Saturday, April 27, 2013

ኦባማ አርፍደው ወደ ኢትዮጵያ? “በአፍሪካ ብዙ ስራ አለን” ጆን ኬሪ

    

በአፍሪካ ህብረት 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ከሚገኙት የተለያዩ እንግዶችና ባለስልጣናት በተጨማሪ አራት ታላላቅ መሪዎች እንደሚገኙ እየተነገረ ነው። በዋናነት የሚጠቀሱት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ኦባማ ሲሆኑ፣ የቻይና አቻቸውም ዋናውና ታላቁ እንግዳ እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ባለፈው ረቡዕ ለአሜሪካ ኮንግረንስ ኮሚቴ የተናገሩትን በመጥቀስ ዜናውን የላኩልን ክፍሎች እንዳሉት ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ ሊያመሩ ይችላሉ።
ውጪ ጉዳይ ሚ/ሩ ኦባማ ኢትዮጵያ ስለመሄዳቸው ፍንጭ ቢሰጡም ስለጉዞው ዝርዝር አለመናገራቸው ታውቋል። የቻይና በአፍሪካ ሚና መጉላት ውሎ አድሮ የጠዘጠዛት አሜሪካ፣ በመጪው ወር በሚካሔደው የአህጉሩ 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ በፕሬዚዳንቷ ለመወከል መወሰኗ “ጉባኤ አድማቂ” አሰኝቷታል።
“በአፍሪካ ብዙ የምንሰራው ስራ አለን” ሲሉ የተናገሩት ኬሪ “በድግሱ” ላይ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል። እየተጣጣመ የመጣው የአፍሪካና የቻይና ፍቅር እንዲሁም ቻይና በአፍሪካ ያላት ሰፋ ያለ ኢንቨስትመንት ለአሜሪካ አሳሳቢ ከመሆኑ ባሻገር ቻይና የምትከተለው የንግድ ስልት በአጠቃላዩ ሁኔታ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩን ውጪ ጉዳይ ሚ/ር ኬሪ አልሸሸጉም፡፡ ዝርዝር ከመስጠት ቢቆጠቡም ጉቦ፣ ሙስና፣ አምባገነኖችን መርዳት በማለት የተወሰኑትን በግልጽ ከመጥቀስ አላለፉም፡፡
ኦባማም ወደ ኢትዮጵያ የሚያቀኑበት ጉዳይ አሜሪካ በአፍሪካ ለምትከተለው አዲስ እቅድ ማጠናከሪያ ካስማ ለመቸንከር እንደሆነ አብዛኞች ይስማሙበታል። “ቻይናን በቅርብ ሆኖ መቆጣጠር” በሚለው መርህ የአፍሪካን አምባገነኖች ወታደራዊ ድጋፍ በመስጠት ልቡናቸውን የመስለብ እቅድ ይዛ እየሰራች ያለችው አሜሪካ፣ የቻይናና የአፍሪካ ግንኙነት “የፓለቲካ እባጭ” የሆነባት ቻይና ድፍን የአፍሪካ መሪዎችን ቤጂንግ ጋብዛ ወዳጅነቷን አደባባይ በማውጣት ጸሐይ ካስመታቸው በኋላ ነበር። በርካታ መረጃዎችም በዚሁ ዙሪያ ቀርበዋል።
በቤጂንጉ ጉባኤ ቻይና ዶላር ለሚናፍቁት የአፍሪካ መሪዎች ብድር ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ፣ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት፣ የቴክኖሎጂ፣ የመንገድ ግንባታ፣ የተለያዩ ርዳታዎች ለማድረግ፣ ከዚህም በላይ አምባገነኖች የስለላ መዋቅራቸውን እንዲያደራጁ የሚያስችላቸው በገሃድ እንዳይሰራጩ የተከለከሉ የአፈና መሳሪያዎችን ጭምር ለመስጠት ቃል ገብታ አፍሪካን የገበያዋ ሳሎን ስታደርግ አሜሪካና አውሮፓውያኖቹ ደነገጡ፤ ታመሙ።
በተመሳሳይ ቻይና ዘይትና የተለያዩ ማዕድኖችን ከአፍሪካ በመዛቅ የገበያ ድሯን ዘርግታ አፍሪካን ተጣባቻት። ዜጎቿንና የንግድ ተቋሞቿን አፍሪካ ምድር በትና ከላይም ከታችም ተቆጣጠረቻት። ከዚህ በኋላ ነበር መቀደሟ ያሳሰባት አሜሪካ ቻይናን በቅርብ መከታተል በሚል አዲስ ስልት የነደፈችው።
ባለሙያዎችና የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት አሜሪካ በኢኮኖሚና በገንዘብ ድጋፍ የአፍሪካን ሆዳም መሪዎች በማባበል ቻይናን ለመፎካከር በዛሬው ጊዜ አይቻላትም፤ በገሃድ እከተለዋለሁ የምትለውን ግብዝ ፖለቲካ ያበላሽባታል። እንደውም አታስበውም። ለዚህ ይመስላል የአፍሪካ አገሮችን ወታደራዊ ሃይል በማሰልጠን፣ በማደራጀት፣ በማስታጠቅ፣ የየአገራቱን ወታደራዊ እዝ ከበላይ ሆኖ በመምራት የቻይናን እንቅስቃሴ ለመበርበር የተንቀሳቀሰቸው። (ከዚህ በፊት “የኦባማ አስተዳደር መጪው የአፍሪካ ዕቅድ” በሚል የጻፍነውን እዚህ ላይ ይመልከቱ)
አምባገነኖች የመከላከያ ኃይላቸውን እንደ ብረት ለማጥበቅ ካላቸው የጸና ፍላጎት አንጻር አሜሪካ የነደፈችው ስልት የተዋጣለት እንደሆነ የሚናገሩ ክፍሎች “አሁን አሜሪካ ወታደራዊ ሃይልን ለማጠናከር በሚል ወደ አፍሪካ የገባችበት ስልት፤ ከአፍሪካ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች እውቅና ውጪ የሚፈጸም ተግባር ስለሌለ መረጃ የማግኘት አቅሟ የቻይናን መስኮት በርግዳ ሳሎኗን የማየት ያህል ነው” ይላሉ፡፡
አሜሪካ አሁን ባለችበት ደረጃ አፍሪካ 50ኛ ዓመት በዓል ስታከብር በይፋ ባይረጋገጥም ኦባማ የመገኘታቸው ሚስጥር ከፖሊሲያቸውና ቻይናን በቅርብ ሆኖ ከመቆጣጠር አዲሱ ስልታቸው በመነሳት እንደሆነ የማያሻማ ነው። በጉባኤው ላይ አራት ከፍተኛ የአገር መሪዎች እንደሚገኙ የኢህአዴግ አንደበት ፋና ጠቁሟል ግን ዝርዝር አላቀረበም። ጆን ኬሪ “ከአፍሪካ ጋር ባለን ግንኙነት ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመሙላት ከአህጉሪቷ ጋር ያለንን ግንኙነት ለማሻሻል እንሰራለን” ማለታቸውን ፋና ምንጭ ሳይጠቅስ አስፍሯል።
ፋናም ሆነ ሌሎች የመንግስት ሚዲያዎች ይፋ ባያደርጉትም የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ባለስልጣናትና የአገሪቱ ፕሬዚዳንት የስብሰባው ታላቅ እንግዳ እንደሚሆኑ ፖለቲከኞች ቅድመ ግምታቸውን አኑረዋል። በኢህአዴግ ጉባኤዎች ላይ የክልል አንድ ልዩ ዞን ተወካይ እስኪመስል ልዑክ በመላክና የቻይንኛ ቀረርቶ በማሰማት ተሳትፎ ያላት ቻይና ለአፍሪካ ህብረት ታላቅ ስጦታ ማቅረቧ የሚታወስ ነው።
የአፍሪካ ኅብረትን ዘመናዊ ህንጻ በራስዋ ወጪ ያስገነባቸው ቻይና በቤቷ፤ ኦባማም ከተገኙ በእንግድነት የኅብረቱን የምስረታ ዘመን አስመልክቶ ቻይና በነጻ ገንብታ ባስረከበችው ህንጻ ውስጥ ሆነው ህንጻውን እያደነቁ ይደሰኩራሉ።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

ዛሬም የኢትዮጵያ ሙስሊም ድምጹ ከፍ ብሎ ሲሰማ ነበር!


‹‹313 ሚሊዮን ብሩን ለልማት!›› ሲል ዋለ!!!

በእርግጥ ጥያቄው ትላንትም ዛሬም አንድ ነው፡፡

ድምፃችን ይሰማEthiopian Muslims latest protest, Addis Ababa Ethiopia
የሃይማኖት ነጻነትና እኩልነት መሰረታዊ ከሚባሉ የሰው ልጅ መብቶች ይመደባል፡፡ ‹‹መንግስት እምነታችን ላይ በጀመረው ኢፍትሀዊ ዘመቻ ነጻነታችንን ነፈገን! ሃይማኖታቸንን በግድ ሊያስለውጠን እየሞከረ ነው! ድምጻችን ይሰማ!›› በሚል ለመብቱ ሲታገል የነበረው የኢትዮጵያ ሙስሊም አደባባይ መዋል ከጀመረ ብዙ ጊዜ ሆነው፡፡ በዚህ ሁሉ ጊዜ ውስጥ በርካታ መስዋእትነቶች እና ዘርፈ ብዙ የመብት ጥሰቶች ከትግሉ ሊያስቆሙት አልቻሉም፡፡ አሁንም ጠንክሮ እግሮቹን አደላድሎ ‹‹ለመብቴ በሰላማዊነት እታገላለሁ›› የሚል ቁርጠኝነቱ እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ አልመጣም፡፡ ከትግሉ መጀመር አንስቶ እለተ አርብ ለሙስሊሞች ብዙ አደጋን ያዘለች፣ በርካቶች የሚደበደቡባት፣ በርካቶች የሚታሰሩባት፣ በርካቶች በግፍ የሚጉላሉባት ብትሆንም ህዝበ ሙስሊሙ ግን በጉጉት ይጠብቃታል፡፡ ለምን? ለመብቱ የሚታገልባት፣ ድምጹን የሚያሰማባት፣ ህመሙን የሚተነፍስባት እለት ስለሆነች ነው! በማንነቱ ተከብሮ የመኖር መብቱን የሚጠይቅባት ቀን ስለሆነች ነው፡፡ ለዚያም አይደል በየጁሙአዎቹ የህዝቡ ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ ሲሄድ የምናየው?
እንደወትሮው ሁሉ የዛሬዋም ጁምአ በሙስሊሞች ተቃውሞ ደምቃ፣ በፍትህ ጥሪ ተንቆጥቁጣ ነው የዋለችው፡፡ በአገሪቱ የተለያዩ ከተሞች ደማቅ ተቃውሞዎች ተካሂደዋል፡፡ እጆች ለዱአ ተዘርግተዋል፡፡ ወንድማማችነት እና አንድነት፣ የአላማ ጽናት እና ቁርጠኝነት ገኖ የወጣባት ከብዙ ያማሩ ጁምአዎች መካከል ደምቃ የወጣች ጁምአ ነበረች፡፡ በዚህች ቀን መንግስት በማን አለብኝነት የአህባሽን ስልጠና እንደአዲስ ለማስቀጠል 313 ሚሊየን ብር በጀት መድቦ ከመጅሊስ ጋር ስምምነት ማድረጉ ያስቆጣቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሙስሊሞች በአገሪቱ የተለያዩ አቅጣጫዎች ‹‹313 ሚሊዮን ብሩን ለልማት›› እያሉ ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ ውለዋል፡፡ የተወሰኑት አብረን እንያቸው፡፡
የህዝበ ሙስሊሙ ተቃውሞ መነሻ እና መዳበሪያ ሆና የቆየችው፣ የትግሉ ጽንስ የተወለደባትን አወሊያን በያዘችው አዲስ አበባ በታላቁ አንዋር መስጊድ ሰው በጠዋቱ መትመም ጀምሮ ነበር፡፡ አንዋር በአራቱም አቅጣጫ በሰው ተሞላ፡፡ በርካታ ፖሊሶች በጠዋቱ ቢስ መብራት በሚገኘው ጅንአድ ግቢ ውስጥ ተጠቅጥቀው የነበረ መሆኑን ያየ የህዝበ ሙስሊሙን ጨዋነት መንግስት የማያውቀው ይመስላል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ግን ሁሉም ሰላምን ትጥቁ አድርጎ ነበር የተገኘው፡፡
ሰላቱ ከተሰገደ በኋላ አፍታም ሳይቆይ ደማቁ ተቃውሞ ተጀመረ፡፡ እጆች የያዙትን ወረቀት አውለበለቡ፡፡ በነዚያ ወረቀቶች ላይ የተጻፉ መልእክቶች የህዝቡን የልብ ትርታ መናገር የሚችሉ ናቸው – ከድምጹ ጋር ተደባልቀው ሩቅ ይሰማሉ፡፡ ‹‹313 ሚሊየን ብሩ ለልማት!›› ብዙዎቹ የያዙት ወረቀት ነበር፡፡ በኮምፒውተር ህትመት፣ አንዳንዶቹ በማርከር፣ አንዳንዶቹ በስክሪብቶ የተጻፉ ናቸው፡፡ ትኩር ብሎ ላየው ይህ ራሱ መልእክት ነው፡፡ ‹‹በእጄ ባለው ነገርና በአቅሜ ለመብቴ እታገላለሁ! ለትግሉ የምችለውን አበረክታለሁ!›› ነው መልእክቱ፤ የያዙት ደግሞ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ወንዶች፣ ጎልማሶች፣ አዛውንቶችና ህጻናቶች ናቸው፡፡ ሁሉም ቁርጠኝነታቸወን ታጥቀው፣ መስዋእትነት ሊከፍሉ ተዘጋጅተው ነው የመጡት፡፡ ሁሉም በአንድ ድምጽ፣ በአንድ ጽሁፍ፣ የአገር ሀብት የህዝብ ነውና ህዝብን በሚጠቅም ነገር ላይ እንዲውል፣ ያ ቢቀር እንኳ ህዝብን በሚጎዳ ነገር ላይ እንዳይውል ይጠይቃሉ፡፡ ‹‹ሰሚው አካል የታለ?›› ይላሉ ከሳምንት ሳምንት!
በአንዋር መስጊድ በሴቶች መስጊድ በኩል የታየው የእህቶቻችን ጠንካራ ተቃውሞ አስደማሚ ነበር፡፡ ሴቶቻችንም ለመብታቸው የሚተኙ አይደሉም፡፡ ለሃይማኖታቸው መከበር ዱላን ተጋፍጠው፣ እስርን ገላምጠው መብታቸውን ጠይቀዋል፡፡ ‹‹እኛም ለመብታችን እንታገላለን!›› ብለዋል፡፡ ‹‹ኢስላም ሰላም! ብራችን ለልማት!›› እያሉ በአንድ ድምጽ አድማሱን ሲሞሉት ያየ በእህቶቻችን ምንኛ ይደሰት?
ይህን በመሰለ ውብ ገጽታ የአንዋሩ ተቃውሞ ያለአንዳች ችግር ተፈጽሟል፡፡ በመሀል ለየት ያሉ መፈክሮችን ለማስረጽ የተደረገው ሙከራም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ በሰላም ተቃውሞውን አሰምቶ ወደየፊናው ተበታትኗል፡፡ ሁሉም ወደቤት ሲመለስ በተስፋ መቁረጥ ሳይሆን በቁርጠኝነትና በታደሰ መንፈስ፣ መብቱ እስኪከበርለት ድረስ በሚያታግለው መጠን ኃይል የተሞላ ነበር – አልሐምዱሊላህ!!!
በተቃውሞ ደምቃ የዋለችው ሌላኛዋ ከተማ ወልቂጤ ናት፡፡ የወልቂጤ ሰላማዊ ሙስሊም ማህበረሰብ በጊዜ ነበር ወደ ጃሚአል ከቢር መስጊድ መትመም የጀመረው፡፡ ትልቁ መስጊድ ሞልቶ በዙሪያው የሚገኘው ገላጣ ቦታ ዲናቸው ላይ የሚደርሰው ጥቃት ባሳሰባቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ተከቧል፡፡ ሁሉም ቁጡ፣ ግን ፍጹም ሰላማዊ ናቸው፡፡ ኢማሙ ሰላት ሰግደው አሰላምተው ሲጨርሱ መስጊዱ በተቃውሞ ተክቢራ ተሞላ፡፡ የእለቱን ተቃውሞ መሪ መፈክር የያዙ እጆች ወደላይ ከፍ አሉ፡፡ በርካታ መፈክሮች በዚያ አስገምጋሚ ድምጽ ተስተጋቡ… ‹‹ፍትሕ!››፣ ‹‹ድምፃችን ይሰማ!››፣ ‹‹አህባሽ አይጫንብንም!››፣ ‹‹አሽእብ ዩሪድ ኢስቃጠል መጅሊስ!››፣ ‹‹ፍትሕ ናፈቀን!››፣ ‹‹ለኢስላም እንሞታለን!››፣ ‹‹የታሰሩት ይፈቱ!››፣ ‹‹ባገራችን ሰላም አጣን!››፣ ‹‹እኛም አቡበክር ነን!›› እና ሌሎችም መፈክሮች በህዝቡ ተሰምተዋል፡፡ ደማቁ ተቃውሞ ያለምንም እንከን በሰላም ተጠናቆ ህዝቡ ወደየመጣበት ተመልሷል፡፡
በተመሳሳይ ጊዜ በስልጢ ዞን ወራቤ በአቡበክር መስጊድ በርካታ ህዝብ በተገኘበት ደማቅ ተቃውሞ ተደርጎ ውሏል፡፡ ትልቁ መስጊድ በተባበሩ ድምጾች ተንጧል፡፡ የትግሉን መንፈስ የሚያንጸባርቁ በርካታ መፈክሮችም በድምጽ ተስተጋብተዋል፡፡ ተቃውሞው የተበተነው በሰላም ያለ አንዳች እንከን ነበር፤ ዱሮውንስ ከጨዋ ህዝብ ከሰላም ውጭ መች ሌላ ይጠበቃል!
የወሎዋ ደሴ ከተማ በበኩሏ ተቃውሞዋን አሰምታ ውላለች፡፡ ጠዋት በዋለው የደሴ ችሎት ለ 260 ቀናት ያለምንም ክስ የታሰሩት እውቅ የዲን አስተማሪ አባቶች በዋስ እንዲለቀቁ ውሳኔውን ያሳለፈ ሲሆን የጀግኖቹን መፈታት በጉጉት የሚጠብቀው ህዝበ ሙስሊም በጦልሀ መስጊድ ተሰባስቦ ተቃውሞውን አሰምቷል፡፡ ሰላቱ ከወትሮው ቀደም ብሎ 6፡42 ላይ መሰገዱ ብዙዎች ሰላቱ እንዲያመልጣቸውና እንዲዘገዩ ያደረገ ቢሆንም ከሰላቱ በኋላ ግን ህዝቡ ተቃውሞውን አሰምቶ በሰላም ተበትኗል፡፡ የትግሉን መንፈስ የሚያንጸባርቁ በርካታ መፈክሮችም ተደርገዋል፡፡
በተደጋጋሚና ተቃውሞዋ የምናውቃት ሻሸመኔ የኦሮሚያ ክልልን ለመብት በሚደረግ ትግል ካደመቁ በርካታ ከተሞች አንዷ ነች፡፡ እንደተለመደው ጀግናው የሻሸመኔ ሙስሊም በአራዳ መስጊድ በጊዜ በመሰብሰብ ሰላቱን በስርአቱ የሰገደ ሲሆን ከሰላቱ መጠናቀቅ በኋላ ከፍተኛና ደማቅ ተቃውሞ አሰምቷል፡፡ ‹‹ድምጻችን ይሰማ!›› እና ‹‹የታሰሩት ይፈቱ!›› የሚሉት መፈክሮች የተስተጋቡ ሲሆን ያለአንዳች የጸጥታ ችግር ህዝቡ ብሶቱን አሰምቶ ወደየመጣበት ተመልሷል፡፡ በተመሳሳይ ሰአት በዚያው በኦሮሚያ ዞን ነጌሌ ቦረና ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ መሰማቱም ተዘግቧል፡፡ የነጌሌውን ለየት የሚያደርገው ረዘም ላለ ጊዜ ሰላማዊው የነጌሌ ህዝብ መፈክር እያሰማ፣ ብሶቱን እየተነፈሰ የቆየ መሆኑ ሲሆን ተቃውሞው የተጠናቀቀውም ያለአንዳች የጸጥታ እንከን ነበር፡፡
ኦሮሚያ ክልል በዚህ ብቻ አልበቃትም፡፡ በኮፈሌ ከተማ ሰላም መስጊድ ውስጥ የተሰባሰቡ ምእመኖቿ ‹‹እኛም ለመብታችን ቆመናል!›› የሚል መልእክታቸውን አስተላልፈውባታል፡፡ ሰጋጆች በሙሉ በከፍተኛ ድምቀት በርካታ መፈክሮችን ሲያሰሙ የነበረ ሲሆን ‹‹አላሁ አክበር!››፣ ‹‹ድምፃችን ይሰማ!››፣ ‹‹ኮሚቴው ይፈታ!››፣ ‹‹ፍትህ ናፈቀን!››፣ ‹‹ህገወጡ መጅሊስ አይወክለንም!›› እና የእለቱ ዋና መፈክር የነበረውን ‹‹313 ሚለዮን ብሩ ለልማት!›› በደማቅ ሁኔታ ሲያስተጋቡ ቆይተዋል፡፡ የኮፈሌ ከተማ አጎራባች በሆኑት ቃጬቀታ እና ቃበቴ ከተሞች ላይም በመስጊዶቻቸው እንዲሁ ከፍተኛ ተቃውሞ ተደርጓል፡፡ ተቃውሞዎቹ ያለ አንዳች የጸጥታ ችግር ነበር የተጠናቀቁት፡፡
ካሁን ቀደም ፖሊሶች ሰላማዊውን ሙስሊም መስጊድ ደፍረው በደበደቡባት አጋሮ ከተማም እንዲሁ ከፍተኛ ተቃውሞ ተደርጎ ውሏል፡፡ በርካታዎች በተገኙበት የተስተጋባው ይህ ተቃውሞ የአጋሮ ሙስሊሞች ወኔ በፖሊስ ዱላ ሊሰበር እንደማይችል ዳግም አረጋግጦ የዋለ ነበር፡፡ የድምጽ ተቃውሞው ከተደረገ በኋላ የፖሊስ ሰራዊት መስጊዱን እና መተላለፊያውን ዘግቶ ከበባ በማድረግ ጥቃት ለማድረስ አስቦ ነበረ ቢሆንም በአላህ ጸጋ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ መስጊዱን የከበበውን ሰራዊት ገብቶ ህዝቡ ላይ እርምጃ እንዲወስድ ሲማጸኑ የነበሩት የመስጊዱ ኢማም ድርጊት ብዙዎን አሳዝኖ የነበረ ሲሆን ጥቃት ግን ሳይሰነዘር ቀርቷል፡፡ ሶስት ያህል ሰዎች ከሙስሊሞች መካከል ታስረው ተወስደዋል፡፡ በቦታው የተገኙ የመንግስት አካላትም ተቃዋሚዎችን ለማስፈራራት ፎቶዎችን እያነሱ የነበረ ቢሆንም ጀግናው የአጋሮ ሰላማዊ ህዝብ ግን ያለአንዳች መሸማቀቅ ከበባው ሲበተን ወደየመጣበት ተመልሷል፡፡
በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል የዱአ ተቃውሞ እንዲካሄድባት ታስባ በነበረችው ኮምቦልቻ ከተማ ላይ በኻሊድ መስጊድ በርካታ የሙስሊሙ ማህበረሰብ አባላት በተገኙበት ሰደቃና ዱአ መደረጉም ተዘግቧል፡፡ ገና በጊዜ ወደመስጊድ ሲመጣ ለችግረኞችና ለየቲሞች ሰደቃ በመስጠት የጀመረው የኮምቦልቻ ኻሊድ መስጊድ ሰጋጅ ከሰላቱ መጠናቀቅ በኋላ ቋጥሮ የመጣውን ብስኩት እየተካፈለ በመብላት ድንቅ ወንድማማችነት አሳይቷል፡፡ ከሰደቃው መጠናቀቅ በኋላም በእስር እየተንገላቱ ላሉ ሙስሊሞች አላህ ፈረጃውን እንዲያመጣ ዱአ በማድረግ ሰዉ ወደየመጣበት ተመልሷል፡፡ በዚያው ሰሜን ኢትዮጵያ ባህር ዳር እና ጎንደር ላይ የዱአ ተቃውሞ መደረጉም ተዘግቧል፡፡ በባህር ዳር በሰላም በር መሰጊድ ከወትሮው በተለየ ከፍተኛ ቁጥር የተሰባሰቡ ሙስሊሞች ደማቅ የዱአ ስነስርአት ያካሄዱ ሲሆን ስነስርአቱ ያለአንዳች የጸጥታ ችግር ተጠናቋል፡፡

TPLF is planning another event in Norway Oslo on April 28, 2013


Free reflections observations, opinions, of Poletical view in Ethiopia.
Eden Abera Ayalew
TPLF is planning again to have fundraising event in Norway Oslo on April 28,2013 by denying the voice of people for justice.
As we all know on April 20,2013 TPLF send two representatives from the Ethiopian Embassy in Stockholm with the agenda of Nile dam fundraising program in Stavanger, Norway and close to 300 Ethiopians in Norway has present in the meeting and brought their question of Justice, freedom and Human Rights but the representatives who has been in the place came up with their own agenda and ignored the mass voice as TPLF usually does. Because of this reason the Ethiopians get angry and shout justice and Freedom before Nile dam and express their opposition clearlly they will not cooprate with TPLF’s agenda before their question for justice has been answered ,so that the Norwegian Polices stopped the program before things are getting worse. And these has been on the Norwegian Aftenbladt News at the same day.TPLF is planning again to have fundraising event in Norway Oslo on April 28, 2013
After these on wensday 24 ,April 2013 on Ethiopian Radio And Television Agency has been reported a vice versa lie News saying Ethiopians and foreigners of Ethiopian origin in stavanger, Norway have demonstrated their commitment to national development by purchasing government saving bonds worth million Birr support of Grand Ethiopian Renaissance Dam project. Additionally Ethiopian News in Sweden has reported similar News!
Today again some TPLF agents are distributing flyers which says they will have the same Fundraising event and meeting on April 28, 2013 sunday starting from 15:00 upto 00:00hrs.
And alot of Ethiopians from different areas of Norway are on the way to Oslo for 28 April and Ethiopians who live in Oslo are preparing again to demonstrate with question of Justice and freedom before Nile Dam Fundraise!
What is it gone be? will the Big Question of Freedom and Justice before Nile Dam Fundraise will make a diffrence? or the Dam will be built over Freedom and Justice?
I will come up soon with New Information soon.

50 Ethiopian immigrants sentenced to lengthy jail term with hard labor in Zambia

   The Horn Times News 26 April 2013
Getahune Bekele-South Africa

Although the word “hard labour” sounds brutal and primitive, Zambian magistrate Shadreck Chanda was merciless in passing judgment when he sent 50 destitute Ethiopians to jail for entering the landlocked nation illegally on 29 March 2013.
Victims of human smugglers...Kembatta Ethiopians flocking south in search of better life…
Victims of human smugglers…Kembatta Ethiopians flocking south in search of better life…
The Ethiopians aged 11 to 37 were caught by Zambian police at Nakonde Border post, according to the Post online website, an online Zambian paper April 21st edition.
The magistrate who failed to show compassion to the juveniles, ordered all 50 including the well known human smuggler Sisay Asefa to serve a one-and-half-year imprisonment with hard labour or to pay fine of KR 400.00.
“The government of Zambia would not allow or tolerate people entering the country without proper papers.” Chanda told the stranded Ethiopians, victims of a well organized TPLF sponsored human smuggling gang operating between Johannesburg and Addis Ababa.
“I would have only deported you to Ethiopia but that the offence committed is serious as it borders on national security.” The Zambian magistrate added warning the Ethiopians that if they repeat the same offence, the court would not be lenient towards them.
The original charge sheet alleges that the Ethiopians didn’t inform an immigration officer upon entry as required by Zambian law.
Meanwhile the Horn Times is working to expose a multimillion dollar smuggling ring operating from GP Street in central Johannesburg involving unscrupulous Kenbatta slave traders, immigration officials and TPLF diplomats.
The damning investigation will be posted soon.
infohorntimes@gmail.com
@infohorntimes

Ethiopia: Concern about two journalist held since June 2011 for terrorism?


(Thomson Reuters Foundation) Reporters Without Borders is very worried about two journalists, Woubeshet Taye and Reyot Alemu, who have been detained since June 2011 and were given long jail sentences more than a year ago on terrorism charges.
Taye, who was the deputy editor of the Amharic-language weekly Awramba Times, was transferred on 19 April to a detention centre in Ziway, 130 km southeast of the capital, Addis Ababa. Alemu, a columnist for the national weekly Fitih and recent winner of an international media freedom prize, is in very poor health.
“Nine months after a new prime minister took over following Meles Zenawi’s death, the Ethiopian government continues to be as inflexible as ever,” Reporters Without Borders said.
“The prolonged detention of these two innocent journalists, Taye’s recent transfer to a place far from his family, and the lack of medical care for Alemu are indicative of the government’s intransigence and have dashed all hope of a more tolerant attitude to media freedom.”
The authorities have given no explanation for Taye’s transfer to the detention centre at Ziway, an isolated village, which will mean that this wife and son will have to travel more than four hours in order to visit him.
Alemu, who was awarded the 2013 UNESCO-Guillermo Cano World Press Freedom Prize on 16 April for “exceptional courage, resistance and commitment to freedom of expression,” continues to be held in Kality prison, on the outskirts of Addis Ababa, where officials are apparently unconcerned about an alarming deterioration in her health.
The two journalists were sentenced to 14 years in prison under Ethiopia’s anti-terrorism law in January 2012. The federal supreme court reduced Alemu’s sentence to five years in prison eight months later but Taye’s has been left unchanged.
Ethiopia is ranked 137th out of 179 countries in the 2013 Reporters Without Borders press freedom index.

Contemporary Dictatorship: The Grim Reality of Succession Politics in Ethiopia

by Zekarias Ezra
Reading the lips of Hailemariam Desalegn
Hailemariam Desalegn
The political succession that took place after the passage of PM Meles Zenawi and at the recent EPRDF Congress is fascinating and intriguing. The Congress is fascinating because it went smoothly, peacefully and predictably. It is intriguing in so far as it is a clear indication of EPRDF’s stand on political leadership-which is institutionalizing the political power succession process.
Vowing to continue PM Meles’s policies, PM Haile Mariam states “The (Ethiopian) people love, thank, mourn (and now with the Meles Foundation) they may cherish the memory of PM Meles Zenawi because he devoted his life-long energies to the Ethiopian people, performed immortal feats for the independence and liberation of the Ethiopian nation.”
The above statement was first spoken by Former Chinese Premier Jiang as eulogy to the late Premier Deng Xiaoping. I simply replaced the names. Notice the striking similarity.
For two weeks after the death of PM Deng, Chinese state media ran news stories and documentaries related to Deng’s life and death, with the regular 7 pm National News program in the evening lasting almost two hours over the regular broadcast time. The Ethiopian TV and News Agency did almost the same for PM Meles. It is not my contention that such extended mourning was uncalled for nor should not have happened for PM Meles.
My objective is to simply underscore the entrenched similarity between CCP’s political and propaganda and that of EPRDF. In short, EPRDF, under the later PM leadership, has adopted in wholesome fashion the play book of the Chinese communist party (CCP). Just like the CCP, in Ethiopia, we have a situation where the State implements the policy developed by the Party.
In China, political power is held collectively by the members of the EPRDF Executive Committee (Politburo). The recent power transfer has shown that decision making has become consensus driven (within the Politburo) and that no single figure can any longer act unilaterally as in the days of Mao Zedong and Deng Xiaoping. Looking at what has transpired in Ethiopia after the passage of PM Meles, we could reasonably deduce the same play book is at work in Ethiopia.
The most important and senior officials of the Ethiopian government are all members of EPRDF. In fact, EPRDF Executive Committee members hold positions in Ethiopia’s national government and regional positions of power simultaneously thereby consolidating EPRDF’s power.
In almost identical manner as in China, key policy topics are addressed in the EPRDF Executive Committee which then determines policy actions to be taken by the national and local governments. The policy direction for the entire country, therefore, rests in the hands of 36 individuals. Theoretically, members are elected to this body but everyone knows that admission into the Executive Committee is extremely difficult. EPRDF is shrouded with secrecy despite the official claim to the contrary.
Just like in China, the process of sending the old guards of EPRDF to semi-retirement has begun with the second generation of the party leaders beginning their carefully staged and choreographed entrance into the limelight of political power.
My friends, whether we want to admit it or not the inner working of the Ethiopian political system resembles that of China with one inconsequential exception. Unlike the CCP, EPRDF allows other Political Parties to take part in elections the outcome of which will always be rigged in EPRDF’s favor.
The gallant sons and daughters of Ethiopia who fought the Derg would have indeed died in vain should the current political system allowed to continue to the third and fourth generations of EPRDF leaders guaranteeing, in effect, Ethiopia is but their fiefdom.
With the ascension of PM Haile Mariam, most have hoped to see a flicker of change in tone and action. Nothing really has changed indicating the political bandwagon the current leaders have chosen to embark on or rather had already embarked on is the same as their Chinese counterpart.
Typical to the characters or modern dictators, EPRDF is ever-morphing, honing its skills and daily replacing more brutal forms of intimidation with seemingly “free” elections and talk of human rights and ‘fake’ judicial systems. In order to face off against Ethiopia’s dictators, all freedom loving and democracy advocates—students, activists, lawyers, and ordinary citizens must grow increasingly savvy themselves and adopting new strategies for the struggle that really define the future of the Country.