Sunday, December 15, 2013

በኢትዮጵያ ላይ ስለ ተፈጸመው የፋሺሽት የጦር ወንጀል ዓለም-አቀፍ ተቃውሞ


መግለጫ
ፋሺሽት ኢጣልያ፤ በቫቲካን ድጋፍ፤ በ1928-33 ዓ/ም በኢትዮጵያ ላይ በፈጸመችው የጦር ወንጀል፤ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ በመጨፍጨፉ እንዲሁም 2000 ቤተ ክርስቲያኖችና 525000 ቤቶች፤ ከነንብረቶቻቸውና ቅርሶቻቸው በተጨማሪም፤ ሕዝቡ የሚጠቀምባቸው ውሀና የአካባቢ ብክለት በመከሰቱና 14 ሚሊዮን እንስ ሶች በመውደማቸው ሕዝባችን የደረሰበትን ረሀብና ሥቃይ መገመት አያዳግትም። ስለዚህ በየዓመቱ እንደሚደረገው፤ ዘንድሮም የካቲት 12 ቀን 2006 ዓ/ም ወይም ሰሞኑን ሰማእታቱን ለማስታወስ በሰላማዊ ሰልፍና በመሳሰሉት ተቃውሟችንን በኢትዮጵያና በዓለም አቀፍ በሚገኙ 50 ልዩ ልዩ ከተሞች ለመግለጽ አቅደናል።
ፋሺሽቶች፤ በሶስት ቀኖች ውስጥ፤ የካቲት 12-14 ቀኖች 1929 ዓ/ም፤ 30፣000 ኢትዮጵያውያንን አዲስ አበባ ጨፍጭፈዋል።
ፋሺሽቶች በኢትዮጵያ ላይ ለፈጸሙት ግፍ የኢጣልያን መንግሥት ለኢትዮጵያ ተገቢውን ካሣ አልከፈለችም። ከኢትዮጵያ ተዘርፎ በኢጣልያና በቫቲካን መንግሥቶችItalian Fascists posing in Ethiopia እጅ የሚገኘው መጠነ ሰፊ ንብረትም አልተመለሰም። አይሑዶችን በመደጋገም ይቅርታ የጠየቀችው ቫቲካንም እስካሁን ድረስ የኢትዮጵያን ሕዝብ ተመሳሳይ ይቅርታ አልጠየቀችም። ኢጣልያ በሊቢያ ላይ ለፈጸመችው ወንጀል $5 ቢሊዮን ዶላር የከፈለች መሆኑ የታወቀ ነው። በተጨማሪም ኬንያውያን በእንግሊዝ መንግሥት ለደረሰባቸው ግፍ ተገቢውን ይቅርታ ተጠይቀው ካሣ እንዲከፈላቸው አድርገዋል። የኢንዶኔዝያ ሕዝብም ከኔዘርላንድስ መንግሥት ተመሳሳይ ይቅርታ መጠየቅና ካሣ እንዲከፈል አድርጓል። የኢትዮጵያ ሕዝብስ መቼ ነው ከቫቲካንና ከኢጣልያ መንግሥቶች የሚገባውን ፍትሕ የሚያገኘው? ለክብራችንና ለመብታችን ካልታገልን ፍትሕ አይገኝም። “ባለቤት ካልጮኸ ጎረቤት አይረዳም” ነውና።
በፖፕ ፓየስ 11ኛ ትመራ የነበረችው ቫቲካን ሙሶሊኒንና የፋሺሽቶችን መንግሥት ትደግፍ
እንደ ነበር በብዙ ማስረጃ የተረጋገጠ ነው። ዝርዝሩን ለማየት www.globalallianceforethiopia.org መመልከት ይቻላል። የቫቲካን አባቶች የፋሺሽቱን ጦር መባረካቸውን፤ ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴም አንድ ሚሊዮን ስተርሊንግ ፓውንድ ጉቦ በመስጠት ሥልጣናቸውን እንዲለቁ መሞከሯን፤ ፖፕ ፓየስ 11ኛ የኢጣልያን ንጉሥ ሲባርኩ፤ “King of Italy and Emperor of Ethiopia” (ትርጉም፤ የኢጣልያ ንጉሥና የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት) ማለታቸውን፤ እንዲሁም ቫቲካንና ፋሺሽቶቹ “ላተራን” የተሰኘ ውል በመፈራረም እጅና ጓንት ሆነው ጥቃታቸውን ያከናወኑ መሆኑ፤ ወዘተ. በታሪክ የተረጋገጠ ሐቅ ነው። ይህ ሁሉ አልበቃ ብሎ፤ በቅርቡ፤ ነሐሴ 1 ቀን 2005 ዓ/ም አፊሌ (Affile) በምትሰኝ የኢጣልያ ከተማ፤ የቫቲካን ተወካይ በተገኙበት፤ ለጨፍጫፊው፤ ለግራዚያኒ የመታሰቢያ ኃውልት ተመርቆለታል።
A Vatican Clergy blessing the Italian Fascist Army on its way to commit war crime
የፋሺሽቱ ጦር በቫቲካን ካሕን ሲባረክ
የዓለም-አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ – የኢትዮጵያ ጉዳይ (Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause) ዓላማዎች
የሕብረቱ ዓላማዎች፤ 1ኛ/ ቫቲካን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ፤ 2ኛ/ ቫቲካንና ኢጣልያ የተዘረፉትን ንብረቶች እንዲመልሱ፤ 3ኛ/ ኢጣልያ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ተገቢውን ካሣ እንድትከፍል፤ 4ኛ/ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በኢትዮጵያ ላይ የተፈጸመውን ግፍ በመዝገቡ እንዲያውልና፤ 5ኛ/ ለግራዚያኒ የተቋቋመው ኃውልት እንዲወገድ ነው።
ለሐገር ክብርና ፍትሕ፤ ለሰብአዊ መብት መከበር የምንቆም ሁሉ፤ የመንፈሳዊ፤ የመገናኛ ብዙኃን፤ የሴቶች፤ የወጣቶችና ለሰብአዊ መብት የሚታገሉ ድርጅቶች፤ ወዘተ. ጭምር፤ የየካቲት 12 ቀን 2006 ዓ/ምን የሰማእታት ቀን፤ ከላይ ለተጠቀሱት ዓላማዎች በመታገል በደመቀ ሁኔታ እንድናከብረው እናሳስባለን። የመታሰቢያው ቀን፤ በሰላማዊ ሰልፍ፤ በጉባኤ እና/ወይም በጸሎት ሊከናወን ይችላል።
“ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” መዝሙረ ዳዊት 67/31
ቸሩ የኢትዮጵያ አምላክ ያበርታን።
Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause; 4002 Blacksmith Drive, Garland, TX 75044
www.globalallianceforethiopia.org; info@globalallianceforethiopia.com

በማንዴላ ሞት መንግሥቱን ከግፍ ለማንፃት?


በልጅግ ዓሊ
የማንዴላን ሕልፈተ ሕይወት ተመልክቶ በዓለም ደረጃ የሚያስደንቅ ሁኔታ ስናይ ሰነበትን። ማንዴላ የሠራውን መስራት ሳይሆን እሱ የታሰረበትን ዓላማ በተጻራሪ የሚተገብሩ ሁሉ በቀብሩ ላይ ለመገኘት ከተደበቁበት ብቅ ብቅ ማለታቸው የሚስደምም ነው።
በተለይ አንዳንዶቹ በተለያየ የመገናኛ ዘዴዎች ስለ ማንዴላ ጥሩ ምግባር ቃለ መጠይቅ የሰጡትን  ስናጤናቸው ብዙ የሚያስተዛዝብ ሁኔታዎችን እንገነዘባለን።  በሺህ መጽሐፍ፣ በሽህ ሬዲዩ ቢታገዙም በደም የወየበ ታሪካቸውን  የማይሰርዝላቸው ፋሽሽቶች ይህችን ወቅት ተጠቅመው ለሕዝብ ሃሳቢ ሆነው ለመታየት መራወጣቸው የሚገረም ነው። ይህንን ወቅት ለመጠቀም “እኔም ነበርኩበት“ የሚለው ፋሽሽቱ መንግሥቱ ኃይለማርያምም ሳይቀር ከዚምባዌ ድምጹን አስምቷል።Former Ethiopian President Mengistu Haile Mariam
ታሪክ  እንደ ማንዴላ ያለውን ጀግናን ሲያከብር ቡከን ፋሽስትንም ሲኮንን ይኖራል። ይህንን መቀየር የሚችል ማንም አይኖርም። ማንዴላ እንዲህ የተወደደውን ያህል እነ ሒትለር፣ እነ ሙሶሎኒ ፣ እነ እስታሊን ደግሞ ሲኮነኑና ሲወገዙ ኖረዋል። ለወደፊቱም እንዲሁ። ታሪክ በሠሩት ግፍ ብዛት ከትውልድ ትውልድ እየተሸጋገረ ሲያወግዛቸው ይኖራል።
የማንዴላ ሞት ዜና በጎላበት ጀምበር በጀርመንም የናዚ ፋሽሽቶች መሪ ሒትለር ሲነሳ መሰንበቱ አንድ ሌላ አስገራሚ ክስተት ሆኗል። ትግሌ (ማይን ካንፍ ፣Mein Kampf )  ሒትለር እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር 1923 በመንግሥት ግልበጣ ሙከራ ምክንያት ታስሮ በነበረበት ወቅት የጻፈው መጽሐፍ ነው። ይህ መጽሐፍ እንደ ናዚዎች ማኒፌሰቶ ሆኖ ይታያል። መጽሐፉ በአይሁዳውያን ላይ ጥላቻን የሚያስፋፋና ጀርመኖች ምስራቅ አውሮፓንን መውረር እንዳለባቸው የሚቀሰቅስ ነው። በጀርመን ሕግ በተደነገገው መሠረት ይህን መጽሐፍ መልሶ የማሳተም መብት እገዳ (copy right) በ2015 ዓ.ም ያልቃል። ስለሆነም ማንም የፈለገ አካል የማሳተም መብት ይኖረዋል።
ይህንን ድንጋጌ በሚመለከት ጀርመን ውስጥ የጦፈ ክርክር ሲከናወን ሰንብቷል። እንደተለመደው የናዚ ደጋፊዎች ሒትለር ሃገሩን ይወድ ነበር፣ ለሃገሩ ጥሩ ሰርቷል . . .  ወዘተ.  የሚል ለሒትለር በታሪክ ጥሩ ቦታ ለመስጠት እንቅልፍ አጥተው ሰንብተዋል። ደጋፊዎቹ መጽሐፉን እንደገና ለማሳተም ሲታገሉ በተቃራኒው የቆሙት ደግሞ በሒትለር የተፈጸመውን ግፍ እያነሱ እንደ ሒትለር ዓይነት በዓለም ውስጥ ዳግም እንዳይነሳ መጽሐፉ መልሶ መታተም እንዳይችል ሲታገሉ ተስተውሏል።
በጀርመን ሃገር ባይረን ተብሎ በሚጠራው ክፍለ ሃገር ግን በ2015 የሚልቀውን የማሳተም መብት በመጠቀም የሒትለር መጽሐፍ  እንደገና ለማሳተም የተደረገው ጥረት ከሽፏል። የባየር አስተዳዳሪዎች በሒትለር የተጨፈጨፉትን በማክበር መጽሐፉን እንደገና ማሳተም ኢ-ሰባዓዊነት ነው ሲሉ ወስነዋል።
http://www.bbc.co.uk/news/world-europe-25346140
የክፍለ ሃገሩ መንግሥት ብዙ በሒትለር የተጎዱ ቤተሰቦችን አነጋርግሮ ይህንን መጽሐፍ ማሳተም በቤተሰቦቹ ላይ ሕመምን መቀስቀስ እንደሚሆን አሳምኖ ማሳተምም ሆነ ማባዛትን እንደገና ከልክሏል። ይህ ውሳኔ ፋሽሽቶችን ለሚቃወሙ ጀርመኖች ትልቅ ድል ነው።
ይህ ዓይነት ትግል የሚደረገው በጀርመን ብቻ መሆን የለበትም። በእኛም ሃገር ይህ ዐይነቱ አመለካከት ሊዳብር ይገባል። ወያኔ ስልጣን ከወጣ በኋላ የተጀመረውን የጎጠኝነት ፖለቲካ ለመቃወም የተጀመረው ትግል የመንግሥቱ ኃይለማርያምን ወንጀል ለጊዜው ወደ ጎን አድርጎ ትግሉ በወያኔ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ቀጥሏል። ግን ይህ ሃገርን የማስቀደም ክቡር ዓላማ በመንግሥቱ ደጋፊዎች ሲጣስና የመንግሥቱን አረመኔነት ለማድበስብስ የሚደረገው ጥረት ብልጭ ድርግም ማለት ከጀመረ ሰነባብቷል።
የፋሽሽቱ ደጋፊዎች መሪያቸው ከወደቀ በኋላ ስለ መሪያቸው ትልቅነት ማውራት የተለመደ ባህሪያቸው መሆኑንም ታዝበናል። እዚሁ ጀርመን ውስጥ ሒትለር ሃገሩን ይወድ ነበር እንደሚሉት የፋሽሽት ደጋፎዎች ማለት ነው። የሒትለር ደጋፊዎች ለዚህም ድጋፋቸው የሚያቀርቡት ምክንያት ባንድ ወቅት ከየሃገሩ በሰበሰባቸው እስረኞች ያሰራው አውራ መንገድ (Autobahn) ሁል ጊዜ ይጠቀሳል። “ሒትለር ቢኖር ኖሮ ጀርመን የትና የት በደረስች ነበር“ በማለት  ዓመኔታ ለመሸመት ይጥራሉ።
እነዚህ የአስተሳሰብ-ደሃ ጀርመኖች በዴሞክራሲ ካገኙት የዓለም የኤኮኖሚ ትልቅነት ይልቅ የእነርሱ ዘር ትልቅነት ላይ የተመረኮዘው የሒትለር ዓላማ ታላቅነትን የሚያጎናጽፋቸው ይመስላቸዋል። ለዚህም የሒትለርን መሪ መፈክር አንግበው ሲጓዙ ይታያሉ። በአሁኑ ሰዓት ያለውን የዓለም ሥርዓትና ይህም ሥርዓት ለጀርመን ሕዝብ የሰጠውን ጥቅም የሚያውቀው የጀርመን ሕዝብ ሥርዓቱን በማናጋት ይህንን የተንደላቀቀ ኑሮውን ለማበላሸት የሚጥሩትን ወገኖች ዕድሉ እንዲሰጣቸው ብዙሃኑ የጀርመን ህዝብ ፍላጎት የለውም።
ፋሽሽቶችን ከፍ አድርጎ ለማሳየት የሚደረገው ጥረት በጀርመን ብቻ ሳይሆን በኢጣሊያም ይታያል። በቅርብ ጊዜ ግራዚያኒ ሐውልት ተሰርቶለታል። ሞሶሎኒንም እንደ ጀግና የሚቆጥሩ አልታጡም። በተለይ በፋሽሽቱ ሥርዓት ጥቅም ያገኙ የነበሩ ወገኖች የሌላው ሕብረተሰብ ቁስል አይሰማቸውም። ይልቁንም እንጨት ሊሰዱበት ይፈልጋሉ።
በእኛም ሃገር የሚስተዋለው ከዚህ የተለየ አይደለም። “መንግሥቱ ሃገር ወዳድ ነው “፣ “መንግሥቱ ቢኖር እንዲህ አይደረግም“፣ “መንግሥቱ ቆራጥ ነበር“. . . .  ሌላም ሌላም ብዙ ከሥርዓቱ ጥቅመኞች የምንሰማው ባዶ ጩኽት አለ። ቆራጥነቱንም በፍርጠጣው፤ ሃገር ወዳድነቱም የተማረ የሰው ኃይል እንዳይኖር በቀይ ሽብርና በሌሎቹ የግድያ ዘዴዎቹ አስመስክሯል። ወንጀሉ የመንገድ ላይ ስጦ ሆኖ የተመለከትነው ነው።  ለሃገራቸው አንድነትና ልዋላዊነት አጽማቸውን ሲከሰክሱ የነበሩ ጀግኖች በመንግሥቱ ነፍስ ገዳዮች ከሃዲ እየተባሉ ሲገደሉ፣ ፈሪ  ፈርጣጩ ቡከን ጀግና ተብሎ ሲወደስ መስማት ውርደትም ሃፍረትም ይሆናል። እነዚህ ጀግኖችን እየሰደቡ ይጽፉ የነበሩ አሁን ደግሞ በውጭ ሃገር የዚህ ፋሽሽት ቆዳ ለማዋደድ የሚደርጉት ጥረት የሚያሳፍር ነው። ለመሆኑ በዚህ ዓይነት ክህደት ይች ሃገር ከወያኔ ነጻ ትወጣለች ብለው ያስቡ ይሆን?
የመንግሥቱ ደጋፊዎች ሰሞኑን የኔልሰን ማንዴላን ሕልፈተ ሕይወት ምክንያት በማድረግ የሃገራችንን ፋሽሽት አረመኔው መንግሥቱን   ቃለ መጠይቅ በማድረግ ፋሽሽታዊ የሆነውን ገጽታውን እንደገና ለማደስ ጥረት አድርገዋል። ደጋፊዎቹ  ይህንን ቡከን ፋሽሽት ከሃገሩ አልፎ ለዓለም አቀፍ ጭቆና እንደታገለ ሊነግሩን ይፈልጋሉ። እነዚህ የመገናኛ ዘዴዎች መንግሥቱን ቃለ መጠይቅ በማድረግ በመንግሥቱ በግፍ የተገደሉትን ወገኖች መልሰው ለመግደል ይጥራሉ። በሕይዎት በተረፉትና የወላድ መኻን በሆኑት ወላጆች ቁስል ላይ ጨው እየነሰነሱ መሆናቸን እንዲገነዘቡ አስታዋሽ የሚሹ ይመስላሉ። እንደ ባየር ክፍለ ሀገር ጀርመኖች የሌሎች ሃዘን ሳይሰማቸው የዚህን አረመኔ ፋሽሽታዊ ገጽታ ለማሳመር ጥረት አድርገዋል። ይህ ደግሞ የሚያሳፍር እንጂ የሚያኮራ ድርጊት አይሆንም። ከማሳፈርም አልፎ  በመንግስቱ ኃይለማርያም የተገደሉትን ሰማዕታት መልሶ  እንደመግደል መግደል ይቆጠራል። በሃገር ላይ የተሰራ ወንጀልም ነው።
በቃለ መጠይቃቸው ላይ ማንዴላን የጦር ሥልት በማስተማር ትልቅ ጥረት ያደረጉትን እነ ጀኔራል ታደሰ ብሩን ለምን መንግሥቱ ራሱ እንደገደላቸው እንኳን ማንሳት አልፈለጉም። ሳያውቁት ቀርተው አይደለም ነገሩን ሳያነሱት የቀሩት። እንደተለመደው መጠየቅ የሚገባቸውን ሃቆች በመሸፈን የፋሽሽቱን ቆዳ የሌለውን መልክ እንዲኖረው ለማድረግ እንጂ።
http://www.bbc.co.uk/news/world-africa-23515879
እነዚህ የሬዲዮ ጣቢያ ሃላፊዎች የመንግሥቱ ጉዳይ መነሳት ለጸረ ወያኔው ትግል ከፋፋይ መሆኑ አይታያቸውም። ከፋፋይ መሆኑም ቢያውቁም ከመንግሥቱ ይበልጥ ሃገር በወያኔ ብትፈርስ ድንታ እንደሌላቸው ነው ድርጊታቸው የሚያሳየን። የብዙሃኑ ጸረ ወያኔ ትግል  መንግሥቱን ሥልጣን ላይ ወይም ደጋፊዎቹን ስልጣን ላይ ለመመለስ እንዳልሆነ ግልጽ ነው። ትግላችን ዘረኝነትን አጥፍተን ዴሞክራሲን መገንባት መሆኑ  ያልገባቸው ካሉ ትልቅ ስህተት ላይ ወድቀዋል። በኢሠፓ አባልነታቸው እንደገና ወደ ስልጣን ተመልሰን እንወጣለን ብለው አስበው ከሆነ ተስፋ ሊቆርጡ ይገባል። ምንም ይሁን ምን ወደ ኋላ አንመለስም።
መንግሥቱ በሃገር መክዳት ለፍርድ መቅረብ እንጂ እንደ ጀግና በየቦታው ቃለ መጠይቅ እየተደረገለት የእሱ ቆዳ ተገልብጦ እንዲለበስ ጥረት መደረግ የለበትም። ከሃገር ሰርቆና ዘርፎ በፈረጠጠው ገንዘብ የሚገዛው የዕውቅና የሃገር ወዳድነት ጃኖም ሊኖር አይገባም። የወንጀለኛ ቆዳ እንጂ። ንፁህ ነን የሚሉ ካሉ በዚህ ጉዳይ ላይ ራሳቸውን ከፋሽሽቱ በመነጠል ግልጽ የሆነ አቋማቸውን ሊያሰሙ ይገባል።
በተለይ በሕዝብ ገንዘብ የተቋቋመ እንደ ኢሳት ዓይነት የዜና ማሰራጫ በመንግሥቱ ግፍ የተሰራባቸው ሁሉ እርዳታቸውን የለገሱት መሆኑን አስተዳዳሪዎቹ ልብ ሊሉት ይገባል። እርዳታቸውን ለጠላታቸው ማስተዋወቂያ ሲያደርጉት ሊያጡት የሚችሉትን ድጋፍ መመዘን ብልዕነት ነው። ለምን ቢባል ጥያቄው የሞራል ጥያቄ ነውና!!  አሊያ ግን የኢሳትን ዓላማ ጥርጣሬ ውስጥ ይከተዋል።
http://ethsat.com/ESAT-Radio-player/archive/ESAT_Radio_Wed_11_Dec_2013.mp3
ለኢሳት ገንዘብ በማሰባሰብ ጥረት ያደረጉ “የሰበዓዊ መብት ታጋይ ነን” የሚሉ ደግሞ ይህ ድርጊታቸው ለሁሉም የሰው ዘር ሰብዓዊ መብት መከበር እንዳልቆሙ ያጋልጣቸዋል። ያገኙት ተሰሚነትም ፀሐይ እንደነካው በረዶ ሊቀልጥ ይችላል።
ይህንን አረመኔ ለፍርድ ይቅረብ ብለው ሲናገሩ ያልተሰሙ፣ በመንግሥቱ ስለተጨፈጨፉት ሲናገሩ ያልተደመጡ፣ ለፍትህ ያልቆሙ፤ ዛሬ ለዚህ አረመኔ መድረክ መስጠታቸው የሃገሪቱ ዜጎች ሁሉ በእኩል አይን እንደማያዩ ድርጊታቸው አጉልቶ ያሳየናል። ሌላው ቢቀር ማንዴላን በሚመለከት ባለውለታዎች ሲነሱ ጀኔራል ታደሰ ብሩም ሆነ ማንዴላን በብዙ የደገፉ የቀዳማዊ ኃይለስላሴ መንግስት ባለስልጣናት የአሟሟት ሁኔታም መጠቀስ ነበረበት። ታሪክ ግማሽ የለውምና ሙሉው የኢትዮጵያውያን አስተዋጽኦ በዘገባው መካተት ነበረበት።
http://www.bbc.co.uk/news/world-africa-23515879
ወያኔን አስወግደን ሃገራችንን ዴሞክራሲያዊት እናደርጋታለን ብለን የምናስብ ሁሉ ከደርግና ከመንግስቱ ኃይለማርያም ፋሽሽታዊ ወንጀል ራሳችንን ነጥለን መንግሥቱም ይሁን ወያኔን የህዝብ ጠላትነታቸውን አውቀን ካልሄድን ሃገራችንን ከወያኔ ጭቆና ነጻ የምናወጣበትን ቀን እናራዝመዋለን። ትግሉ ጥርት ብሎ ለዴሞክራሲ ካልሆነ በስተቀር ከሃገር በተሰረቀ ገንዘብ መልሰን ስልጣን እንወጣለን በሚል እቅድ መጓዝ በሃገሪቱ ውስጥ ሊነሳ የሚችለውን ችግር አለማጤን ይሆናል። ማንም ከድጡ ወደ ማጡ መሄድ የሚፈልግ አይኖርም።
መንግሥቱን ለቃለ መጠይቅ የጠሩ የሬዲዮ ጣቢያዎች ይህንን በማድረጋቸው ምን ያህል ከወያኔ ጋር የሚደረገውን ትግል እንደከፋፈሉ ካልተረዱ የሚያሳዝን ነው። በዚሁ አጋጣሚም የሕዝብ ድጋፍ እንደሚያጡ ሊረዱት ይገባል። ነጻ ፕረስ ሃላፊነት የጎደለው ፋሽሽቶችን ማመጻደቂያ ሊሆን አይገባምና ከዚህ መጥፎ ምግባር መቆጠብ አስተዋይነት ይመስለኛል።
ሂትለር፤ ጀኔራል ፍራንኮ፤ ሞሶሎኒ፤ መለስ ዜናዊ፤ መንግስቱ ኃይለማርያም፤ (በቁም የሞተ) ሁሉም ፋሽሽቶች ሞተዋል። ስማቸው ግን ከታሪክ ጠባሳ ገጾች አይፋቅም። ባንጻሩ ጋንዲ፤ ማንዴላ፤ ማርቲን ሉተር ኪንግና ሌሎቹም ጀግኖች ሞተዋል። ግን ሰማዕታት ናቸው። ታሪካቸውም በጀግንነት የወርቅ ቀለም ተጽፎ ትውልድ ሲወራረሰው ይኖራል። የሁለቱም ወገኖች ስም ከመቅበር በላይ ውሏል። ሆኖም የፋሽሽቶቹ የነ ሂትለር በፀረ-ህዝብነት፤ የነማንዴላ ግን በህዝባዊነት!!
በፋሽሽቶች ለተጨፈጨፉ ሁሉ የሚያስብ በሰላም ይክረም !
ታህሳስ 2006
Beljig.ali@gmail.com

Mandela laid to rest in Qunu, ending journey that transformed South Africa


(CNN) — Nelson Mandela was laid to rest in his childhood village of Qunu on Sunday, marking the end of an exceptional journey for the prisoner turned president who transformed South Africa.
Mandela was laid to rest in the afternoon, when the sun is at its highest.
Under the scorching sun, a military escort accompanied his coffin to the burial site and took off the national flag that draped his casket. White wreaths sat around it.
His widow, Graca Machel, and others watched from under a tent as helicopters carrying flags whizzed past.
“Now you have achieved the ultimate freedom in the bosom of God, your maker,” the officiator said.
Tribal leaders clad in animal skins joined dignitaries in dark suits at the burial grounds atop a hill overlooking Qunu valleys.
Before making their way to the site, mourners attended a service in a tent set up for the event. Ninety-five candles glowed behind his casket, one for each year of his life.
Mandela died December 5 after a recurring lung infection and declining health.
The service
The service started with a somber military procession wheeling his casket into the tent. Residents watched and danced in what has become a familiar celebration of his life.
Inside the tent, the wall of candles flickered, casting a soft glow on tearful mourners.
And as the national anthem “Nkosi Sikelel’ iAfrika” or “God Bless Africa” drifted over the rolling hills, a giant picture of Mandela smiled down on mourners.
“Today marks the end of an extraordinary journey that began 95 years ago,” South African President Jacob Zuma said during the ceremony. “It is the end of 95 glorious years of a freedom fighter … a beacon of hope to all those fighting for a just and equitable world order.”
The president thanked Mandela’s family for sharing him with the world, and said his memory will live on.
“We shall not say goodbye, for you are not gone,” Zuma said. “You’ll live forever in our hearts and minds.”
About 4,500 people gathered in the tent, including Mandela’s widow, Graca Machel, who occasionally dabbed her eyes with a handkerchief. His ex-wife, Winnie Mandela, sat next to her.
‘I’ve lost a brother’
Mourners represented all spheres of Mandela’s life. There were celebrities, presidents, relatives and former political prisoners.
“You symbolize today and always will … qualities of forgiveness and reconciliation,” said a tearful Ahmed Kathrada, a close friend who served time in prison with Mandela for defying the apartheid government. “I’ve lost a brother. My life is in a void, and I don’t know who to turn to.”
Talk show host Oprah Winfrey, Prince Charles and business mogul Richard Branson were also among the attendees.
Final chapter
The funeral and burial cap 10 days of national mourning for a man whose fame transcended borders.
“Nelson Mandela was our leader, our hero, our icon and our father as much as he was yours,” Tanzanian President Jakaya Kikwete said, regaling mourners with tales of a secret visit Mandela made in 1962 to Dar es Salaam to gather support for the ANC.
During his fight against apartheid, Mandela fled to Tanzania, which housed the headquarters of his party, the African National Congress. The white minority government had banned it in South Africa.
In sharp contrast to the days of apartheid, the events honoring Mandela included a great deal of pageantry, as well as state honors.
Eastern Cape province, where he grew up surrounded by lush, tranquil hills and velvety green grass.
Before its arrival in Qunu, it lay in state for three days in Pretoria. After an emotional service at the air base there, which included the handing over of his body to the ruling African National Congress, it was put in a military helicopter for the final leg of his journey.
Though he dined with kings and presidents in his lifetime, the international icon relished his time at the village. He herded cows and goats there as a child, and always said it’s where he felt most at peace. Some of his children are also buried there.
“He really believed this is where he belonged,” said his daughter, Maki Mandela.
Mandela was imprisoned for 27 years for defying the racist apartheid government that led South Africa for decades. He emerged from prison in 1990 and became South Africa’s first black president four years later, all the while promoting forgiveness and reconciliation.
His defiance of white minority rule and long incarceration for fighting against segregation focused the world’s attention on apartheid, the legalized racial segregation enforced by the South African government until 1994.
Years after his 1999 retirement from the presidency, Mandela was considered the ideal head of state. He became a yardstick for African leaders, who consistently fell short when measured against him.
Following the service, family and friends will walk to the gravesite, overlooking the rural home he loved so much, to say goodbye.
In keeping with tradition, Mandela was laid to rest in the afternoon, when the sun is at its highest.

Tamrat Layne: Another Botched Marxist Rollout


by Mark Baisley
Meles Zenawi and Tamrat Layne were born just months apart in 1955
The political philosophy of German sociologist Karl Marx inspired the imaginations of many aspiring revolutionaries. While he did not live to see his theories played out on the large scale of the Soviet Union, Marx did leave volumes of written instructions for his followers in The Communist Manifesto and Das Kapital.
During the mid-1950s, while Fidel Castro and Che Guevara were busy installing the first communist oligarchy in the Western Hemisphere, a parallel partnership was emerging half-way across the globe in eastern Africa. Meles Zenawi and Tamrat Layne (pronounced “lie-nay”) were born just months apart in 1955 in the northern market villages of Ethiopia.
As the boys matured into adulthood, their close friendship was solidified in a shared admiration of Karl Marx. They read and reread every Marxist writing that they could get their hands on. By the time they reached their thirties, Zenawi and Layne were convinced that they themselves were called to lead the transition of Ethiopia into the utopian ideal of communism.
By the late 1980s, Zenawi and Layne had initiated a methodical and escalating plan towards replacing Ethiopian dictator Mengistu Haile Mariam. Over the course of years, Zenawi and Layne accumulated soldiers, weapons, tanks and loyalties. Working from their mountain refuge, they would confront Mengistu‘s army in small battles. Many times, an entire battalion would defect to their cause rather than fight. By 1991, Zenawi and Layne marched their Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front into the capital of Addis Ababa.
Having easily overthrown the Ethiopian government, Meles Zenawi was installed as President and Tamrat Layne as Prime Minister. There had been previous attempts at standing up a communist regime in Ethiopia, but it always ended up looking more like a dictatorship. Aspiring utopian leaders frequently convince themselves that, this time, it really will work.
Predictably, the experiment eventually proved a disappointment for the expectations of the young despots. Following Karl Marx’ rollout plan did not result in a happy and prosperous nation. And after a series of trial and error, the boys tossed the roadmap and ruled by their own intuitions. Then in 1996, Meles Zenawi also tossed Tamrat Layne in prison and assumed for himself a more powerful version of Prime Minister.
The melee surrounding this mini coup d’état saw many Ethiopians fleeing the country in fear of the recurring nightmare of violent unrest. Among the refugees to Kenya was Tamrat Layne’s wife and two young children. In time, they made their way to the United States Embassy in Nairobi.
Realizing that their lives were in danger, the U.S. granted Layne’s wife and children political asylum and put them on a plane to Colorado. In a matter of months, Layne’s wife transitioned from First Lady to refugee to clerk at a 24-hour gas station convenience store. It would be twelve years before she would see her husband again.
During most of the period from October 1996 through December of 2008, Tamrat Layne was kept in solitary confinement. Every conviction that had, at one time, made so much sense now seemed to betray him; the philosophies of communism, his lifelong comrade, and soon – the certainty of atheism.
Around the midway point of his prison term in 2002, Layne tells of his encounter with a very real God. The personal interaction claimed by millions of others came about for this former revolutionary and deposed ruler while sitting very alone in solitary confinement. For Tamrat Layne, devotion to Karl Marx had been joyously displaced by faith in Jesus Christ.
Six years later, on December 19, 2008, Layne was finally released from prison. The American Ambassador to Ethiopia made arrangements to reunite Tamrat with his family in the United States. His devoted wife, his now adult son, and his daughter who was an infant when he last saw her, all greeted him at the Denver International Airport. And the awkward delight in reacquainting with his own flesh and blood was about to be followed by a surprising revelation regarding his new host country.
While his outlook on life had been drastically improved, Tamrat Layne anticipated that he would be living in a dysfunctional American society. He had spent decades immersed in the worldview that the West had humanity all wrong and that the United States was the ultimate infliction of unfair capitalism.
But it did not take many weeks of observing Americans in their natural habitat to see that they were generally happy and thriving. Tamrat asked himself, “How did this America become the most powerful and prosperous nation in history after only 200 years of existence when Ethiopia remains poor after 3,000 years of attempts at progress?” The inquisitiveness that once sought theories to solve complex sociological problems was now seeking explanations for demonstrated success.
Layne walked into a Denver public library and asked, “How do I understand how America works?” I hope one day to find and thank the librarian who responded by handing Tamrat a copy of the Declaration of Independence, the United States Constitution, and an inspiring account of America’s founding history.
Today, Tamrat Layne is a kind, humble, and deeply thoughtful man. He carries the burden of regret for the nation that he used to rule. But with his unique perspective, Tamrat has wisdom for both Ethiopia and for America. And, as it turns out, that powerful advice is the same for both nations: “Seek the liberty that God gave you.”
Source: Town Hall Finance

አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ስለምኒሊክና ስለኢትዮጵያ

 

bulcha d
የአጼ ምኒሊክን መቶኛ የሙት አመት መከበር ምክንያት በማድረግ በ DW ሬድዮ በተደረገው ጥያቄና መልስ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ፣ ዶ/ር ሓይሌ ላሬቦና ዶ/ር ሹመት ሲሳይ (የታሪክ ተመራማሪዎች) ቃለ መጠይቅ ተደርጎ በሚሰጠው መልስ ላይ ስለ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ በተናገሩት ላይ አስተያየቴን አቀርባለሁ።
አንባቢያንን ቃለመጠይቁን ቢያዳምጡ ጥሩ ነው ባይ ነኝ፤ ሁለቱ የታሪክ ምሁራን ትምህርታዊ ትንተና ይሰጣሉና፡፡
ውሸት ሲደጋገም እውነት ሊመስል ይችላል፤ በተለይም የአገራችንን የኢትዮጵያን ታሪክ ለማያውቁ እውነታው ምን እንደሚመስል መረጃ ለማቅረብ እሞክራለሁ።
አቶ ቡልቻ ኦሮሞ ከባሌ እየተስፋፋ ሲመጣ ልብነ ድንግል እንዳይስፋፋ አቆሙት ይላሉ፡፡ ለምን ይህን ምሳሌ እንዳቀረቡም ግልጽ አይደለም ለሳቸው ትንታኔ የማይመች በመሆኑ፤ ለዛውም በአጼ ልብነ ድንግልና በኦሮሞች መሀከል ስለነበረው ግኑኝነት በከፊል ዶ/ር ሃይሌ ላሬቦ ሊያስረድዋቸው ሞክረዋል፤ ስለመስፋፋቱና እንዲያውም አማራውን እንደገፋው ለአቶ ቡልቻ መረጃ ላቅርብ፡፡
ጥንት ሌላ ስም የነበራቸው በኦሮሞ ከተያዙ ማግስት ስማቸው የተቀየረ፤ ደዋሮ-ጨርጨር፣ ጋፋት-ሆሮ፣ ገራሪያ-ሰላሌ፣ ዳሞት-ወለጋ፣ አበቤ-በቾ፣ ሽምብራ ኩሬ-ሞጆ … (የሃያኛው ክፍለዘመን ኢትዮጵያ ገጽ 50 በጥላሁን ገ/ስላሴ) በቅኝ ተገዛ የሚሉት ኦሮሞ ተጨማሪ ቦታ እንደያዘ እንጂ እንደተወሰደበት አይደለም ታሪኩ የሚመሰክረው፡፡
BULCHADEMEKSAአቶ ባልቻ የኦሮሞን ታሪክ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ሊያዛምዱት ይሞክራሉ፤ ኦሮሞም እንደ ደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች ኢትዮጵያ ውስጥ ሲረገጥ የኖረ ሕዝብ አድርገው ያቀርቡታል። መፍትሄውንም ሲጠይቁ reconciliation እርቅ ኦሮሞ ይቅርታ ተጠያቂ የተቀረው ይቅርታ ጠያቂ በተለይም የፈረደበት አማራ ለዚህ ወንጀል ትልቁን ድርሻ ይወስዳል፡፡ ባለፉት አስተዳደሮች ስህተቶች አልተሰሩም ብሎ የሚከራከር የለም፤ ጥያቄው እንዴት አብረን ወደፊት መሄድ እንችላለን ነው?
እንደቅኝ ተገዛን የሚሉት ቡልቻ ደመቅሳ አገሪቱን በእርሻ ሚኒስቴርነትና በምክትል ገንዘብ ሚኒስቴርነት አስተዳድረዋል – ቸር ቅኝ ገዢ ነበር የነበራቸው፤ እኛ ቅኝ እየተገዛን ስለሆንን በሚኒስቴርነት ቅኝ ገዢዬን አላገለግልም ብለው አላንገራገሩም፡፡
ኦሮሞ በሲቪሉም ሆነ በወታደራዊው ክንፉ ታላቅ የሚባሉትን ስልጣኖች ይዞ የኖረና ያለ የህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡ አገሪቱ ውስጥ ለነበሩትና ላሉትም ደግ ነገሮችም ሆነ ክፉ ነገሮች ተጠያቂነቱ እኩል ነው፡፡ አቶ ቡልቻ ቅኝ ገዢ የሚሉትን የአማራውን ክፍለሀገር ደጃዝማች ክፍሌ ዳዲ ያስተዳድሩት ነበር፡፡ (ምሳሌ የሚያቀርቡበት ደቡብ አፍሪካ የማስተዳደር ቅንጦት ይቅርና ነጭ በሚዝናናበት ቦታ ጥቁር መግባት አይፈቀድለትም ነበር)፡፡
ስለኦሮሞ ባለስልጣናት እስቲ እንመልከት
ምኒሊክ በሸዋ ሲነግሱ የረዷቸው አብሮ አደግ ባልንጀራቸው ጎበና ዳጬ ናቸው፡፡ የወለጋውም አስተዳዳሪ ኩምሳ ምኒሊክን በደጃዝማችነት አግልግለዋል፤ እነ ባልቻ አባ ነፍሶም የማይረሱ ታላቅ ኢትዮጵያውያን ናቸው፡፡
የአጼ ሃይለስላሴ አባት ራስ መኮንን ወልደሚካኤል (ጉዲሳ) አባታቸው ኦሮሞ ነበሩ፤ እናታቸውም ወ/ሮ እመቤት እናታቸው ኦሮሞ ነበሩ፡፡
ራስ ዳርጌ የሸዋው ንጉስ ሳህለስላሴ ከወለዷቸው አራት ወንዶች መሃከል አንዱ ሲሆኑ ጥናታቸው አርሲ ውስጥ የአንድ አካባቢ ኦሮሞ ባላባት ልጅ ነበሩ (አባ ቦራ በታቦር ዋሚ፤ ገጽ 9)
ራስ አበበ አረጋይ  መከላከያ ሚኒስትር
አቶ ይልማ ዴሬሳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ የገንዘብ ሚኒስትር
ደጃዝማች ክፍሌ ዳዲ የጎንደር አስተዳደር
አቶ ቡልቻ ደመቅሳ የእርሻ ሚኒስትርን ምክትል የገንዘብ ሚኒስትር
ሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ የክብር ዘበኛ አዛዥና የባህል ሚኒስትር
ደጀዝማች ገረሱ ዱኪ የኢሊባቡርና የጎሙገፋ አስተዳዳሪ
ሜጀር ጀኔራል ደምሴ ቡልቲ የሁለተኛው ክፍለ ጦር አዛዥ
ሌተና ጀኔራል ጃጌማ ኬሎ የአራተኛው ክፍለጦር አዛዥና የባሌ አስተዳደር
ፊታውራሪ ለማ ወልደጻድቅ የሲዳሞ ምክትል አስተዳደር
ሜ/ጀኔራል አበራ ወልደማርያም የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ
ደጃዝማች በቀለ ወያ የጨቦና ጉራጌ አስተዳደር ከዚያም የጨርጨር አስተዳደር
ደጃዝማች ካሳ ወልደማርያም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትና የእርሻ ሚኒስትር
አንባቢያን መረዳት ያለብን ሁላችንም በመጀመሪያ ደረጃ ኢትዮጵያውያን መሆናችን ነው፡፡ ሕዝባችን በጋብቻ፣ በእምነት፣ በባሕል፣… የተሳሰረ በመሆኑ መሰረት የሌለው ታሪክ እያነበነቡ ሊበታትኑን የሚያስቡትን ታሪካዊ መረጃ እያቀረብን ወግዱ ልንላቸው ይገባል፡፡ ድር ቢያብር አንበሳ ያስር ነው፤ ምኒሊክም ያስተማሩን መቻቻልን አንድነትንና ፍቅርን ነው፡፡
ዶ/ር ካሳሁን በጋሻው