Tuesday, May 20, 2014

መች ገባና ወጣሁ ይላል? አቶ ሙሴ ተገኝን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር የተሰጠ መግለጫ


April 6, 2012
Ethiopian People Patriots Front
ከጥቂት ሳምንታት በፊት ኢትዮ ሚዲያ በተባለውና የትግራዩ ተወላጅ አቶ አብርሃ በላይ በሚያስተዳድረው ድረ ገጽ አማካይነት አቶ ሙሴ ተገኝ በድርጅታችን ላይ የከፈተውን ዘመቻ በተመለከተ ምላሽ ላለመስጠት ያደረግነውን ጥረት ወገን ሁሉ ይረዳዋል ብለን ተስፋ እናደርጋለን።
ነገር ግን አቶ ሙሴ ተገኝ በጥቂት የአካባቢው ሰዎችና ጸረ ኤርትራ ህዝብ ጭፍን አመለካከት ባለቸው ግለሰቦች እየታገዘ በየዕቁብ ቤቱ ሳይቀር የከፈተው ጥቃት እየጨመረ በመምጣቱና  የግለሰቡ ጉዞ ያበሳጫቸው ወገኖችም ለምን ምላሽ አይሰጠውም በሚል ባቀረቡልን ተደጋጋሚ ጥያቄ መሰረት  ይህን መግለጫ እንድናወጣ ተገደናል።
አቶ ሙሴ ተገኝ ወይንም በተለምዶ አጠራር ፕሮፌሰር ሙሴ ሰሞኑን ከኤርትራ ለቀን ወጥተናል በማለት ራሱን እንደ ኢህአግ አባልና መሪ በመቁጠር የህይወት መስዋዕትነትን ዛሬም እየከፈለ ባለፈው አርበኛ ሰራዊት ደም መቀለዱን ስንሰማ የተሰማን ስሜት አስቆጪ እንደሆነ መግለጽ የተገባን ይሆናል።
በሰላማዊ ትግል ስም እየማሉና ከአምባገነኖች ጋር እየተሻሹ መቆየት ቀላል ሲሆን ጠመንጃ አንስቶ ለፍልሚያ መዘጋጀት አይደለም ጠመንጃ ካነሱ አርበኖች ጋር እንኳ ቆሞ ማውራት ብቻውን ምን ያህል ላብ ላብ እንደሚልና መች ከዚህ ቦታ ጠፍቼ እንደሚያሰኝ ያሳለፍናቸው ተሞክሮዎች አያሌ ናቸው።
ጠመንጃ አንስቶ ስርዓት ለመለወጥ የሚታገል ድርጅት ፋራ ነው እያሉ ሲሳለቁብን ከነበሩ የሰላማዊ ትግሉ ፋኖዎች አንስቶ ከአርበኞቻችን ጋር ፎቶ ግራፍ እየተነሱ አርበኛ አርበኛ ለመሽተት ብሎም “የመሃይምናኑ” አርበኞች መሪ ለመሆን በስተጀርባ ሲሯሯጡብን የነበሩትን በትግስት ያስተናገድንበትም ጊዜ ሩቅ አይደለም።
ታግለው ባታገሉንና በትረ ስልጣኑን በጨበጡ እሰየው በነበረ ። ቅር የሚያሰኘውና እንባ እንባ የሚለው ግን በርቀት በሪሞት ኮንትሮል ካልተቆጣጠርናችሁ ማለታቸውን ጠልተን  ፊታችንን ስናዞርባቸው በጠላትነት የሚፈርጁን ዝና በግዱ ግለሰቦች ለወያኔ ገመናችንን ማደላቸውና መረጃችንን ማሰራጨታቸው ይብሱን ጎዳን እንጅ።
በአዲስ መንፈስ ራሱን ያዘጋጀውና ወደ ወያኔ ጉያ ለመግባት ሰውነቱንን እያሟሟቀ የሚገኘው የዛሬውም አቶ ሙሴ ተገኝ ከነኝህ ከላይ ከጠቀስናቸው አንዱ ሲሆን በርዕሳችን ላይ እንዳመለከትነው ግለሰቡ ሲጀመርም የአርበኞች ግንባር እንኳን መሪ፤ ሙሉ አባል ያልነበረ የጤናው ሁኔታ እንኳ አጠራጣሪ በመሆኑ አርበኛው በሙከራ አባልነት በአስመራ ከተማ ነዋሪ በመሆን እንዲቆይ የወሰነበት ግለሰብ መሆኑን በቅድሚያ መግለጽ እንወዳለን።
ለዕለታዊ ኑሮ ቅመም መጨመርንና ለአንዲት ቀን አዳር ብትሆን ውበት መስጠትን የተካነበት ሙሴ ተገኝ የገንዘብ ምንጭንም ማፈላለግ እንዲሁ አብሮ አድጎበታልና ከአለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ጋር በመተባበር የመጀመሪያው የአስመራ ከተማ ኢንቨስተርና አካለ ስንኩላንን በስፖርት ማሰልጠን በሚል የረዴት ድርጅት  አስተዳዳሪ ሆኖ የቆየ ሰው ነበረ።
የዛሬን አያርገውና በአስመራ ሲሶ መንግስት አለው እየተባለ በወቅቱ ይቀለድበት የነበረው አቶ ሙሴ ተገኝ ፕሮፌሰር በሚለው ስሙ  ማልለን በአስመራ ከተማ የሚገኙትን ኢትዮጵያውያን ወደኛ ድርጅት ያመጣልናል በሚል የአስመራና አካባቢው የአባላት ማደራጃ ጽ/ቤት ሃላፊ በማድረግና ማህተም በመስጠት ያሰማራነው ሰው ነበረ።
ከኢትዮጵያውያን ዜጎች ብቻ አይደለም ከኤርትራውያንም ጭምር ገንዘብ በመቀበልና ማህበራዊ ሙስና ውስጥ በመዳከር ከሃገር ማስኮብለልን እንደተጨማሪ መተዳደሪያ በማድረግ እንዲህ እንደዛሬ ሳይታወቅና በኤርትራ መንግስት የወንጀለኛነት ማህደር ውስጥ ስሙ ሳይካተት  የ1990ዎቹ መጀመሪያ ወቅት ነበረ ከግንባራችን አርበኖች ጋር ትውውቅ የፈጠረው።
ኢትዮጵያውያን ማለት የአባይ ተፋሰስ ሃገሮች ማለትም ጎጃም ጎንደርና ከፊል ወሎ ናቸው በማለትና በአባይ ጉዳይ ፈቃድ ልንጠየቅ የሚገባን እና ጎጃሜዎቹ ወይንም እንደሱ አጠራር ፈለገ ግዮኖቹ ብቻ ነን በማለት ጎሰኛ ድርጅት አቋቁሞ የነ መለስ ዜናዊን ዘረኛ ፖሊሲ ያቀነቅን የነበረው አቶ ሙሴ ተገኝ የአስመራ ከተማ ነዋሪ ከሆነበት ጊዜ አንስቶ ጥቂት አዱኛ ሰራሽ ደጋፊዎቹን በዙሪያው በማሰባሰብና የሌላውን አካባቢ ተወላጆች እርስ በርስ በማባላት የያዘው አባዜ ለኛም አርበኖች እንደተረፈ ለሚያዳምጠን ወገን ማካፈሉ ምን ያህል የመከራ ዘመን እንዳሳለፍን ያስረዳልናል የሚል እምነት ይኖረናል።
የፖለቲካና የማህበራዊ ኑሮ ካሪዝማ ወይንም የደስደስ ቀድሞውንም ያልተፈጠረበት፤ ከትንሽ እስከትልቅ አክብሮት ተችሮት የማያውቀው፤ዛሬ አንድና ብቸኛ ባህርዩ ዜጎችን በገንዘብ የማማለል ክህሎቱ እንኳ ከላዩ ላይ ወልቃ የሾለከችበት አቶ ሙሴ ተገኝ ከውጭ የረድኤት ድርጅቶች በሚጎርፍለት ገንዘብ ሴት አካለ ስንኩላንን ጭምር ከማባለግ የዘለቀ አንድ ቀን ወንዶች ከዋሉበት ሊያውለው የሚችል ተግባር ላይ ሳይሳተፍ ራሱን አዋርዶ ኢትዮጵያውያንና ህዝቧን ያዋረደ ግለሰብ መሆኑን በድፍረት ለመናገር ግዴታችን ይሆናል።
የረድኤት ድርጅት ሃላፊ በመሆኑና በአስመራ ከተማ የኢሕአግን ደጋፊዎች ያስተባብርልናል በሚል ያስቀመጥነው ሙሴ ተገኝ በተለያዩ ጊዜያት አርበኞቻችንን ለመጎብኘት ወደ ግንባር ሲመጡ ከነበሩት ለምሳሌም ያህል ከሳይንቲስት ኢንጂነር ቅጣው እጅጉ እንዲሁም አብርሃም ያየህ ጋር በመሆን ከአስመራ ይመጣ በነበረበት ጊዜ ነበረ ከሰራዊታችንና ከመሪዎቻቸው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የመሰረተው።
ለአርበኞች ግንባር ተዋጊዎች፣ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ማለት መሃከላቸው የሚተኛ አርበኛ ማለት ነው። ሳይገባ ወጣሁ፤ አባል ሳይሆን መሪ ነበርኩ  በማለት ዛሬ ለያዢ እያስቸገረ ያለው ሙሴ ተገኝ ይዞ በሚንቀሳቀሰው የረድኤት መኪና አንዲት ቀን እንኳ አንድ አርበኛ ሳይሳፈርባት፣ ለአንዲት ምሽት እንኳ ከአርበኛው ጋር ጨረቃን ሳያይ፤ የአርበኛውን የሌሊት ህይወት ሳይካፈል ወደሞቀበት የከበርቻቻ መንደር ይመለስ የነበረ ሰው እንደነበረ ለወገኖቻችን መግለጽ የተገባ ነው።
በ1993ቱ የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ምስረታ፤ በኋላ የግንባሩ መሪ ከሆነው መስከረም አታላይ ጋር የቅርብ ግንኙነት ስለነበረው በዕለቱ የክብር እንግዳ እንደነበሩት የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችና የኤርትራ መንግስት ባለስልጣናት አይነት በክብር እንግድነት ተጋብዞ ተገኘ እንጂ እንደ ተራ የድርጅት አባል እንኳ አንዳችም ስፍራ እልዳልነበረው ለወገን ይፋ ማግድረግ ግዴታችን ነው።
ኤርትራ ከገባበት ጊዜ አንስቶ በሚያካሂዳቸው ማህበራዊና ፖለቲካዊ ነውሮች በኢህአግ አባላት ዘንድ የተጠላው ሙሴ ተገኝ  ከስራ አስፈጻሚ አባላት ጋር ወደ አርበኞቹ ማሰልጠኛ ይምጣ እንጂ  ዛሬ ለጥፋት ተልዕኮ የሚጠቀምበትን ቪዲዮ ካሜራ ያጥፋ ያብራ እንጂ ፤ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርጉ ቃላት ብተና ላይ ሲንቀሳቀስ ይስተዋል እንጂ ለአንዲት ቀን እንኳ በላዩ ላይ የለጠፈውን ፕሮፌሰር የተሰኘ አንዳች የሚያክል ትልቅ ስም በአግባቡ ሲጠቀምበት ያልታየ ሰው እንደሆነ ማስረዳት አስፈላጊ ነው።
ዛሬም በጽ/ቤታችን ውስጥ ለላንቲካነት ተጎልታ የምትገኛውን ሰርታ የማታውቅ ዴስክቶፕ ኮምፒውተር ይዞ የተጠጋው ሙሴ ተገኝ ለግል ዝናው ይመቸው ዘንድ በወራት አንድ ጊዜ በማሰልጠኛው እየተገኘ የኢህአግንና የትህዴድ አባላትን በቪዲዮ ይቀርጽ የነበረ ሲሆን ጎጃም ፈለገ ግዮን የሚለው ጠባ ብሄረተኛ ፍልስፍናው ተቀባይ በማጣቱም ኢትዮጵያዊነት የሚል አዲስ መሰል ፍልስፍና በመስበክ ስሙን ለማረቅ የጀመረው በዚህ ወቅት ነበረ።
በ2004 አመተምህረት ከረን ከተማ ከምትገኝ ቡና ቤት ውስጥ  ከወያኔ ከድተው ከመጡ የሰራዊት አባላት መሃከል በመንቀስ 6 የጎጃም ተወላጅ ወታደሮች ሰብስቦ ስለ ጎጃም ህዝብ የመገንጠል መብት መከበር ተገቢነትና  አባይ የጎጃም ህዝብ ብቸኛ ሃብት ነው በሚል ያቀረበው ትምህርት ተቀባይነትን ሊያገኝ አልቻለም። የሚበትነው በሩ ሁሉ መልሶ እየለበለው እንደሆን የተሰማው ሙሴ ተገኝ ኢትዮጵያዊነትን ለመውደዱ ማረጋገጫ ይሆነው ዘንድ ኢትዮጵያኒዝም የሚባል ገመና መሸፈኛ ትምህርት ለጥቂት ቀናት በአርበኛው የመሰብሰቢያ ታዛ ስር ራሱን ከቪዲዮ እየከተተ ለመስጠት የሞከረውም የዛኑ ሰሞን ነበረ።
በ1996 አመተምህረት ኢህአግ  ወደ ህብረት ሲመጣ  ከቅርብ ጓደኛው መስከረም አታላይ ጋር በመቀራረቡ ብቻ አሁንም የኢህአግ የአስመራ ከተማ የድጋፍ ጽ/ቤት ሰራተኛና ከአባሎቻችን ላይ ገንዘብ ተቀባይ ሆኖ የሰራ ፤እንዲሁም ያለውን ትርፍ ጊዜ አጋጣሚ ይጠቀምበት ዘንድ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደጋፊዎቻችንን ሲገናኝ የቆየ ሲሆን የመሃል ሃገር፤ የጎንደር፤ የአርማጭሆ፤ የወልቃይትና የጎጃም ተወላጆች በሚል የመከፋፈል አባዜ የተጠናወተው ሙሴ ተገኝ ተዋጊዎችን ከፖለቲካ ካድሬዎች፤ እንዲሁም የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን ከስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ጋር በማናቆር መሰሪ የመከፋፈል ተግባራትን በተፈጠረለት ትንሽ ቀዳዳ በመጠቀም ሲያከናውን  የሰነበተ ፤ የድርጅቱን የአመራር አካላት በመከፋፈልም ገሚሱን ወደ ሱዳን ቀሪዉንም ወደ ሌላ ሃገር እንዲሄዱ አፍራሽ ተግባር ሲፈጽም የከረመ ነው።
በሺህ የሚቆጠሩ አርበኞቻችን የተሰዉለት ድርጅታችን ያለፈባቸው የመከራ አመታት የበዙ እንዲሆኑና በድርጅታችንም ውስጥ ለተፈጠሩት አሳዛኝ ክስተቶችም  ዋነኛውንና  ከፍተኛውን ሚና ሲጫወቱ ከነበሩት አንዱ ሙሴ ተገኝ መሆኑን ሳንወድ ዛሬ እንድንናገር ስንገደድ በድርጅታችን ውስጥ ለተሰሩ ወንጀሎች አቶ ሙሴ ተገኝና የቅርብ ጓደኞቹ ወደፊት የኢትዮጵያ ህዝብ ሊፋረዳቸው የሚያስችል መረጃዎች ዛሬም በጽህፈት ቤታችን እንደሚገኙም በተጨማሪ መግለጽ አስፈላጊ ነው።
በጥቂት ተባባሪዎቹ አማካይነት እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ2000 ዓ/ም ወይንም እንደ ኤሮፓ አቆጣጠር 2008 ላይ በተጠራው የድርጅቱ 1ኛ ጉባኤ ላይ ወደ ሙሉ አባልነት እንዲሁም የማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት እንዲሸጋገር ከቅርብ ጓደኞቹ በተደረገው ጥቆማ  ሙሴ ተገኝ የአንድም አባል ድምጽ ሳያገኝ ጭራሹኑም ቁጣና ሁከት ተቀስቅሶ የነበረ ከመሆኑም በላይ ችግሮቹን ላንዴና ለመጨረሻ ለመቅረፍ በተካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ላይም በጠቅላላ ድምጽ ከድርጅቱ እንዲወገድ  የተወሰነበት ነው።
የፖለቲካ ቆሌ የራቀው ሙሴ ተገኝ ላለፉት አራት አመታት ባዘጋጀው ድረገጽ ላይ የአርበኞቻችንን ምስል በመለጠፍ ምስጢሮቻችንን ከአደባባይ በማኖርና የማሰልጠኛ ጣቢያዎቻችንን ሳይቀር ለጠላት በማስተዋወቅ የእጅ መንሻ እያደረገን የቆየ መሆኑን ወገን ልብ እንዲል እንወዳለን።
አዎ ኢሕአግ ዛሬም ወያኔን እያሳደዱ የሚቀጡ፤ የሚሰዉ፤ እንደወታደር የሚማረኩና የሰቆቃ ሰለባ የሆኑ አርበኞች ያሉት ድርጅት ሲሆን ሙሴ ተገኝ የወያኔን ቴሌቪዥን ገልብጦ ለህዝብ እንዳቀረበውም አምና በወያኔ ተማርከው አምልጠው በመውጣት ዘንድሮም አብረውት የሚፋለሙ አርበኞች ያሉት ድርጅት ነው።
እነ ሙሴ ተገኝ የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኖች ግንባር ተዋጊ ኤርትራ ውስጥ የለም ማለታቸው እኛን ሁነው ማውራታቸው ከሆነ ትክክል ናቸው ለማለት እንደፍራለን። ምክንያቱም አዎ የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት ኤርትራ ውስጥ ምን ይፈይዳልና። የኢሕአግ ሰራዊት አባላት እየታገልን እየደማንና እየሞትን ያለነው በበቀልንበት ምድራችን፤ እትብታችን በተቀበረባትና አባቶቻችን ለዳር ድንበራቸው በወደቁባት መሬታችን ላይ ነው።
እኛ የኢሕአግ ሰራዊት አባላት እንደ አቶ ሙሴ ተገኝ አይነቱን የበሉበትን ወጭት ሰባሪና የክህደት አውራ ዋልጌ ግለሰቦች በጥብቅ እንጠላለን። በገዳዩ የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ምክንያት ሃገራቸውን ጥለው የተሰደዱ ዜጎች ከጅቡቲ ከሱዳንና ከመሳሰሉት አጎራባች ሃገሮች እየታነቁ ወደ ወያኔ እስር ቤት ሲጣሉ፣የኤርትራ ህዝብና መንግስት ግን ዛሬም ድረስ አቅፈው ደግፈው፣ያላቸውንም አቃምሰውንና አልብሰውን ፣ለነጻነታችንም እንበቃ ዘንድ አይዟችሁ በማለት እስከ አሁኗ ደቂቃ ድረስ ከጎናችን መሆናቸውን በድፍረት እንናገራለን።
የኢሕአግ ተራ አባል እንኳ ሳይሆኑ ከኤርትራ ለቀን ወጥተናል በማለት በየድረገጹና የመነጋገሪያ መድረኩ ያዙን ልቀቁን የሚሉት ግለሰቦች ቁጥራቸው የበዛ በመሆኑ ወገን ሁሉ እኒህን በድርጅታችን ስም የሚነግዱ፣ የድርጅታችንን ማህተም በመጠቀምም ከስደተኛ ወገኖቻችን ጭምር ሳይቀር ገንዘብ በመሰብሰብ መተዳደሪያቸው እያደረጉ ያሉትን ግለሰቦች ወጊዱ ይላቸው ዘንድ በዚህ አጋጣሚ ማስገንዘብ እንወዳለን።
ራስ ሳይጠና ጉተና እንዲሉ ስምንት ሁነው በተሰበሰቡ በሳምንቱ ንፋስ የጣለውን የኤሌክትሪክ ቋሚ ፎቶ እያነሱ ሰራዊታችን ድልን እየተጎናጸፈ ነው ከሚሉ ሃሳዌ መሲሆች ኢትዮጵያዊ ሁሉ ራሱን እንዲያርቅ ስንመክር፤ በውን መሳሪያ አንስተው ገዳዩን ስርዓት በመፋለም ላይ ያሉ ወገኖች ካሉ ግን ዜጋ ሁሉ እገዛ ያደርግላቸው ዘንድ ጥሪያችን እናቀርባለን ። ምክንያቱም በመሳሪያ ሃይል ብቻ ነውና ዘረኛው አገዛዝ ከህዝባችን ጫንቃ ላይ ተሽቀንጥሮ የሚወድቀው፤ ብሎም እውነተኛ ሰላምና ዴሞክራሲ በሃገራችን ላይ ሊሰፍን የሚችለው።
አንድነት ሃይል ነው!
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር
መጋቢት 27 ቀን 2004

በኦክላንድ መካነ ሰላም መድሃኔዓለም ካቴድራል በተካሄደው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ… የተሰጠ መግለጫ


አማራውን በሁለንተናዊ መልኩ አዳክሞ መግዛት ወይም ማጥፋት


በጌታቸው ፏፏቴ
ራስ ስሁል(ራስ ስዑል) ሚካኤል መቀመጫውን በጐንደሩ ቤተ-መንግሥት በማድረግ በሥሩ ንጉሶችን በማንገስ ከላይ ሆኖ የሚቆጣጠራት በመሳፍንቶች የምትመራና አንድ ማዕከላዊ የሆነ ግዛቷ ለተወሰነ ጊዜ ተዳክሞ የነበረች ኢትዮጵያችን ይገዛ ነበር። በኋላ በመይሳው ካሣ(አፄ ቴዎድሮስ) የተገነባ ማዕከላዊ መንግሥት ተመስርቶ እነሆ እኛ እስካለንበት ዘመን ደርሷል። የኛው ሞራልና ኢትዮጵያዊነት ወኔ ደግሞ የት እንደሚያደርሰን እናየዋለን።ወደ ራስ ስሁል ልመለስና ራስ ስሁል ሚካኤል ጨካኝና ተንኮለኛ መሆናቸውን የሚያሳይ አንዱን ንጉሥ ከምግብ ጋር መርዝ በመጨመር አንደኛውን ንጉሥ በሻሽ አሳንቀው መግደላቸውን የሚገልጽ አንድ ጹሑፍ አንብቤ ስለነበር የህወሃት ድርጅታዊ ፕሮግራም ከዚህ የተቀዳ ይሆን ? በማለት አንዳንድ የቀደምት ጸሓፍትን መመልከት እንዳለብኝ የግድ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።ራስ እየተባሉ ንጉሶችን ይገዙ የነበሩት ራስ ስሁል ሚካኤልና ዛሬ ህወሃት ብዙ የክልል ንጉሶችን አንግሶ የክልል ንጉሶችን እየገዛ ሕዝባችን በጭቆና መዳፍ ሥር ወድቆ መተናፈሻ ተነፍጎት ሳይ ይህን ችግር ቶሎ ነቅለን ካልጣልን እስከ ወዲያኛው ትውልዳችን መክኖ እንደሚቀር ግልጽ ማሳያ መስሎ ይታየኛል።የዘመኑ የክልል ገዥዎች ወይም መሪዎች ከህወሃት መንገድ ትንሽ ሲያፈነግጡ ምን እንደሚከተላቸው ግልጽ ሲሆን ውክልናቸው ወይም ታማኝነታቸው ላሉበት ክልልና ህዝብ ሳይሆን ለህወሃት ብቻ እንደሆነ ማሳመኛ የሚያስፈልገው አይመስለኝም።በቅርብ ወራት የሞተውን የኦሮሞ ክልል ፕሬዘዳንት ዓለማየሁ አቶምሳን ህመም ምንጭ ምን እንደሆነ በተለያየ መንገድ ያፈተለኩት ወሬዎች እንደሚነግሩን ህወሃት የራስ ስሁልን ታሪክ እንደደገመ ነው።የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ፕሬዘዳንት ከህወሃት የተቀሰረበትን ጣት ለማስነሳት ተገንጥየ ወደ ሶማሌ ሄጀ እቀላቀላለሁ ብሎ ለጊዜው ቢያስፈራራም ነገ የሚገጥመውን በጋራ የምናየው ይሆናል። እንግዲህ ይህን ያህል ካልኩ አቅሙና ጊዜው እንዲሁም መረጃው ያላችሁ ይህን መነሻ በማድረግ ጠንከር ያለ ጹሑፍ ታስነብቡን ይሆናል ብየ ተስፋ አደርጋለሁ። [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

ዘር ማጥራት ወይስ ኢህአዴግን ማፍረስ ? (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ )


ኢህአዴግ ያነበረውን ቋንቋንና ዘውግን መሰረት ያደረገ ፌዴራሊዝም አደገኛነት በተመለከተ በርካታ ምሁራን፣ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች… ሳያሰልሱ ለመምከርና ለማስጠንቅቅ መዋተታቸውን አልዘነጋሁም፡፡ እኔም ከ“ፍትህ” ጋዜጣ እስከ “ፋክት” መጽሔት ድረስ ችክ ያልኩበትም ሆነ ዛሬ በዚህ ተጠየቅ የተመለስኩበት ምክንያት ችግሩ እያደር እየተባባሰ በመምጣቱና ከምንጊዜውም በላይ አዘናግቶ ወደተፈራው የእርስ በእርስ እልቂት ሊዘፍቀን እየተንደረደረ በመሆኑ፣ ቅድሚያ ሰጥተን በሕብረ-ድምፅ ‘የሀገር ያለህ!’ ብለን መጮህ እንዳለብን ስለማምን ነው፡፡Temesgen Desalegn "Fact" Ethiopian Amharic newspaper editor
አርባ አራት ዓመት ወደኋላ…
በኢትዮጵያ የዘውግ ጥያቄ ለአደባባይ የበቃው በ60ዎቹ መጀመሪያ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ ከዘመነኞቹ የተማሪ እንቅስቃሴ መሪዎች ይህንን ጥያቄ አለቅጥ ለጥጦና አጋንኖ በማቅረብ ግንባር ቀደሙ ዋለልኝ መኮንን ነው፡፡ በ1962 ዓ.ም በአራት ገፅ ቀንብቦ ባዘጋጀው ታሪካዊ ጽሑፉ አማካኝነት “የብሔሮች ጥያቄ” ይፋ ሆኖ ለውይይት ከመቅረቡ በፊት፣ የተማሪው ዋነኛ የመታገያ አጀንዳ የመሬት ጉዳይ እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያወሳሉ (በደብዛዛውም ቢሆን ይንፀባረቅ የነበረውን መደብ ተኮር መንፈስ ሳንረሳ)፡፡ ዋለልኝ የሀገሪቱን መንግስታዊ አወቃቀርም ሆነ ባሕልን በአማራና በትግሬ ተፅእኖ ስር ስለመውደቁ በተቸበት በዚያ “ዝነኛ” ጽሑፉ ላይ እንዲህ ይላል፡-
“…ማንንም ሰው የኢትዮጵያውያን ቋንቋ ምንድን ነው ብላችሁ ጠይቁ፤ የኢትዮጵያውያን ሙዚቃ የቱ ነው ብላችሁ ጠይቁ፤ የኢትዮጵያውያን ባሕል የቱ ነው ብላችሁ ጠይቁ፤ ብሔራዊ ልብሳችሁ የቱ ነው ብላችሁ ጠይቁ፤ የአማራ ወይም የትግሬ ይላችኋል፡፡”
ይህ ሀቲት በወቅቱ በአብዛኛው ተማሪ ዘንድ ቁጣ ከመቀስቀሱም በላይ ዋለልኝን በ‹ፀረ-አማራና ትግሬነት› አስፈርጆ ለውግዘት ዳርጎት ነበር፡፡ እራሱም ቢሆን በአንድ የዩንቨርስቲው መድረክ ላይ የተሰነዘረበት ከባድ ተቃውሞ በፈጠረበት ብስጭት ‹‹እኔም አማራ ነኝ፤ ያውም ከአማራ ሳይንት-ቦረና›› ማለቱ ይታወሳል (ቦረና በተለምዶ አማራ መጥቶበታል የሚባለው አካባቢ መሆኑን ልብ ይሏል)፡፡ ግና፣ ዋናው ጥያቄ የእርሱ አማራ መሆን ያለመሆን አይደለም፤ እዚህ ድምዳሜ ላይ የደረሰበት ምክንያት ከተጨባጩ እውነታ ጋ ምን ያህል ይዛመዳል? የሚል ነው፡፡ ሌላው ነገር ደግሞ ከዚህ ጽሑፍ በፊት ብሔር ተኮር ጎዳዮችን አንስቶ ካለማወቁም በዘለለ፣ ሌሎች ሲያነሱ ፅንፈኛ ተቃዋሚ ስለነበረ ነው፡፡ ለምሳሌ ተማሪ ኢብሳ ጉተማ (ኋላ ላይ የኦነግ መስራችና አመራር የሆነው) ‹‹ኢትዮጵያዊ ማነው?›› በሚል ርዕስ ባቀረበው ግጥም እጅግ ተናድዶ ‹‹እንዴት እንዲህ አይነት ግጥም ታቀርባለህ? ዘረኛ ነህ፤ ኢትዮጵያውያንን የመከፋፍል ዓላማ ነው ያለህ?›› በማለት እስከመቃወም መድረሱ የክርክሩ አንዱ ጭብጥ ነው፡፡
ታዲያ ዋለልኝ መኮንን ድንገት እዚህ ድምዳሜ ላይ የደረሰው ከምን የተነሳ ይሆን? በርግጥ ለዚህ ድንገቴ የአቋም ለውጥ ሶስት መላ-ምቶች ሲነገሩ ቆይተዋል፡፡ የመጀመሪያው ‹በአፄው ሥርዓት ላይ አሴረዋል› ተብለው ከተከሰሱትና ‹ኦሮሞ እየተጨቆነ ነው› የሚል እምነት ከነበራቸው ጄነራል ታደሰ ብሩ ጋር በታሰረበት ወቅት፣ በጄነራሉ ስብከት አመለካከቱ ተቀይሮ ሊሆን ይችላል የሚለው ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ‹‹መገንጠልን መደገፍ በመጨረሻ የማትገነጠል ሀገር እንድትኖር ያደርጋል›› በማለት ከተከራከረበት ከራሱ አቋም ጋር የሚያያዝ ነው፤ ሶስተኛው ‹የሻዕቢያ (ኤርትራውያን ተማሪዎች) አሊያም የአሜሪካኑ የስለላ ተቋም (ሲ.አይ.ኤ) መጠቀሚያ ሆኖ ነው› የሚሉት ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ይሁንና ከዋለልኝ ጀርባ ‹ስውር እጅ›ን ለመፈለግ ያስገደደው በጊዜው ብዙሁ ተማሪ ለሀገሪቱ ዘርፈ-ብዙ ችግሮች ‹የንጉሣዊው አስተዳደር ኋላቀርነት እና ስግብግበነት ነው› ብሎ ከማመኑም ባለፈ፣ ከፌዴራላዊ ይልቅ የቻይና ኮሙኒስታዊ ሥርዓት አድናቂ የመሆኑ ጉዳይ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ የተማሪውን እንቅስቃሴ በመምራት በዘመኑ ከዋለልኝ የላቀ ተሰሚነት የነበረው ጥላሁን ግዛው ‹‹ጎሰኝነትን›› በአደባባይ አጥብቆ ይቃወም እንደነበረ፣ በ1968 እ.ኤ.አ የታተመው ‹‹Struggle›› ቅፅ 3፣ ቁጥር 1 መጽሔት ጋር ያደረገውን ቃለ-መጠይቅ መጥቀስ ይቻላል፡-
‹‹በመጀመሪያ ደረጃ በጎሰኝነትና በሶሻሊዝም መካከል ያለውን ልዩነት ማሳየት እፈልጋለሁ፡፡ ጎሠኝነት በተወሰነ አካባቢ ብቻ የሚቀርና አካባቢ ቀመስ ነው፡፡ ሶሻሊዝም ግን ዓለም ዓቀፋዊ ነው፡፡ …እንደ ዩንቨርስቲ ተማሪነታችንና እንደ እጩ ምሁርነታችን የሕብረተሰባችንን አቋም ከመደብ አንፃር መተንተን እንጂ በጎሣ መከፋፈል አይገባም›› ማለቱ ይታወሳልና፡፡
የህወሓት-ውልደት
ዋለልኝ መኮንንን ‹‹የብሔር ጭቆና›› ትንተናን መሰረት ያደረጉ ጥቂት የማይባሉ የፋኖ ድርጅቶች መመስረታቸው አይካድም፡፡ ከእነዚህም መንግስታዊውን ሥልጣን ለመጨበጥ የበቃው ህወሓት አንዱ ነው፡፡ የአማራና ትግሬ ጨቋኝነትን የሚያውጀው ጽሑፍ በተሰራጨ በአምስተኛው ዓመት የትግርኛ ተናጋሪውን ብሔራዊ ጭቆና ለማስረገጥ ጽሑፉን እንደ ሰነድ ማስረጃ ቆጥረው ‹‹ትግራይን ነፃ እናወጣለን!›› ያሉ ፋኖዎች ነፍጥ አንግበው በረሃ ቢወርዱም፣ በመጀመሪያዎቹ ጥቂት ዓመታት አካባቢ ‹‹እንታገልለታለን›› በሚሉት ዘውግ ተወላጆች ሳይቀር መናፍቅ ተደርገው መወገዛቸው ይታወሳል፡፡ ደራሲና ገጣሚ አስማማው ኃይሉም ‹‹ኢህአሠ›› በተባለው መጽሐፉ እንዲህ ይለናል፡-
‹‹በ1969 ዓ.ም አጋማሽ አካባቢ በእምባ ሰገንይቲ ወረዳ ነበለት አካባቢ ሽምዕጭ ተብሎ በሚጠራው መንደር የህወሓትና የኢሕአሠ አባላት ሕዝብን ለመቀስቀስ ተገኝተው ነበር፡፡ ሁለቱም ቡድኖች የድርጅታቸውን ዓላማ ካስረዱ በኋላ ያካባቢው አዛውንት ማሳረጊያውን ንግግር አደረጉ፡፡ አዛውንቱ መሔድ የሚሳናቸው ስለነበሩ ሰዎች ደግፈው ወደ በቅሏቸው እንዲያወጧቸው ከጠየቁ በኋላ የሚከተለውን ንግግር አደረጉ፡፡ ወደ ህወሓት አባላት እጃቸውን ዘርግተው ‹እናንተ ከሆዳችን የወጣችሁ ልጆቻችን ናችሁ›፤ ወደ ኢሕአሠ አባላትም ፊታቸውን አዙረው ‹እናንተ ደግሞ ከሁሉም የኢትዮጵያ ግዛት መጥታችሁ ለእኛ ስትሉ ነው የምትታገሉት፡፡ የሆነው ሆኖ እኛ የትግራይ ሰዎች ሆነን ስንቀር ኢትዮጵያ ከማን ጋር ልትቀር ነው? ስለሆነም እኛ ኢትዮጵያዊ ከሚል ጋር ነው የምንወግነው› ሲሉ ሃሳባቸውን ሰነዘሩ፡፡›› (ገፅ 235)
ህወሓት በትግራይም ሆነ በተቀረው የሀገሪቱ ክፍል የነበረውን አገዛዛዊ ጭቆና፣ የብሔር አስመስሎ እስከ መገንጠል ቢንደረደርም፣ የገጠመው ተቃውሞ ፕሮግራሙን ለመከለስ አስገድዶታል፡፡ ዘግይቶ ላገኘው ድጋፍም ቢሆን ከዘውግ ተኮሩ ተረት-ተረት ይልቅ አምባ-ገነናዊው የደርግ አስተዳደር የወለደው ሽብርና ጭፍጨፋ የተሻለ ጠቅሞታል፡፡ ለዚህም በዛሬይቷ ትግራይ ከሶስት ያላነሱ ፀረ-ህወሓት ድርጅቶች መኖራቸው ማሳያ ይሆናል ብዬ አስባለሁ፡፡
በሌላ በኩል ከህወሓት ምስረታ አንድና ሁለት ዓመት አስቀድሞ ወደ አደባባይ የመጡት ኢህአፓና መኢሶን የትግል አጀንዳቸው የመደብ ቅራኔ ላይ የተመሰረተ ነበር፡፡ ይህ ግን በወቅቱ ከህወሓትም በከረረ መልኩ ‹‹የብሔር ጥያቄ በመገንጠል ብቻ ነው የሚፈታው›› የሚል እምነት ተከታዩ ኦነግን ህልውና አያስክድም፡፡ እዚህ ጋ የምንመለከተው ሌላኛው ግራ አጋቢ ጉዳይ የመጀመሪያው የቀዳማዊ ኃ/ስላሴ ዩንቨርስቲ ተማሪዎችን የ‹‹መሬት ላራሹ››ን ሠልፍ (በ1957 ዓ.ም) አስተባብሮ የሕግ-መወሰኛው ምክር ቤት ድረስ የመራው ባሮ ቱምሳም (በአብዮቱ ሰሞን የኢጭአት የአመራር አባል ነበር) ሆነ፤ የመኢሶኑ ቁልፍ ሰው እንደሆነ የሚነገርለት ኃይሌ ፊዳን የመሳሰሉ የኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪ ልሂቆች፣ ከኦነግ በተቃራኒው ከብሔር ይልቅ የመደብ ጥያቄ አቀንቃኝ የነበሩ መሆኑን ነው፡፡ በነገራችን ላይ በግሌ ዛሬም ቢሆን ኢትዮጵያዊ ብያኔ እነዋለልኝ የለጠጡትንና ያጎኑትን ያህል እንኳ ባይሆንም እንደገና መከለስ እንደሚያስፈልገው አምናለሁ፡፡
የሆነው ሆኖ ህወሓት መንግስታዊውን ሥልጣን በጨበጠ ማግስት ‹የሰነበተውን የብሔር ቅራኔ በማያዳግም ሁኔታ የሚፈታ› ሲል ያንቆለጳጰሰውን ቋንቋ ተኮር ፌዴራሊዝም ቢተገብርም፤ ከዚሁ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ችግሮችን የመግታት አቅም እንደሌለው ለማረጋገጥ የአንድ እጅ ጣቶች ያህል ዓመታት እንኳን አልፈጀም፡፡ በደቡብ በጉጂ እና ጌዲዮ፣ በጉጂ እና ቡርጂ፤ በጋምቤላ በአኝዋክ እና ኑዌር፤ በቤንሻንጉል በጉምዝ እና በርታ መካከል የተከሰቱት የይገባኛል ግጭቶች በማሳያነት ይጠቀሳል፡፡
የፌዴራሊዝሙ ቀዳዳዎች
ዘውግ ተኮር ፌዴራሊዝሙ፣ ገና ከጠዋቱ ለከፋ ዕልቂት ሊዳርግ እንደሚችል በማስታወስ ይሰሙ የነበሩ የተራዘሙ ጩኸቶችን ችላ ብሎ ዛሬ ላይ ቢደርስም፤ ለፕሮፓጋንዳ በሸነቆራቸው ቀዳዳዎች እየገባ ያለው ከባድ ንፋስ ከራሱ አልፎ ሀገሪቷንም ከበታኝ አደጋ ፊት አቁሟታል፡፡ ለዚህም አገዛዙ የፈጠራ ትርክቱን ለማስረፅ የሄደበት የኑፋቄ መንገድ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡ በፓርቲው ካድሬዎች በኩል በየዕለቱ የሚዘራው የጥላቻ ፖለቲካ፣ ሐውልት ማነፅ፣ ከፋፍሎ ማቆም እና መሰል ስልቱ በተጨማሪ ሜጋ በሚያሳትማቸው መጻሕፍት እልቂት ጠሪ ዘውግ ተኮር ቅስቀሳዎችን እስከማሰራጨት መድረሱን ተመልክተናል፡፡ ለአብነትም የሚከተለውን ግጥም ልጥቀስ፡-

“ነፍጠኞች እቤታቸው በክብር ይጎለታሉ፣
እኛን በኃይል አስገድደው ያሰራሉ፣
ቁጥቋጦ እንደምትመነጥረው መንጥራቸው
ወደመጡበት ወደ ሸዋ አባራቸው፡፡”
 (“ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ” ቅፅ 3፤ ገፅ 145)
ግና ‹‹ሸዋ›› ሱዳን ወይም ግብፅ አይደለምና ዛሬ ከጉራፈርዳ እስከ ደንቢዶሎና ጊምቢ ለተተገበረው የማባረር ዘመቻ ዋነኛው ተጠያቂ የሥርዓቱ ኤጲስ ቆጶሳት መሆናቸውን ግጥሙ ያስረግጣል፡፡ በግልባጩ እነዚህ ሰዎች በ97ቱ ምርጫ ዋዜማ፣ ሚያዚያ 30 ቀን መስቀል አደባባይ ቅንጅት በጠራው ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ፣ አቶ በድሩ አደም ‹‹ወደመጡበት እንመልሳቸዋለን›› ማለታቸውን፣ ወደ ዘውግ ጥላቻ ከመቀየራቸውም በላይ፣ የቅንጅቱን አመራሮች ለቅመው ካሰሩ በኋላ የሰውየውን ንግግር ‹‹የዘር ማጥፋት ሙከራ!›› ሲሉ ለመሰረቱባቸው ክስ በማስረጃነት ማቅረባቸውን አስታውሳለሁ፡፡ በዚያው ሰሞን አቦይ ስብሃት ነጋም የብአዴን ጓዶቻቸውን ‹‹እኛ ወደመቀሌ ስንባረር፤ እናንተን መንዝ ላይ አራግፈን ነው የምንሄደው!!›› አሉ መባሉም ጉዳዩ በራስ ላይ ሲደርስ ምን ያህል አሳማሚ እና ለበቀል እንደሚያነሳሳ ሁነኛ ጥቁምታ ቢሰጥም፣ ገዥዎቻችን ትምህርት ሊወስዱበት አለመቻላቸው ያስቆጫል፡፡ እንዲያውም ከምርጫ 97 በኋላ በዩንቨርስቲዎች ግቢ የሚነሱ ተቃውሞዎች ዘውግ-ተኮር ወደመሆን ነበር የተሸጋገሩት፡፡ ኢህአዴግም ቢሆን በዩንቨርስቲዎች በተናጠል (በህወሓት፣ ብአዴን፣ ኦህዴድ እና ደኢህዴን) ስር ማደራጀት የጀመረው ከዚሁ ምርጫ በኋላ እንደነበረ አይዘነጋም፤ ለእንዲህ አይነቱ የፓርቲው ተልዕኮ ደግሞ እንደ ዶ/ር አድማሱ ፀጋዬ አይነት የገዥው-ፓርቲ መንፈስ የሰረፀበት ‹‹ምሁር›› ጠቀሜታን ለመረዳት አሁን አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ያለበትን ሁኔታ መቃኘቱ ብቻ በቂ ነው፡፡ በርግጥ ባለፉት ሁለት አስርታት የህወሓት አባልና ደጋፊ ተማሪዎች የግቢውን መንፈስ አይመረምሩም (አይሰልሉም) ነበር እያልኩ አይደለም፤ በግላጭ የጓደኞቻቸውን እንቅስቃሴ እየተከታተሉ ሪፖርት ያደርጉ ነበርና፡፡ በአናቱም የዘውግ ተኮር ፖለቲካው መተግበር በጀመረበት ወቅት ወደ ትምህርት ቤት የተላኩ ልጆች፣ ዛሬ ለዩንቨርስቲ መብቃታቸው፣ አጀንዳው በቅፅበት ሊፈፀም የመቻሉን እውነታ በኦሮሚያ ሰሞኑን የተመለከትነው ቀውስ በቂ ማሳያ ይሆናል፡፡
የተጭበረበረው አጀንዳ
‹የብሔር ጥያቄ ዋነኛው የቅራኔ ቅርፅ ነው› የሚለው ህወሓት ይህን ጥያቄ መፍታት ሥርዓታዊ ግብ እንደሆነ እስኪሰለቸን ቢደሰኩርም፤ አጀንዳውን ከማጭበርበሪያነት የዘለለ ዋጋ አልሰጠውም፡፡ እናም ታሪክ ቢያንስ በዚህ በኩል በበጎ እንደማያስታውሰው ለመናገርም ብዙ ማስረገጫዎችን መጥቀስ አይገድም፡፡ አሁንም ኢትዮጵያን እየናጣት ያለው፤ ጥያቄያችን አልተመለሰም› የሚሉ ብሔርተኛ ቡድኖች መበርከት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በስያሜ ደረጃ እንኳን (መሬት ላይ ያላቸውን ጉልበት ትተን) ከአስራ አንድ የማያንሱ ተገንጣይ ንቅናቄዎች መኖራቸው እውነት ነው፡፡ የእነዚህን ከኦጋዴን እስከ ጋምቤላ፤ ከቤንሻንጉል እስከ አፋር ድረስ ያሉ አማፅያን እንቅስቃሴን የጥቂት ልሂቃን ቅብጠት አድርጎ መውሰድ ርትዕ አይሆንም (ስለምን ቢሉ ደርግም ህወሓትን የሚያስበው እንዲያ ነበርና)፡፡ እናም ከትልቁ ኦሮሞ ጥያቄ መጠለፍ ጀምሮ፤ እነዚህ ጉዳዮች አስቀድሞ ግንባሩ የብሔር ጥያቄን ለሥልጣን መወጣጫ ብቻ ለመጠቀም ማስላቱን ይጠቁሙናል፡፡
ሌላኛው ጭብጥ አሁንም ድረስ ማንነት ተኮር ጥያቄዎች አለመቆማቸው ነው፡፡ ከቅማንት እስከ ወለኔ እና ቁጫ ድረስ ያሉት ‹‹ማንነታችን ታውቆ ዞን ይሰጠን›› ጩኸቶች ማቆሚያቸው የቱ ጋ እንደሆነ ራሱ ኢህአዴግም የሚያውቅ አይመስለኝም፡፡ በግልባጩ ለእነዚህ ሶስት የማህበረሰብ ክፍሎች ጥያቄ በቅርቡ የሠጠው ምላሽ ጭፍለቃ መሆኑን ስናስተውል፤ ‹ተነሳሁለት› ከሚለው የብሔር ጭቆናን ማጥፋት አኳያ የሚነግረን ሀቅ ሥርዓቱ የሄደበትን ቁልቁለት ብቻ ነው፡፡
በሶስተኛነት ከዚሁ ጋር አያይዘን ልናነሳው የምንችለው ርዕሰ ጉዳይ የመገንጠል መብት ነው፡፡ ከዋለልኝ እስከ ጥላሁን ታከለ እና ቱሞቱ ሌንጮ (ፕ/ር እንድሪያስ እሸቴ) ድረስ የነበሩ የዘመኑ ትውልድ መንፈስ ተርጓሚዎች መገንጠልን ሕብረ-ሱታፌ (ሶሻሊስታዊ) ሥርዓት ለመገንባት መዳረሻ መንገድ አድርገው ቢያቀርቡትም፤ ጥራዝ ነጠቆቹ ህወሓቶች ሕገ-መንግስቱ ውስጥ ቀርቅረውታል፡፡ ለዚህም እንደምክንያት ‹‹መገንጠልን ለመከላከል ነው›› ቢሉም፤ ከፌደራሊዝሙ አወቃቀር አኳያ ‹የማይተገበር መብት› ስለመሆኑ ብዙ ተብሏል፡፡ ይህንን ለማስረገጥ በዋናነት ሁለት ነጥቦች ይነሳሉ፤ ‹እንደ ስታሊኒስቷ ሩሲያ ሁሉ መብቱ በሕገ-መንግስቱ ውስጥ ቢካተትም፣ የማዕከላዊ መንግስቱ ሥልጣን ፍፁማዊ መሆን እንዳይተገበር ያደርገዋል› የሚለው የመጀመሪያው ነጥብ ነው፡፡ ሁለተኛው የመብት አፈፃፀሙ ራሱ በተለያዩ አስገዳጅ ተዋረዳዊ ትግበራዎች መጠላለፉ ነው፡፡ በተለይም ሁለትና ከዚያ በላይ ዘውጎችን ያቀፉ ክልሎች የመገንጠል ጥያቄ ቢያነሱ ተፈፃሚነት እንደማይኖረው ለመረዳት የክልሎቹን አወቃቀር መመልከቱ ብቻ በቂ ይመስለኛል፡፡ ከእነዚህ ሁለት ነጥቦች ስንነሳ የመገንጠል ግብ ያላቸው እንቅስቃሴዎች በትጥቅ ትግል አገዛዙን ካላስወገዱት በቀር በሕገ-መንግስቱ መሰረት በሰላማዊ መንገድ ሊተገበሩ አለመቻላቸውን እንገነዘባለን፡፡ ይህ ሁነትም ሥርዓቱ ቋንቋን መሰረት ያደረገ ፌዴራሊዝም ያነበረው ከፋፍሎ ለመግዛት እንጂ፤ እስክንደነቁር በጩኸት ስለሚነግረን ‹‹ጭቁን ብሔር ብሔረሰቦች›› መብት ደንታ ኖሮት እንዳልሆነ ያስረግጥልናል ብዬ አስባለሁ፡፡

ግን እስከመቼ?
በዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ከአፄ ኃይለስላሴ ቀጥሎ ረዘም ላለ ዓመታት ሀገሪቱን የመምራት ዕድል ያገኘው ኢህአዴግ የተሻለች ሀገር የመገንባት በርካታ ዕድሎችን አምክኗል፡፡ ወደሥልጣን በመጣ ማግስት ዘውገኝነትን የመንግስታዊ መዋቅሩ ብቸኛ ገፅ ሲያደርገው፣ ከብዙ ጫፎች ከተነሳበት ከባባድ ተቃውሞዎች መሀል፡- ቋንቋ ተኮር ፌዴራሊዝሙ ማሕበረ-ባሕላዊ መሰረቱ በጣም የተሳሳተ መሆኑን እና የዘውግ ማንነትን ብቸኛው የክልሎች ድንበር አሰማመር መነሻ ማድረግ ለእርስ በእርስ የዜጎች ትንቅንቅ ያጋልጣል የሚሉት ዋነኞቹ ነበሩ፡፡ ሥርዓቱ ይህን ጆሮ ሰጥቶ ከማዳመጥ ይልቅ ቢያፈገፍግም፣ ያሳለፍናቸው ሃያ ሶስት ዓመታት በሞቶችና በመከራዎች የተፃፉ ኩነቶችን አሳይተውናል፡፡ ‹‹ባለሥልጣን›› እና ‹‹ሥልጣን የለሽ›› (ባለቤትና መጤ) በሚል ጨዋታ፣ በየክልሎቹ የሚገኙ የሌላ ቋንቋ ተናጋሪዎች ከክልሉ የሥራ ቋንቋ ውጪ በመናገራቸው ብቻ፣ አንዳችም ተቋማዊ ውክልና እንዳያገኙ ማድረጉ፣ ከየአካባቢዎቹ በግፍ ለተፈናቀሉት የማሕበረሰብ ክፍሎች ዋነኛው መነሻ ሆኗል፡፡ አዲሱን የአዲስ አበባ የማስፋፊያ ዕቅድ ተከትሎ የተነሳው የኦሮሞ ተማሪዎች ተቃውሞም ሌላ ቅርፅ ወደመያዝ መሻገሩ አንዱ ሰሞነኛ ማሳያ ነው፡፡ በምዕራብ ወለጋ ለረዥም ጊዜ ኑሯቸውን መስርተው የነበሩት የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ መገደዳቸው የሚቀጥል ከሆነ ደግሞ፣ የአማራ ክልልን ጨምሮ የየክልሎቹ ዘውጎች ‹‹መጤ›› ያሏቸውን ማባረር ላለመጀመራቸው እርግጠኛ መሆን የምንችልበት ምንም አይነት ዋስትና የለንም፡፡ እናሳ! ይህ አይነቱ ክልልን ከ‹‹መጤ›› ዘውግ የማንፃት ሂደት ማቆሚያው የቱ ጋ እንደሆነ ማን ሊገምት ይቻለዋል? ዘግናኝ ደም መፋሰስስ ሳያስከትል ይህንን ክፉ ድርጊት መሻገር የምንችለው እንዴት ነው?
እንግዲህ ይህ ሁሉ የፍርሰት መርዶ እየተሰማ ያለው፣ የሥርዓቱ ሰዎችና የጥቅም ተጋሪዎቻቸው ለዚህ ከፍታ የበቁበትን ሃያ ሶስተኛ የድል ዓመት በፌሽታ ለማክበር ደፋ ቀና በሚሉበት ዋዜማ ላይ ቆመን ቢሆንም ‹‹ጊዜው ከቶም ቢዘገይ አልረፈደም›› እንዲሉ፤ ተገፍቶ ገደል ጠርዝ የተንጠለጠለውን የኢትዮጵያን ህልውና በደለደለ መሰረት አፅንተን ለቀጣዩ ትውልድ ለማሻገር አንዳች እርምጃ መውሰዱ ብቸኛ አማራጭ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ለዚህ ዘመን ለጣለው ትውልዳዊ የማንነት ዕዳ ክንውን ቀዳሚው ተግባር ኢህአዴግን ‹‹በቃህ!›› ብሎ ማስቆም እንደሆነም መቀበል የሚያስቸግር አይመስለኝም፡፡ ግና፣ ይህ ሳይሆን በወታደራዊ ጡንቻ ካሳለፍናቸው ዓመታት ጥቂቱን እንኳ እንዲሰነብት ከፈቀድንለት፣ የደም ባሕር ሲያጥለቀልቀን ቆመን ለመመልከት ተስማምተናል ማለት ነው፡፡
Source Ethiomedia

The “Farce” of U.S. Diplocrisy


Is the Obama Administration’s human rights policy a “farce”?
Last week U.S. Secretary of State John Kerry called Syrian president Bashar al-Assad a “terrorist” criminal and called Assad’s electoral plans a “farce”. “Assad’s is making partnership with terrorist elements, attracting terrorists and engaging in terrorist activities against his own people.” Assad’s planned presidential elections are “staged elections [that] are a farce. They’re an insult. They are a fraud on democracy, on the Syrian people and on the world.”President Barack Obama and his Human Rights policy
I do not doubt that Assad is a scourge on the Syrian people and one of the top five criminals against humanity in the Twenty-First Century. In May 2007, in a single-candidate referendum, Bashar was “elected” president for a second seven-year term “winning” 97.6  percent of the votes. At that time, State Department spokesman Sean McCormack said, “The United States is concerned by reports that the Syrian regime has used intimidation to restrict the candidate pool and threats of reprisal to discourage political dissent. President al-Assad is again denying the right of the Syrian people to an open, transparent and fully participatory political environment.” There is nothing new about Assad’s “farcical staged elections”.
In March 2011, former U.S. Secretary of State Hillary Clinton defended the bloodthirsty Assad (who massacred thousands of Syrian civilians using chemical weapons at least 14 times since last October).  “There is a different leader in Syria now. Many of the members of Congress of both parties who have gone to Syria in recent months have said they believe he’s a reformer.” In less than three years, Assad the “reformer” had morphed into Assad the “terrorist” and genocider.
Kerry’s condemnatory words against Assad raise parallel questions in my mind. Could it be reasonably said that the Obama Administration’s human rights policy is diplomatically “staged” and a “farce”? Is it a “fraud [perpetrated] on the world”? Is it “an insult to humanity” and human rights? Does the Obama Administration practice human rights diplomacy by hypocrisy or “diplocrisy”, (a neologism I coined to describe the barefaced hypocrisy of the Administration’s global human rights policy)? One should be careful pointing an accusatory index finger at others unmindful that three fingers are pointing at him.
In April 2013, Secretary Kerry dismissed the election of Nicolás Maduro as president of Venezuela. Maduro won that election by a razor thin margin of 50.66 percent of the votes. When opposition leader Henrique Capriles demanded a recount, Kerry chimed in. “We think there ought to be a recount… Obviously, if there are huge irregularities, we are going to have serious questions about the viability of that [Maduro] government.” White House spokesman Jay Carney also issued a statement calling for a recount of all the votes.
When Zimbabwe held its presidential election in August 2013, Kerry said, “Make no mistake: in light of substantial electoral irregularities reported by domestic and regional observers, the United States does not believe that the results announced today represent a credible expression of the will of the Zimbabwean people… The balance of evidence indicates that today’s announcement was the culmination of a deeply flawed process.” Mugabe “won” that “election” by 61 percent of the votes.
In May 2010 when the late Meles Zenawi claimed 99.6 percent victory in the parliamentary elections, the U.S. brushed it off with the obligatory expression of “concern” and “disappointment”. White House National Security Spokesman Mike Hammer said, “We are concerned that international observers found that the elections fell short of international commitments. We are disappointed that U.S. Embassy officials were denied accreditation and the opportunity to travel outside of the capital on Election Day to observe the voting.  The limitation of independent observation and the harassment of independent media representatives are deeply troubling. An environment conducive to free and fair elections was not in place even before Election Day…” Was the 2010 “parliamentary election” in Ethiopia a “staged election that was a farce”? Was it “an insult and a fraud on democracy, on the Ethiopian people and on the world”?
I admit that there could be no beauty contest among warthogs but it is noteworthy that the U.S. condemned  Bashar for “winning” the presidency  by 97.6  percent of the votes in a single-candidate referendum while turning a blind eye to Meles Zenawi’s  parliamentary electoral victory  by 99.6 percent in a “multiparty election”.
Understanding the Obama human rights doctrine
The Obama doctrine on human rights seems pretty straightforward. Human rights policy making is essentially a choice between the lesser of two (d)evils. The world is full of nasty “S.O.Bs” like Assad, Mugabe and Maduro who commit crimes against humanity. Then there are nice “S.O.Bs” like Egypt’s el-Sisi, Uganda’s Museveni, Rwanda’s Kagame and the late Meles Zenawi who commit crimes against humanity as a pastime. The difference between the two sets of (d)evils is that the latter are our “S.O.B.s”. They do our bidding. IN return, they get free passes. We give them billions of dollars in handouts every year.
In 2008, candidate Obama lamented the pervasive “cynicism” in the “conventional foreign policy thinking in Washington”. He said “one of the enemies we have to fight [is] not just terrorists,…  it’s also cynicism.” Six years into his presidency, Obama’s supporters in the human rights community believe he has thrown them right under the Cynicism Bus. Ken Roth, the executive director of Human Rights Watch, recently observed, “President Obama has disappointed many by failing to make human rights a priority.” His “readiness to compromise” on critical human rights issues “leaves the impression that he is not committed to the human rights ideal.” It seems Obama has forgotten “that people around the world share a common desire for freedom and respect for their rights.”
When President Obama visited Accra, Ghana in 2009, he told young Africans that “History is on the side of brave Africans’. He assured them, “You have the power to hold your leaders accountable, and to build institutions that serve the people.” Recently, Obama had a chance encounter with one of those young and brave Africans from Ethiopia who reminded him of the high price exacted by the “enemy” called “cynicism”. At a San Jose, California fundraiser, Ethiopian-born journalist and activist Abebe Gellaw had the following exchange with  President Obama as posted on the official White House website:
[Abebe Gellaw] AUDIENCE MEMBER:  President Obama!  Freedom for Ethiopia!  Freedom!  Freedom for Ethiopia, sir!
THE PRESIDENT:  Hold on.  I agree with you, although why don’t I talk about it later because I’m just about to finish.  (Laughter.)  You and me, we’ll talk about it.  I’m going to be coming around.
[Abebe Gellaw]AUDIENCE MEMBER:  (Inaudible)–
THE PRESIDENT:  There you go.
[Abebe Gellaw] AUDIENCE MEMBER:  (Inaudible) –
THE PRESIDENT:  I agree with you.
[Abebe Gellaw] AUDIENCE MEMBER:  (Inaudible.)
THE PRESIDENT:  I want to hear from you.
[Abebe Gellaw] AUDIENCE MEMBER:  We love you!
THE PRESIDENT:  I love you back.  You kind of screwed up my ending, but that’s okay.  (Laughter and applause.)  That’s okay. And we’ve got free speech in this country — (applause) — which is great, too.
Thank God we have freedom of speech in America. An ordinary journalist and human rights activist can stand up and freely  speak up to the President of the United States without fear of arrest, detention, persecution or torture. Bothe President Obama and Abebe were speaking in the same sentiments. President Obama joked that Abebe had “screwed up the ending” of his speech. Abebe was seriously protesting that Obama’s policy had “screwed up” his country of birth.
The important fact is that the most powerful man in the world and an ordinary citizen could face off on the world stage because they both believe in freedom, particularly the freedom of speech. IN contrast, the millions of Abebe Gellaws in Ethiopia for whom  Abebe Gellaw lifted his voice in San Jose do not have freedom of speech or of religion, or the right to assemble or petition for grievances. That’s is why Abebe shouted out, “President Obama!  Freedom for Ethiopia!”
I do not doubt that President Obama agrees there should be freedom of speech and other freedoms in Ethiopia and elsewhere in Africa. The question is the disconnect between his lofty words of freedom and his unwavering support for African dictators. If Obama truly believes in freedom of speech in Ethiopia, why doesn’t he (or his Secretary of State, ambassadors and representatives) exercise his freedom of speech and call for the release of imprisoned Ethiopian journalists and bloggers such as  Eskinder Nega, Reeyot Alemu, Woubshet Taye, Asmamaw Hailegeorgis, eelancers Tesfalem Waldyes, Edom Kassaye, Abel Wabella, Atnaf Berhane, Mahlet Fantahun, Natnail Feleke, Zelalem Kibret, and Befekadu Hailu, to name just a few.
Obama surely must know freedom ain’t free. Talk of freedom is cheap. It is a dime a dozen. Freedom is priceless; and in Ethiopia freedom comes at an extremely high price in Ethiopia. Eskinder Nega, Reeyot Alemu, Woubshet Taye and the others are paying up for their freedom by sacrificing their liberties. They languish in jails that are an insult to humanity; their very existence is a crime against humanity. Nearly 200 unarmed protesters in 2005 paid for their freedom with their lives. Tens of thousands paid for their lived over a quarter century of tyranny. Their killers today cling to the highest offices in the land. It is no exaggeration to say Obama keeps them in office by handing them billions of dollars every year. Dambissa Moyo, the noted African economist and author of “Dead Aid” reports that, “in Ethiopia a whopping 97 percent of the government’s budget derives from foreign aid.” The U.S. is the sugar daddy of the dictatorial regime in Ethiopia! Ninety million Ethiopians today are paying for their basic humanity by suffering the indignities, injustice and abuse of a gang of vicious thugs and corrupt ignoramuses palming themselves off as leaders.
It is impossible to distinguish between Obama’s human rights policies and principles from his human rights palaver. He drew an imaginary “red line” for Assad and told him not to cross it by using chemical weapons of mass destruction against the Syrian people. Just over the past several months, Assad has used such weapons at least 14 times.  For African dictators, Obama has given them the green light to go through the red light of human rights criminality.
If the Obama Administration does not have true commitment to enforcement of human rights principles, why does it bother to make grandiose statements that create the audacity of hope in the minds and hearts of millions of oppressed peoples throughout the world? Does the Administration believe that people are stupid and dumb and are unable to see the incongruity between his words and actions? Why does Obama make statements on human rights that make him look duplicitous, hypocritical and cynical? Could it be that Obama really believes that African thugtators in time will be born again into liberal democrats with the proper amount of human rights evangelization? Do dandelions grow up to be roses?
A proposal for a U.S. human rights and human wrongs policy
Obama is said to be a “realist” in foreign policy. His “Realpolitik” subordinates moral and political values to strategic national interests and practical considerations. In other words, he will talk a good human rights and human wrongs talk, but when push comes to shove, he will sacrifice human rights at the altar of human wrongs. He will talk about  ending tyranny and establishing democracy in the world but never at the cost of short-term narrow conceptions of American national interest.
As a realist, Obama must formulate a “U.S. human wrongs policy”, at least for Africa, founded on the principle that given the massive and unending violations of internationally recognized human rights in Africa, the U.S. could not realistically formulate and implement a human rights policy.  The basic tenets of a “realist” “U.S. human wrongs policy” would be based on the following simple propositions:
Africa is simply not worthy of human rights as imagined or                        practiced in the West.
“Stability and peace” are the utmost and paramount concerns of U.S. policy in Africa. Crimes against humanity by African leaders will be ignored to the extent that such crimes could result in destabilization and conflict. (For instance, Silva Kir and Reik Machar in South Sudan will be absolved of any liability for all of the crimes they committed including murder, extermination, forcible transfer of population, imprisonment, torture, rape and ethnic genocide.)
Stealing elections, corruption and abuse of power in Africa will be tolerated so long as African regimes fully support U.S. global and regional interests including the U.S. “war on terror”.
Franklin D. Roosevelt’s four essential freedoms for people “everywhere in the world” are no longer applicable to Africa. Roosevelt’s vision for the principles of U.S. engagement with a brave free world facing the darkness of tyranny shall be modified and qualified. “We look forward to a world founded upon four essential human freedoms. The first is freedom of speech and expression—everywhere in the world (except in Africa). The second is freedom of every person to worship God in his own way—everywhere in the world (except in Africa). The third is freedom from want—which, translated into world terms, means economic understandings which will secure to every nation a healthy peacetime life for its inhabitants—everywhere in the world (except in Africa). The fourth is freedom from fear… [so]  that no nation will be in a position to commit an act of physical aggression against any neighbor—anywhere in the world (except in Africa).
Eleanor Roosevelt’s Universal Declaration of Human Rights and all of the other human rights conventions that have been spawned by the Declaration shall be practiced everywhere in the world, except in Africa.
I believe a real realist and practitioner of “Realpolitik” in U.S. human rights policy will openly embrace the foregoing principles of a U.S. human wrongs policy. Human rights advocates and human rights abusers will have a clear understanding of U.S. values, principles and policies in Africa. There will be no misunderstandings and miscommunications about the intentions or aims of U.S. policy in Africa. Human rights advocates will have little to say on a U.S. human wrongs policy. They will have to bite their lips. Most of all, Africa’s dictators will get the just recognition they deserve for their loyal service. The U.S. cannot pretend not to know them the morning after the sleepover.
Professor Alemayehu G. Mariam teaches political science at California State University, San Bernardino and is a practicing defense lawyer.
Previous commentaries by the author are available at:
Amharic translations of recent commentaries by the author may be found at:

Exiled Ethiopian church convenes in Oakland


OAKLAND — Bishops from one of the world’s oldest Christian churches gathered in the Oakland hills for a four-day summit last week, hoping to sort out their differences as they shepherd an East African denomination to new lands.Mekane Selam Medanialm Ethiopian Orthodox Cathedral in the Oakland hills
The gathering was “to talk about the next generation, the one in the United States, what we have to do for them,” said Palo Alto resident Benyam Mulugeta, president of the board of Oakland’s Ethiopian Orthodox Tewahedo Mekane Selam Medhane Alem Cathedral. “We don’t want to lose the next generation.”
Exiled Patriarch Abune Merkorios was scheduled to preside over the convening of the Holy Synod, but the elder church leader fell sick shortly before his flight to the Bay Area.
Merkorios was dethroned and replaced amid Ethiopia’s political turmoil of the 1990s, but still has a worldwide following of Ethiopian emigrants who consider him the true spiritual leader of an institution that dates back to the 4th century.
Merkorios lives in New Jersey. A rival patriarch and institution continue to be seated in the Ethiopian capital of Addis Ababa.
Clergy from Australia, Canada, Germany, South Africa, Sweden and across the United States gathered at the Mountain Boulevard cathedral last week from Wednesday through Saturday.
Ethiopian Orthodox Christians say they hope to establish the kind of American footprint that Greek and Russian Orthodox churches began more than a century ago, building their own church buildings and monasteries and appealing to younger, U.S.-born congregants who grow up speaking English.
Hosting the convention was 90-year-old Abune Melketsedek, who heads the Oakland cathedral and is also the general secretary for the exiled church. Bishops and congregants were seen tearfully hugging on Friday after resolving some internal disputes over church policies.
“It’s one of the big events of our church,” Mulugeta said of the meeting.
Inside Bay Area News

Ethiopia: Journalists are not terrorists


Reporters Without Borders has learnt today that the court in Addis Ababa granted the police investigating the case against the 6 bloggers and three journalists, 28 more days for further investigations. The police notably claimed they were unable to access the Facebook and Twitter accounts of the detainees, which were reportedly disabled after the hearing on May 7th and 8th.Zone 9 bloggers complained of sever torture
According to the Eastern Africa Journalists Association ’s Secretary general, Alexis Niyungeko. “The request by the police for more time to conduct further investigations clearly shows that the three journalists and six bloggers were arrested without sufficient evidence”.
Following today’s hearing, the news providers are now being officially charged under thecountry’s infamous anti-terrorism proclamation of 2009, which can carry imprisonments sentences from 5 to 10 years.
During today’s hearing, a witness said that Zone9 blog member Atinaf Berhanecomplained of sever torture and interrogation throughout the night. The detainees were able to see their lawyers for the first time on May 14th and May 16th, according the defense lawyer Amha Mekonnen. The next hearing is scheduled for June 14th.
Reporters Without Borders

Silencing the Zone9 by hook or crook


by Hindessa Abdul
It has been over three weeks since close to a dozen journalists and bloggers were arrested, most of whom members of the blogging collective known as Zone 9. Their site, hosted in Google’s Blogger platform, was launched two years ago with a catching motto “We blog because we care.” They coined the name after a visit to the Zone 8 of the Kaliti prison, where a fellow journalist, Reeyot Alemu, is serving a five year sentence. Zone 9 is a metaphor to say the rest of the populace is also in jail but in a different cell block. No surprises, their page was blocked within weeks of its launch.An Ethiopian court granted police 10 more days to investigate six bloggers and journalists
Abel Wabela, Asmamaw W/Giorigis, Atnaf Berhane, Befekadu Hailu, Edom Kassaye, Mahlet Fantahun, Natnael Feleke, Tesfalem Weldyes, Zelalem Kebret have been locked up in the notorious Maekelawi in the north of Addis, where the tradition of torture is well alive and kicking.The bloggers were public servants,university professors,information technology professionals, full time journalists so on and so forth.
As it has become absurdly the norm, police had detained then started to investigate the alleged crimes, dashing the hopes of a speedy trial. So far the broad allegations are: working with a foreign organization that claim to be human rights group; conspiring to incite violence via the social media. An advisor to the Prime Minister put it as “criminal activities” without delving into specifics. Police have requested more time to investigate. The courts have no problem granting the wishes of the police at the expense of the detainees.
Some papers that came out in the last couple of days said, weeks after the arrest nobody knows the reason for their detention. However piecing together the words of police and close associates of the ruling party , there are clues to indicate where this thing is going to end up.
The dots
At the beginning of April, security officials detained Patrick Mutahi, a Kenyan national and a staff of Article 19 – a London based rights group working for the defense of freedom of expression — at the Bole International Airport. His earlier visits to the country (said to be five times) have been closely monitored.
Ironically Patrick’s travel to Ethiopia was related to a training on security and safety. Talking of safety, media watchdog groups train journalists in various skills. In recent years, with governments filtering the web, the subject of circumnavigating censorship; concealing the location from where blogs are posted have gained traction. Back in the early days of Internet filtering, the Paris based Reporters without Borders produced a famous manual called Handbook for Bloggers and Cyber-dissidents to help protect journalists in otherwise unfriendly political systems.
While Patrick was deported back to his country after a day in custody, his cell phone was confiscated, leaving behind a trove of information.
Enter HRW
In March of this year Human Rights Watch published a report on the state of surveillance in Ethiopia. The 100 page report entitled: ‘They Know Everything We Do: Telecom and Internet Surveillance in Ethiopia’ explains how security officials willy-nilly eavesdrop on the phone conversation of citizens. Here is a witness telling his encounter in the report:
“After some time I got arrested and detained. They had a list of people I had spoken with. They said to me, “You called person x and you spoke about y.” They showed me the list—there were three pages of contacts—it had the time and date, phone number, my name, and the name of the person I was talking with. “All your activities are monitored with government. We even record your voice so you cannot deny. We even know you sent an email to an OLF [Oromo Liberation Front] member.” I said nothing.”
Hence, the call log in Patrick’s phone will reveal all the individuals he had contacted. No matter what the conversations, it would be construed in a way that justifies the government’s paranoia.
TPLF insiders
A day after the detention of most of the suspects, Mimi Sebhatu, a close confidant of the Meles-Azeb family went on to her radio station and said the suspects had contact with Article 19. Mimi may have an inside knowledge not least because of her association with the inner circle as to her family’s history in the lucrative security business in the country.
In the closed court appearance police told the judges that some of the suspects travelled to Kenya and have received money and training from a human rights group. Police stopped short of mentioning who the rights group was.
TPLF run online media in North America are having a field day attacking Article 19 and the bloggers. They call the group “a neo-liberal extremist organization for hire, created for the sole reason of overthrowing democratically elected governments.” And the bloggers are guilty even before they are formally charged. “It’s a criminal act to make Addis Ababa turn into Ukraine’s Kiev for the sake of money, by working with the likes of ‘Article 19’ Eritrea and Egypt,” opined one.
So there should be no doubt as to what the charges will be associated with. The insiders have told us in no uncertain terms that it is all about Article 19. We, surly, will stay tuned.