው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ላይ በመንግሥት የተሾሙ አመራሮች ይህንን የማድረግ ኃላፊነታቸውን አለመወጣታቸው ሳያንስ፤ ጭራሽ በዚህ መንፈስ ይካሄዱ የነበሩ የሙስሊም ሊቃውንት ውይይቶችን ማሰናከላቸው እየታወቀ፣ የኢሕአዴግ መንግሥትን እና በእርሱ ሹማምንት የሚመራውን መጅሊስ ፀረ‑አክራሪ፣ ህዝበ ሙስሊሙን ግን የፖለቲካዊ እስልምና አስፋፊ አድርጎ ለመሳል የሚደረገው ሙከራ በጣም የሚያሳዝን እና የሚያስተዛዝብ ነው፡፡
ስለ እኛ ማን ይናገር
ዊኪሊክስ ይፋ ያደረጋቸው የስቴት ዲፓርትመንት የ2010 ሰነዶችን ዋቢ በማድረግ በዳያስፖራ ራዲዮ በ‘ፖለቲካዊ እስልምና’ ዙርያ በቀረበው ዝግጅት ላይ የምናቀርበው ሌላው ዐብይ ሒስ፣ ለኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ስለ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ማንነትና ምንነት ማን ነው የሚነግራቸው በሚል ጥያቄ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ በእኛ እምነት ሙስሊም ላልሆኑ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ስለ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ማንነትና ምንነት በሦስተኛ ወገን ሊነገራቸው አይገባም፡፡ መንግሥታችን የገዛ ዜጎቹን፣ ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖቻችንም ለዘመናት አብረናቸው የኖርን ሙስሊም ወገኖቻቸውን በውጭ መንግሥት ዕይታ፣ ግንዛቤ፣ አረዳድና አስተሳሰብ ላይ ተመሥርተው ሊያዩን ይገባል ብለንም በፍፁም አናምንም፡፡ በእኛ እምነት ይህ ለዘመናት አብሮ በመኖር ያጎለበትነውን ተዋድዶ፣ ተፋቅሮና ተከባብሮ የመኖር ታላቅ እሴት ትርጉም‑አልባ የሚያደርግ የተሳሳተ አካሄድ ነው፡፡ …
**********
በኢትዮጵያ፣ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በህዝብ ሀብት የሚንቀሳቀሱትና ሙሉ በሙሉ በኢሕአዴግ ቁጥጥር ሥር ያሉት መገናኛ ብዙኃን፣ እንዲሁም ከከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት አንስቶ እስከ ወረዳና ቀበሌ ድረስ ያሉ የኢሕአዴግ ካድሬዎች፣ “ወሃቢ!” የሚለውን ስያሜ ህዝብን፣ በተለይም ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖቻችንን የሚያስፈራሩበት ጭራቅ አድርገውታል፡፡ … ከኩዌት መንግሥት በተገኘ የገንዘብ እርዳታ መስጊዶች መገንባታቸው አልያም አሮጌ መስጊዶች መታደሳቸው የወሃቢ እምነት መስፋፋቱን ይገልጻል ብሎ መደምደም የሚቻል አይመስለንም፡፡ በአዲስ አበባ ፒያሳ አቅራቢያ የሚገኘው ኑር (በተለምዶ በኒ) መስጂድ ከኩዌት በጎ አድራጊዎች በተገኘ የገንዘብ እርዳታ ነው ፈርሶ በአዲስ መልክ የተገነባው፡፡ ነገር ግን መስጂዱ የአንድ የተለየ አስተምህሮ ማስፋፊያ አይደለም፡፡

UDJP members attacked by local militias in Fiche town


UDJP members attacked by local militias in Fiche town

Should the ESFNA Solicit Leadership from the Community?


by LJD
This write up – which is dedicated to the founders of the Ethiopian Sport Federation in North America (ESFNA) – is intended to strengthen the Federation.Ethiopian Sport Federation cultural Festival July 2013
A board’s ability to govern, monitor and manage an Executive Committee (EC) actions and activities is critical for a success of an organization. The EC credibility with the board is essential to its ability to function effectively.  While the ESFNA leadership team lacks basic leadership and communication skills, the organization’s reach has grown exponentially.
On the one hand, the ESFNA’s tax returns show that it spent about $1.4 million – 62% of its five years revenue from 2006 to 2011 – for travel, conferences and meetings.  On the other hand, to participate in the ESFNA’s annual soccer tournament – its soccer clubs raise funds from their community, even though it might not be much. At times, the clubs get a negligible amount of funds from their Federation, about $900 per year from 2006 to 2011. The players pay for their own transportation and food, and they chip in to buy their soccer gear as needed.
The Federation’s Progress
The organization is significantly advancing in some areas, and it is keeping its status quo in others. To illustrate, the ESFNA heard one of the public calls to honor Judge Birtukan Mideksa for her contribution to bring democratic system of government in Ethiopia. And it extended its invitation on April 21, 2011 to pay her homage at its July 2011 28th anniversary in Atlanta, GA – which triggered its bankroller, Sheikh Al Amoudi collaborator of the TPLF/EPRDF, to cut ties with it.  Though pretext for terminating the sponsorship was an email a board member of the ESFNA, Getachew Tesfaye, sent to his colloquies stating “it is what our leaders did to reverse the selection and the relentless effort by the PR office to maintain the status quo.  The leadership is convinced that money will cure all. I disagree. My preference would be to return back this blood money.”
Since the ESFNA association with Al Amoudi ended and, by extension, the TPLF/EPRDF, the Federation has held two of its most successful soccer tournaments under the leadership of its President Getachew Tesfaye, a Nuclear Physicist, in which tens of thousands of Ethiopians across the globe congregated at Loos Stadium in Addison, TX in 2012 and at Byrd Stadium in College Park, Maryland in 2013 – even though the Federation remains non-transparent.
Some of the highlights of the weeklong events at the stadiums were the surge in the Ethiopians pride in their traditional clothing and display of patriotism in their flag. For instance, they flashed the stadiums with their untampered red, green and yellow flag “which stands as a symbol for Ethiopia which resolutely defended itself from Italian colonization at the Battle of Adwa.” Also the patriotic display of passion for the flag was exhibited in their clothing. They proudly rocked their flag dresses, skirts, pants, t-shirts, bandanas, tattoos, etc. Nobody guessed the Ethiopian flag would be so fashionable, particularly those who tampered with it.
For making the ESFNA 29th and 30th anniversary quite extraordinary, viva la the ESFNA fans, the media of the Ethiopian Diaspora and the Federation!!!
The Federation’s Organizational Behavior
“Organizational behavior is a field of study that investigates the impact that individuals, groups and structures have on behavior within an organization for the purpose of applying such knowledge towards improving an organization’s effectiveness”, according to Wikipedia.
After the first year in office, most of the ESFNA EC members tragically fail to harness the full trust and collaboration of the Federation’s soccer clubs. For example, most Federation’s board members allege that the current president has not been able to inspire, to motivate and to unify the soccer clubs during his first term. As a result, team spirit between the board and the EC hit a new low at the 30th anniversary.
To prove their point: For the soccer players, there was no physician and medical kit during the 2013 games, due to lack of coordination among the EC. Volunteers who were assigned by the host team to help the EC during the tournament failed to show up thereof members of the EC blatantly violated the bylaws, which is a violation of fiduciary duty, by breaching internal control procedures under the watchful eyes of the board and the public – which was a hard blow to the individual’s reputation. Those board members who were observing the incident did not attempt to rectify – which was a blow to the Federation.
Obviously, the federation has been lacking leadership and/or ethical and moral standards which set the tone for trust, teamwork, respect for self and others with the soccer clubs. Between the federation board and the EC there have been a chronic interpersonal conflict that requires an analysis of how they have been working (organizational behavior analysis). The Federation’s board might consider reaching out to the community volunteers or paid expertise to get their organizational behavior analyzed.
Concerning Transparency
For years, while showing solidarity with the Federation – its fans have been diligently encouraging it to run its business transparently – without successes. Though it has been in business for 30+ years, it has not yet developed systems, controls and standard procedures that would help its soccer clubs to effectively govern, monitor and manage the actions and activities of the EC.
Moreover, the EC has never made the organization financial records readily accessible to its board, let alone to the public. If lucky, a board member might obtain a copy of the Federation financial records after dealing with many unreturned telephone calls and email exchanges. The general public who has a desire to be informed about the finances of the Federation has to find its old tax returns, which are cumbersome for inexperienced eyes, on other company websites that are specializing in reporting on U.S. nonprofit companies such as GuideStar USA, Inc.
Since the Federation’s inception, a year has hardly passed without the soccer clubs alleging that the Federation’s resources were mismanaged by those who were entrusted with duties – the EC. This vicious cycle of allegation of misappropriation of funds by the EC has been heartbreaking and embarrassing for its fans resulting in negative publicity for the Federation. It makes one wonder why the soccer clubs have not been able to place controls and standard procedures to help them safeguard the Federation resources.  For instance, some board members are calling for an inquiry into unacceptable practices at the 2013 venue in Maryland. They allege that key components of risk management, prevention and detection internal control procedures were compromised in a violation of the organization’s bylaws.