Tuesday, June 3, 2014

ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ በስዊትዘርላንድ በርን





ቀን JUNE 26/2014

በሃገራችን ኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ ከዕለት ወደ ዕለት ወደባሰና ወደለየለት ፖለቲካዊ ምስቅልቅል እየሄደ መሆኑ ይታወቃል፣ ለዚህም ማሳያ የሆኑት ከሰሞኑ የተፈጸሙት ፍጹም ሰላማዊ በሆኑ ዜጎቻችን የሚደርሰው ግድያ፣ የጅምላ እስርና የመብት ጥሰት ሲሆን፣Ethiopians in Switzerland demonstration
በአምቦ፣ በሃሮማያ፣ በመደወላቡ/ወለጋ/ እና ናዝሬት ዩኒቨርሲቲዎች በገዢው መንግስት እየተፈጸሙ ያሉና መብታቸውን በሰላማዊ መንገድ በጠየቁ ኢትዮጵያውያን ኦሮሞ ተማሪዎች ላይ በደረሰው የግፍ ግድያና እስካሁን ድረስ ባልቆመው ከመማርያ ክፍላቸው እና ከማደሪያቸው እየተለቀሙ ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደው በሚሰወሩ ተማሪዎችና የሚፈጸምባቸውን ግፍ በመቃወም፣
በቅርቡም ይበጃል ያሉትን ሃገራዊ ራዕይና በጎ ሃሳብ በመጦመራቸው ምክንያት በማዕከላዊ የጭለማ እስር ቤት በግፍ የሚማቅቁ እና የሚሰቃዩ ጦማርያንና ጋዜጠኞችን እስር በመቃወም፣
ገዢው መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ በመግባት መረን ለቆ የሃገሪቱን ታላላቅ የሃይማኖት ተቋማት በማተራመስና የእምነት ቦታዎቹን በመድፈር እንዲሁም የሃይማኖት መሪዎችን ሳይሆን ፖለቲከኞችን ለመሾም፣ ይህንና መሰል እኩይ ተግባራት በማድረጉ ሂደት በተለይም መጅሊሳችን በመስጊዳችን ያሉ የእስልምና ሃይማኖት የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎችን በማሰር ፖለቲካዊ ህልሙን የእምነት ቦታዎቹን በማርከስ ለማሳካት የሚያደርገውን ጥረት በመቃወም፣
በጠቅላላው የሃገራችን ክፍሎች በጉጅሌው አገዛዝ ካድሬዎች ሆን ተብለው የሚፈጸሙ ዜጎችን እርስ በርስ የማጋጨትና ያለአግባብ ማፈናቀልን በመቃወም ወዘተ…. እነዚህና ሌሎችም ዘርፈ ብዙ የሆኑት መሰረታዊ የሰው ልጆች መብቶች በአምባገነኑ ህውአት ኢህአዴግ የግፍ አገዛዝ በሚጣስባት እንዲሁም ዜጎች የተለየ አመለካከት ስላላቸው ብቻ ህይወታቸውን በሚያጡባት ሃገር. . . ግድያውን፣ እስሩንና፣ ግርፋቱን ሸሽተው የሚወጡ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የስደተኝነት ምክንያታቸው በአግባቡ ባለመታየቱ እና በአብዛኛው ተቀባይነት ባለማግኘቱ የስዊትዘርላንድ መንግስት የወያኔው ዘረኛ እና አምባገነን አገዛዝ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እያካሄደ ያለውን አፈናና ግድያ በመመርመር የዘረኛውን አገዛዝ እኩይ ድርጊት እንዲያወግዝና ከኢትዮጵያ ህዝብ ጎን እንዲቆም በተጨማሪም በስዊዘርላንድ ተጠልለው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የስደት ጥያቄአቸው በድጋሚ ባግባቡ እንዲታይና አዎንታዊ ምላሽ እንዲያገኝ ጥያቄአችንን ለማቅረብ መሆኑን በአክብሮት እናስታውቃለን::
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብትና ዴሞክራሲ ግብረ ሃይል በስዊትዘርላንድ
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!
NB: የሰልፉን ሰዓት፣ ቦታና ዝርዝር የትራንስፖርት ሁኔታዎችን በቀጣይ የምንገልጽ መሆኑን እናስታውቃለን

No comments:

Post a Comment