Friday, January 16, 2015

አርበኞች- ግንቦት 7 ለ አንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ ለ ኢትዮጰያ ህዝብ፣ ለመከላከያ ሰራዊቱና ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥሪ አቀረበ።

image
አርበኞች- ግንቦት 7 ለ አንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ ለ ኢትዮጰያ ህዝብ፣ ለመከላከያ ሰራዊቱና ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥሪ አቀረበ።
ጥር ፯(ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ንቅናቄው በግንቦት 7 እና በ አርበኞች ግንባር መካከል የተደረገውን ውህደት አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፤ << እኛ መዋሃድ መወሰናችንን ስንገልጽ፤ በተናጠል ከሚደረጉት – በጋራ የሚደረጉ የትግል ጥረቶች ውጤታማ ይሆናሉ በሚል ብቻ ሳይሆን፣፡”የተቃዋሚ ድርጅቶች፣ በምንም ዓይነት ሁኔታ በሀገርና በሕዝብ ደረጃ ትርጉም ያለው ሥራ በጋራ መስራት አይቻሉም’ የሚለውን፣ አስከፊ ተመክሮና አመለካካት ለመስበርም ጭምር ነው።” ብሏል።
<<ከትናናሽ ድርጅቶች ዙሪያ ከሚሽከረከሩ ሀሳቦችና ስሜቶች ለመውጣትና ሀገራዊና ሕዝባዊ የሆነውን ጉዳይ ለማስቀደም የወሰነ ማንኛውም ድርጅት፣ አርበኞችና ግንቦት7፣ እንደደረሱበት የውህደት ውሳኔ ፤ወይም በሌሎች በጋራ ሊያሰሩ በሚችሉ ስምምነቶች አብሮ ለመስራት መወሰን የማይችልበት ምንም ምክንያት አይታየንም።>>ብሏል ንቅናቄው።
<<በወያኔ አድሎ ስርዓት የተንገፈገፈና ትግሉን ለመቀላቀል የቆረጠ ማንኛውም ዜጋ፣ የተገኘውን አጋጣሚ በመጠቀም ትግሉን መቀላቀል ይችላል>>ያለው አርበኞች-ግንቦት 7፤ <<የኢትዮያ ሕዝብ በአንድነት የተነሳ ቀን ደግሞ፣ የወያኔ ግብዓተ መሬት ይፈጸማል ብለን ከልብ እናምናለን።>> ሲል የመተባበርን አንድነት በ አጽንኦት ገልጿል።
ንቅናቄው ለተቃዋሚ ድርጅቶች ባስተላለፈው መልእክት <<ዛሬ በአርበኞችና በግንቦት 7፣ የተጀመረው ጉዞ ውጤታማ በመሆን ሀገራዊና ታሪካዊ ትርጉም እንዲኖረው፣ ሌሎችም በተግባር የምትንቀሳቀሱ ተቃዋሚ ድርጅቶች፣ ወያኔን የማስወገድንና ብሎም ሀገር የማረጋጋቱን ሀላፊነት በጋራ እንድንወጣ የሚያስችል መቀራረብ እንድናደርግ ፣ በውህደት በመሰረትነው- በአርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ዴሞክራሲ፣ ንቅናቄ፣ ሥም፣ ጥሪያችንን እናቀርባለን።>> ብሏል።
ንቅናቄው ለወታደራዊና የፖሊስ ሠራዊት አባላት ባስተላለፈው መልእክት ደግሞ፤<<የወያኔን ዘረኛና አምባገነን ቡድንን ዕድሜ ለማሳጠርና ሁላችንንም በእኩልነት የምታስተናግድ ሀገር እንድትኖር፣ የሰሞኑን ቆራጥ የዓየር ሃይል መኮንንኖች ያሳዩትን ዓርያነት በመከተልና በተገኘው አጋጣሚና ሁኔታ በመጠቀም በየቦታው የሚደረገውን ትግል እንድትቀላቀሉ በውህዱ ድርጅታችን ሥም፣ ጥሪያችንን እናቀርባለን።>>ብሏል።
ንቅናቄው በመጨረሻም፦<<የተከበርከው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ፣በረጅም ታሪክህ አይተሄው ለማታውቀው ውርደት፣ ክፋት፣ የመከፋፈልና የመጋጨት አደጋ የዳረገህን እና ሀገርና ሕዝብን የማራከስና የመሸጥ ዕኩይ ተግባር የተጠናወተውን አገዛዝ ከነግብር አበሮቹ ጠራርጎ ለማስወገድ በተጀመረው የጋራ ትግል ውስጥ በቀጥታ እንድትሳተፍ አለያም በምትችለው ቀዳዳ ሁሉ ድጋፍ እንድታደርግ፣ በአርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ዴሞክራሲ፣ ንቅናቄ ሥም፣ ጥሪያችንን እናቀርባለን።>> ሲል መግለጫውን ቋጭቷል።

አንዳርጋቸው ጽጌ (ይናገራል ፎቶ)


ይህ ታሪካዊ ፎቶ የተገኘው ከጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ነው:: አንዳርጋቸው ጽጌን ከነወታደር ልብሱ በረሃ ላይ ያሳየናል:: ፎቶው ታሪካዊ ከመሆኑ አኳያ ሊቀመጥ የሚገባው ነው:: ለዚህም ነው ይናገራል ፎቶ ብለን ያቀረብነው:: ፎቶውን ካሳየን አይቀር ታዋቂው ጸሐፊ ጸጋዬ ገብረመድህን አረአያ ከፎቶው በታች “አንዳርጋቸው ጽጌ ልዩ የኢትዮጵያ አፈር” ሲል በአውስትራሊያ ለሚታተመው አሻራ መጽሔት ላይ የጻፉትን ታሪካዊ ትንታኔም ዘ-ሐበሻ አስተናግዳዋለች::
andargachew Tisge
አንዳርጋቸው ጽጌ ልዩ የኢትዮጵያ አፈር
ከጸጋዬ ገብረመድህን አረአያ
በ1950 ዓ.ም. ደብረብርሀን በሚገኘው የሀይለ ማርያም ማሞ ሁለተኛ ደረጃ ትም ህርት ቤት ስገባ የዓጼ ዘርአ ያዕቆብ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዳይሬክተር የነበሩ ት አቶ ጽጌንና ባለቤታቸውን በየቀኑ አያቸው ነበር። ወይዘሮ አልታዬ ዘወትር በቀኝ እጃቸው እየደገፉት እሱ ድክ ድክ የሚልም ትንሽ ልጅ አይረሳኝም። የየዕለቱ ትርኢት ስለነበር . . . . ብዬ አልፌዋለሁ።
ከዘመናት በኋላ እኔም አድጌና በመንግስት ስራ ኃላፊነት ቆይቼ ይህቺን አገር የ ሚያናውጡ ሰዎች ወደ ፖለቲካው መድረክ ሲመጡ በመጥረጊያ ከተጠረጉት የጥን ት ጋዜጠኞችና የሚዲያው አመራር አባላት ጋር እዳሪ ስንጣል ያ ልጅ ይመስለኛል ከ ጦቢያ ቢሮ ያገኘኝ። አንዳርጋቸው ጽጌ ከመቼው በወያኔ መርከብ ተሳፍሮ ፣ ከመቼ ው ወርዶ፣ ከመቼው ወደ ተቃዋሚነት እንደተሸጋገረ የፖለቲካው ጉዞ ቅፅበት አልገ ባኝ አለ። የተቀላቀለው ቡድን አካሄድና ይልቁንም “አማራ” በተባለው የህብረተሰብ ክፍል ላይ ያለውን ግልጽ አቋም በመረዳት “የአማራው ህዝብ ከየት ወዴት?” የሚል መጽሀፍ ጽፎ ለህዝብ ሲያቀርብ እኔም ሆንሁ ብዕሩ እልፍ የሚጥለው ጓደኛዬ ሰውነ ት መልካሙ ጥርጣሬ ውስጥ ወድቀን ነበር። ስለዚህ ሰውነት (በብዕር ስምነት ይቆይ ና) “በኢትዮጵያዊነት ላይ የተወረወረ ቦምብ” በሚል ርዕስ የራሱን ቦምብ አፈነዳ። አ ንዳርጋቸው አስተያየት የመስጠት መብታችንን እየጠቀሰ በመሰረቱ ግን “አቶ ሰውነ ት ትክክለኛው ጉዳይ የገባቸው አይመስለኝም” ብሎ ከእኔ ጋር በጦብያ ቢሮ (አክፓ ክ ነው እንባል የነበረው) ደስ የሚልና ምሁራዊ ቅባት የነበረበት ሙግት ገጠምን። ድር። በእኔ በኩል ይህን ድርጅት ፋሽስት ለማለት የፈለግሁት ኢሰብዓዊ አቋሙን ፣ ደ ም የማፍሰስ ሱሱን፣ ለህይወት አንዳች ዋጋ ለመስጠት ያለመፈለግ ዝንባሌውን . . . ለ ማሳየት ነበር። አንዳርጋቸው ደግሞ የተማሪው ፖለቲካ ፍሬ እንደመሆኑ ወደ ክላሲ ካል ትርጉሙ ለመሄድ ነበር የፈለገው። በነገራችን ላይ አንዳርጋቸው በችኮላ ላይ ስለ ነበርና ጊዜም ስላልነበረው ስለፋሺዝም ብዙ ሳንወያይ ተለያየን። ጊዜ ቢኖረው ኖሮ “አብዮታዊ ዴሞክራሲ” ከቤኒቶ ሙሶሊኒ “አቫንቲ” እና ከፋሽዝም የተዳቀለ መሆኑን (ያው መጻህፍት በመጠቃቀስ) አስረዳው ነበር። የተማሪ ፖለቲካና የሶቭየት (ኢምፓ የር) ቀኖናውያን እንደሚሉት “ቀኝ ክንፍ ፍልስፍና” (ኢዲዮሎጂ) አለመሆኑን ለማብ ራራት እሞክር ነበር። በነገራችን ላይ ሙሶሊኒ ሮጦ ከሂትለር ክንፍ ሥር ሳይወድቅ የ ምዕራቡ ዓለም መሪዎች (እነ ሩዝቬልትና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሐል) ፋሺዝምን እንደ ታላቅ የዓለም ፖለቲካ የዕድገት ማስረጃ አድርገው ያዩት ነበር። ፋሺዝም የመ ጣው እንደ ሬቮሉሲዮን ስለሆነ የቀኝ ክንፍ ፍልስፍና አይደለም። ይህ ክርክር ያልተ ፈጸመና በአጭሩ የቀረ ጭንጋፍ ሙግት ነው። አንዳርጋቸውን በዚህ ዓይነት ሙግት የምዘርር አይደለሁም። እሱ ላቅ ያለ አመለካከትና ትንፋሹ ሳይቀር ሕይወት ያለው ነ ው። በዓለም አቀፍ የቅንጅት ኮሚቴ ውስጥ አብረውት የሠሩ ዘመዶችና ወዳጆች አሉ ኝ። ይሳሱለታል። “አንዱ . . .አንድዬ . . . አንዳርግ . . .” ይሉታል። የቅንጅት አመራር አባላት በወያኔ ወኅኒ ዓለም በተወረወሩ ጊዜ በሳምንት ውስጥ ለቢቢሲ ሰባት ቀናት መግለጫ ሲሰጥ ሰምቼዋለሁ። በበሰለ አሳብ ፣ በጠራ ቋንቋና በጨዋ አንደበት። ይህ ብቻም አልነበረም ፤ በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ ስብሰባ በአክራ ሲካሄድ የጋ ናን ሚዲያ በተለይ፣ እና የአፍሪካ መገናኛ ብዙሀንን በአጠቃላይ በቁጥጥሩ ስር አው
ሎበኢትዮጵያላይእየተካሄደያለውን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊ ሰዕ ልበሚያስደንቅአኳኋንሲያቀርብየነ በረጀግናነው።አንድመቶየፕሮፖጋን ዳ ሰራዊት የማይችለውን የአትላስ ሽክ ምብቻውንበአስገራሚሁኔታያከናወ ነልዩፍጥረትነው።እኔደግሞየዚህን ሥራአስቸጋሪነትበልዩልዩገጽታውአ ውቀዋለሁ ባይ ነኝ።
“ተራራ አንቀጠቀጥን . .” የሚሉ የ መሣርያ አምላኪዎችና ባሩድ ነካሾች ይ ህንታላቅነፍስ-የኢትዮጵያነፍስናከ ኢትዮጵያ ጎን የወጣ ልጅ -ከአስመራ እ ስከዱባይ…ከየመንእስከደቡብአ ፍሪካ….ከእንግሊዝአገርእስከአውስ ትራሊያናአሜሪካወዘተባሰማሯቸው የስለላናየአፈናጓዶችአማካኝነትዓለ ምን ሲያካልሉ ከርመዋል። ቁጥር ስፍ ርየሌለውገንዘብምአፍስሰዋል።በመ ጨረሻምዱባይ፣አስመራ፣ደቡብአፍ ሪካ ያሉት የቆስጤ ሴረኞች … የምስራ ች ተባብለዋል። እነሆ ውቡ ወፍ ተጠ ምዷል። የትግሉም ሆነ የዓለምም ፍጻ ሜግንአይደለም።አይሆንምም።አን ዳርግየከፈለውሰማዕትነትበሚቀጥሉ ትየኢትዮጵያትውልዶችበክብርይወ ሳል።ለአዲሱዘመንአውራጀግናበማ ግኘታችን ልንኮራ ይገባናል።
እግዚአብሄርይከበር-ስለአንዳርጋ ቸው!አገሮችበታሪካቸውትልልቅፈተ ና ያጋጥማቸዋል ። ሕዝብ በችግር ሰዓ
ትይጠራራል። እንደዚህ ላስቀምጠው። – በጭንቅ ሰዓት ፣ በፈተና ጊዜና ቀን የጎደለ በ ሚመስልበት ወቅት ከማዕበሉ ጋር የሚታገልና ድልን የሚያስገኝ ፤ ካልተሳካም በድፍ ረቱ ፣ በልበ ሙሉነቱ ይህን ያህል የማይባል ረቂቅ ድልን የሚያቀዳጅ ሰው ይሻል። በ ደሙና በማይነገር – በማይበገር ጥንካሬው አማካይነት ወጀቡን የዋኘ ፣ ማዕበሉን ጸጥ ያደረገና የሚያደርግ ፤ ለዛሬው ትውልድ የነጻነት ብልጭታ ያሳየ (የሚያሳይ) ፤ ለመ ጪው ከውስጡ ብርሀኑ ቦግ ያለ የትግልን ችቦየሚያቀብል (ያቀበለ) ሰው ይሻል።
የህንድ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀዋህርላል ኔህሩ በታላቁ የዓለም ሰው በማህተመ ጋንዲ (በአክብሮት ጋንቲጂ) ሥርዓተ ቀብር (በሂንዱ ልማድ ቀብር ሳይሆ ን የማቃጠል ሥርዓት ነው ያለው) ላይ ሲናገሩ የተጠቀሙበትን አንድ ሐረግ ልሰርቅ አፈልጋለሁ። ለአንዳርጋቸው ጽጌ ለመስጠት! “ጋንዲ ልዩ አፈር ነው። ከእኛም ልዩ የ ሚያደርገው ልዩ አፈርነቱ ነው።” ብለዋል። እኔ ራሴ መንቀሳቀስ የማይሆንልኝና በማ ንኛውም የአገሪቱ ታሪክ ላይ ይህ ነው የሚባል አሻራ ለማሳየት የማይሆንልኝ ቧጋች ነ ኝ። ሰዎችን የማወቅ ዕድል ግን አለኝ። ጀግና ብቻ ሳይሆን ባንዳና ምንደኛም አውቃ ለሁ። ተጎልቼ ይህን የመሳሰለውን ወግ እጠርቃለሁ። አላጋንንም።
አንዳርጋቸው እንደማናችንም ከአፈር -ከኢትዮጵያ አፈር ተፈጥሯል። እእ! ከኢትዮጵያ ልዩ አፈር! ስለዚህ ‹ልዩ ሐረግ› የኔህሩን ሽንት ይባርክ! የአንዳርጋቸው ጠላፊዎችና አሳሪዎች የጀግና መንፈስ የላቸውም እንጂ በክብር የ ሚጠብቁት ልዩ እንቋቸው በሆነም ነበር። ሚኒልክ የጎጃሙን ንጉ ስ ምርኮኛቸውን የተንከባከቧቸው በክብር በመጠበቅ ነበር። ወያ ኔዎች ከፈሪ ልብ የተቆረጡ ፈሪዎች በመሆናቸው እንጂ አንዳርጋ ቸውን ያንን ያህል የስጋ ስቃይ ባላደረሱበት ነበር። ለትርዒት መ ላልሰው ባላቀረቡትና የደስታቸው ምንጭ ባላደረጉትም
ነበር። እነሱ ዛሬ የሥጋ ቁስልና የመንፈስ ስቃይ የሚግቱት ሰ ው ነገ የታሪካቸው ፈርጥ የሚሆን ልዩ አፈር ይሆናል። ሃሌሉያ! በአጠቃላይ አንዳርጋቸው የነጻነት ተጋድሎውን የተወጣ ፤ ምድ ራዊ መከራን፣ አካላዊና መንፈሳዊ ቅጣትን ሁሉ የተቀበለ፣ትግሉ ን ለሌሎቻቸን በአደራ ያስተላለፈ ታላቅ ነፍስ ነው። ታላቁ ህንዳ ዊ ጋንዲ “ማሀትማ” ይባላል። “የተከበረ ነፍስ” ማለት ነው። የዓለ ም ጌታ እንዳለው ነቢይ በአገሩና በዘመኑ አይከበርም ሆነና አንዳ ርጌ የሚገባውን አክብሮትና አድናቆትን ጠላት በተንጣለለበት አ ገሩ ለማግኘት ባይችልም በውጪው ዓለም የተበተኑና የውስጡ
ንም የሚወክሉ ወገኖች ሁሉ ህዝብ ለማንም ሰጥቶ የማያውቀው ን ክብር ሰጥተውታል። የኢትዮጵያ ጆን ኦፍ አርክ፣ የኢትዮጵያ ማንዴላና ጋንቲጂ ብለውታል። ጠላቶቹ የአገር አጥፊዎች እየተዘ ባበቱበት፣ እየሰደቡትና እንደ “ጊኒ ፒግ” መላልሰው በቴሌቪዥ ን እያቀረቡት ነው። ልዩ ወፋችንን—ናይቲንግኤላችንን ባሰቡ ቁ ጥር መንፈሳቸውን የሚያሸብር አንዳች ስሜት ተጣብቷቸው ቆይ ቶ መያዙንና በእጃቸውመግባቱን ያለማመን ችግር ደርሶባቸዋል። “ሶባጅ – ሳቬጅ!” ፍሬደሪክ ኤንግልስ ወዳጁና ጓዱ ስለነበረው ካ ርል ማርክስ በቀብሩ ሥነ ሥርዓት ላይ የተናገረው ምስክርነት ት ዝ ይለኛል። The best hated man ይለዋል። (ከሁሉ የበለጠ የ ተጠላ ሰው እንደማለት ነው።) በወቅቱ በተፈጠሩም ሆነ በኋላ በተነሱ ትውልዶች ዘንድ ግን ካርል ማርክስ The best hated man ብቻ ሳይሆንThe best loved man ሆኗል። አንዳርጋቸው ጽጌ በእጃቸው በገባ ሰዓት ማራኪዎቹ ወያኔዎች የተሰማቸውን ደ ስታ ጣኦታቸውና የሴረኞች ሁሉ አባት የሆነው አምባገነን ከሞተ በት ዕለት ኅዘን ጋር ማስተያየት ይቻላል። አዎን አንዳርጋቸው በ ወያኔዎች ለወያኔዎች የቀትር ጋኔን ነበር። የሚያስፈራ ነፍስ – እ ንኪያስ The most hated man ለኢትዮጵያ ሰፊ ህዝብ ደግሞ The most loved man! ይታደለዋል እንጅ …በዚህም መሰረት ይቀጥላል። 
አበበ አረጋይ …በላይ ዘለቀና አሞራው ውብነህ፣ ጅማ ሰንበቶ፣ በቀለ ወያ፣ አብዲሳ አጋ ሲደመር ሲደማመር ቅዱስ ያሬድ፣ ዮፍታሄንጉሴ፣ ዶክተር ዓለመወርቅ . . . ነው። አ ላበዛሁበትም። ክብር ሁሉ አልከመርኩ በትም። ቢሆንልኝ ከነጋ ድራስ ተሰማ እሸቴ ጋር “እንደምን አድርጌ ከፍቼ ላውጣው” እያ ልኩ አቀነቅን ነበር።
ጀግኖች የኢትዮጵያ ወጣቶችና ጸጥ ወዳለው ዓለም የምትሸ ጋገሩ አእሩግ! ናፖሊዮንም ተማርኳል።ታላቁ ጄነራልና ጦረኛ መ ሪ። ያንን ታላቅ የጦር መሪና ገናና የዓለም ገዢ የማረከው እንግሊ ዝ ደግሞ ጀግንነትን የማድነቅ፣ ሰብዐዊ መብትን የማክበር ባህል -ድንቅ ባህል ባለቤት ስለሆነ አክብሮ ነበር የያዘው። ናፖሊዮን ከ ሴንት አልባ አምልጦ እንደገና ለመቶ ቀናት ፈረንሳይን መርቷል። ማን ያውቃል የዴስቲኒን አድራሻ! ማን ያውቃል የዴስቲኒን የፍጻ ሜ ምዕራፍ? የዚህን ወጣት ታሪክ ከሥር መሰረቱ የሚያወጉ ወዳ ጆቹና የትግል ተካፋዮች እንዳሉ አያጠራጥርም። በመድረክና እን ደኔም በመስኮቱ ንግግር ፣ ራቅ ብሎም በመሄድ የከፈለውን መስ ዋዕትነት በጨረፍታ ለምናውቀው አንድ መደምደሚያ ላይ እንደ ርሳለን። አንዳርጌ የሚከበር ፣ የሚወደድና በአእምሮው ትልቅነት ፣ በሰብአዊነቱና በአርቆ አሳቢነቱ – ማናቸውንም የነጻነት መስዋዕ ትነት ለመክፈል ባሳየው ቆራጥነቱ የሚደነቅ ነፍስ ነው። እንደሱ ያሉ ሰዎች ከጊዜያቸው በፊት መጥተው ፈተናን ሁሉ ይቀበላሉ። መንፈሱንና ስጋውን ለአምላክ እንዳስረከበ ደካማ ሰው እግዚአብ ሄርን የምለምነው አንድ ነገር አለኝ። ሲድራቅ ፣ ሚሻቅና አብድና ጎን ከሚንቀለቀለው እሳት አራት ሰው አድርጎ በፍጹም አቸናፊነ ት ያወጣቸው አምላክ ምን ይሳነዋል? በወያኔ እስር ቤት የሚንገዋ ለል አንበሳ በሕልሜም በውኔም ይታየኛል። እናንተስ ጎበዝ! በክ ርስቶስ ላይ ያሾፉ፣ የሾህ አክሊል በራሱ ላይ የደፉበት ፣ እስኪደ ክማቸው የገረፉት፣ ጎኑን የወጉት የሰው አራዊትና አራዊት ሰዎች ሥዕል አይመጣባችሁም? “ሶባጅ! ሳቬጅ!” “አኒማሌ” አል ጣልያ ን! ለወያኔዎች አንድ ምስጢር ልተውላቸው እወዳለሁ። “አንዳር ጋቸው ጽጌ መንፈስ ነው።”
ይህን ትንቢት ተቀበሉኝ። አምላካችን ለዚች ሀገር እንደማ ዕዘን ድንጋይ ሆነው ሕዝቡን የሚያገለግሉ መሪዎች ይሰጠናል። የሰራዊት ጌታ የምህረት ተስፋ ነው። እንደ ድንኳን ካስማ የሆኑ አስተዳዳሪዎችና እንደ ጦር ሜዳ ቀስት የሆኑ የጦር አዛዦችን ይ ሰጠናል። ብርቱ የሆኑ ጀግኖችን እንጠብቃለን። ከላይ ከጸባዖት! ከመሬቲቱ ከኢትዮጵያ ማኀጸን።እነዚህ ደግሞ የኢትዮጵያን ጠላ ቶች ረግጠው ከመንገድ ጭቃ ጋር እንደሚለውሱ ያደርጋል – ማ ን? የኃያላን ኃያል! የጌቶች ጌታ! ትዕቢተኞች ይዋረዳሉ። ዕብሪተ ኞች ይንኮታኮታሉ። (ከነቢዩ ኢሳያስ የትንቢት ቃል ያዳቀልሁት ነው።)
የአንዳርግ “ሌጋሲ” – ኑዛዜና ቅርስ ነው። የትውልድ ቅርስ፣ የትግል ቅርስ … የመስዋዕትነት ቅርስ! በአንዳርጋቸው ላይ የሚፈ ጸ መውን ኢሰብዓዊ ድርጊት ሁሉ ሳስበው ከጥንት ጀምረው ኢ ትዮጵያን ከሰለጠነው ዓለም ጋር ለማሰለፍ ብዙ መስዋዕትነትን የ ከፈሉ ሰዎች እነ ሎሬንዞ ታዕዛዝ፣ ተስፋዬ ተገኝ፣ ተክለ ሃዋርያት ዋየህ፣ ሐኪም ወርቅነህ እሸቴ ቢሞቱ፤ እነ ሐዲስ ዓለማየሁ፣ ቢ ትወደድ ዘውዴ ገብረ ሕይወት፣ እነ አማኑኤል አብርሀም… በህይ ወት ቆይተው ኢትዮጵያ የገባችበትን የኋሊት ጉዞና ቅድመ መሳፍ ንት ዘመን አገዛዝ አይተውታል። የተጓዙበትን ርቀት ሜዳ ስለሚ ያስታውሱ (ለምሳሌ የባርያ አስተዳዳሪነትን ለማስቀረት የተደረገ ውን ያነሧል) በኢትዮጵያ አዲስ የባርያ ስርዓት የገባ ይመስላል። እንደቀድሞው በዓለም አቀፉ አካል ቁጥጥር ቢደረግ እኮ ከድርጅ ቱ ከሚባረሩ አገሮች ግንባር ቀደም የምትሆነው የእነ ኃይለማርያ ም ኢትዮጵያ በሆነች ነበር። ኢትዮጵያ ዛሬ የእነ ኃይለማርያም ናት። ነገ ነው የደቂቀ አንዳርጋቸው የምትሆነው።
አንዳርጋቸው ጽጌ በወያኔ ዓለም አቀፍ ሴራ ከተያዘበት ዕለት ጀምሮ በተለይ በውጪ ያለው ኢትዮጵያዊ በነቂስ ወጥቶ የት ግል ቃል ኪዳን ሲያደርግ ይታያል። ይኽ ደግሞ የሚቀጥል ነው። ሕዝብ በራሱ አነሳሽነት ተንቀሳቅሶ በራሱ መፈክር አቋሙን ሲገ ልጥ ለማየት የታደልንበት አንድ አጋጣሚ የአንዳርጋቸው ሌጋሲ ይመስለኛል። “እኔ አንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ” የሚለውን ከኢትዮጵያ ጋር የተካሄደ መሐላ በግንቦት ሰባቶች በድርጅታዊ አሰራር የመጣ መስሎ ይታይ ይሆናል። አይደለም። ሕዝቡ ጀግንነቱ፣ ወኔው፣ ወ ንድነቱ፣ የተሟሟቀበትና የተነሳበት ነበር ለማለት ይቻላል። በእ ኔ በኩል ምርኮ ተብሎ የተጠራውን “ክተት” ለማለት እወዳለሁ። …. ያገሬ ሕዝብ ጆሮ ይሰጠኝ ይሆን?

በዞን 9 ጦማርያንና ጋዜጠኞች ላይ የቀረበው ክስ በድጋሜ ‹‹ተሻሻለ››


.በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር......................... ጦማርያኑና ጋዜጠኞቹ ጥር 6 ቀን 2007 ዓ.ም ለ15ኛ ጊዜ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ የተሰየመው ቀደም ብሎ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ የተመሰረተው ክስ እንዲሻሻል ባዘዘው መሰረት የፌደራል አቃቤ ህግ ክሱን ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ያላሻሻላቸው ነጥቦች ስለነበሩ እነዚህኑ ነጥቦች በድጋሜ አሻሽሎ እንዲቀርብ ባዘዘው መሰረት የተሻሻለውን ክስ ለመስማት ነበር፡፡
በመሆኑም የፌደራል አቃቤ ህግ አሻሽየዋለሁ ያለውን ክስ ይዞ ቀርቧል፡፡ ክሱ ‹‹ሌሎች ብዙ ‹ኬዞች› ስላሉ›› በሚል ምክንያት በችሎቱ ላይ በንባብ እንዲሰማ አልተደረገም፡፡ ተሻሻለ የተባለው ክስ ለተከሳሾችና ለጠበቆች እንዲደርስ የተደረገውም እዚያው ችሎት ውስጥ ነው፡፡ ክሱ በንባብ ባለመሰማቱና ጠበቆቹና ዳኞቹም ስላላነበቡት በሚል ተሻሻለ በተባለው ክስ ላይ ምንም አስተያየት አልቀረበም፡፡ በመሆኑም ክሱ መሻሻል አለመሻሻሉን ለመመርመርና ብይን ለመስጠት ለጥር 20 ቀን 2007 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ የጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ጠበቃ የሆኑት አቶ አምሃ መኮንን እንዳሉት በቀጣዩ ቀጠሮ ላይ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ተሻሽሎ ካልሆነ ነጥቦቹን ፍርድ ቤቱ ውድቅ ያደርጋል ብለው እንደሚጠብቁ ገልጸዋል፡፡ ‹‹በእኛ በኩል ከዚህ በኋላ የማሻሻያ ሀሳብ አቅርበን ጊዜ አንፈጅም፤ ከሚቀጥለው የፍርድ ቤቱ ውሳኔ በኋላ መደበኛ ክርክራችንን መቀጠል ነው የምንፈልገው›› ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ በዛሬው የችሎት ውሎ ላይ በጣም ብዙ እስረኛ (ተከሳሽ) ችሎቱ ውስጥ በመገኘቱ ምክንያት ከፍተኛ የቦታ ጥበት ማጋጠሙ ተስተውሏል፡፡ በአጠቃላይ እስከ 70 የሚደርሱ እስረኞች በችሎቱ ተገኝተዋል፡፡ ስለሆነም ችሎቱን መታደም የቻሉት ጥቂት ጋዜጠኞችና ዲፕሎማቶች ብቻ ሆነዋል፡፡ የተከሳሽ ቤተሰብና ወዳጅ ዘመዶች ችሎቱን መታደም አልቻሉም፡፡

Ethiopia dam will turn Lake Turkana into ‘endless battlefield’, locals warn

Kenyans near world’s largest desert lake predict conflict, hunger and cultural devastation when hydroelectric project is completed

An armed Turkana man on the shore of Lake Turkana. Locals fear the completion of the Gibe III dam could exacerbate tension in the region between Kenyans and Ethiopians. Photograph: Siegfried Modola/Reuters
January 13, 2015 (The Guardian) — People living near Lake Turkana in northern Kenya have little understanding that the fresh water essential to their development is likely to dry up when a huge hydoelectric dam in neighbouring Ethiopia is completed.
Fishermen, farmers, teachers and others living near the world’s largest desert lake say Turkana’s volume has reduced significantly over the past 30 years because of higher temperatures and changing weather patterns.
But few of the 100 peopleinterviewed by a Kenyan researcher for International Rivers watchdogsaid they had been consulted or warned what could happen when the reservoir of the Gibe III dam, one of Africa’s largest hydropower projects, is completely filled in about three years’ time. The $1.8bn construction project, which is 90% complete, will start limited power generation in June.
The downstream impact of the dam is hotly contested. Some hydrologists have predicted that Ethiopia’sexpansion of water-intensive sugar and cotton plantations on the Omo river, which the Gibe 111 dam allows, could reduce flow to Lake Turkana by up to 70%. This would kill ecosystems and greatly reduce the water level of the lake.
This, says International Rivers, could make the difference between marginal livelihoods and famine for the tens of thousands of already vulnerable people who depend on the lake for their livelihoods.
When told of the possible impact of the project, ethnic groups and communities near the lake predicted widespread conflict, hunger and cultural devastation. “If the Gibe III dam is constructed, the lake will dry up and this will lead to desertification and there will be depletion of resources: there will be no fish, no farming, and low humidity [and less rain]. If that is the case, the community will be finished,” said Sylvester Ekariman, chairman of the council of elders in Kakalel pastoral village.
A far-away view of the Gibe III dam under construction in Ethiopia s Omo valley and surrounding hills. Photograph: Jenny Vaughan/AFP/Getty Images
Currently, the lake, which could split into two if incoming water is restricted, helps to prevent conflict between communities in Ethiopia and Kenya, and locally between the Turkanas and the Rendille ethnic groups, who live on opposite sides of the lake. If the lake shrinks, conflict is much more likely, says the report.
Helen Alogita, a seed seller, told researcher Narissa Allibhai that she feared the people living on the other side of the lake. “They will come and kill us and that will bring about enmity among us as we turn on each other due to hunger. Find the person [building the dam] and ask them where they expect our communities to go? Where are our Kenyan leaders? If famine and hunger will make us die of starvation, where will they get votes from?”
Fisherman Dennis Epem said: “When the lake goes back, our enemies, which are the people of Ethiopia, will be reaching here. They have weapons, but we don’t have weapons. How will we defend ourselves when the people of Ethiopia cross? This lake is our security.”
Many of the people interviewed in the 14 communities said they were angry that an Ethiopian dam should affect Kenyans. “Not a single country [should] harm the other one by taking its waters without discussing with the other countries, because water is life. It should not be decided by one country. Who is funding these Gibes? They should withdraw their assistance or the loans they are giving,” the researcher was told.
Children sitting on the Omo river bank, which is cracked due to falling water levels.Photograph: Alamy
“Awareness of the dam’s impacts and development process is extremely low,” said Allibhai. “A majority of interviewees were extremely uninformed. Any consultations with local communities were either minimal or non-existent. People in the villages had either heard about the dam only through local NGO Friends of Lake Turkana’s awareness-raising or through rumours; misinformation was rampant.
“Those in the towns were slightly more informed, especially the few with access to the internet – but even so, not one interviewee was sure of the details of the upstream developments, agreements and progress,” she said.
“All community members are opposed to the dam and irrigated plantations, as it will deprive them of their livelihoods and lead to increased famine, conflict and death. Their messages to the Kenyan and Ethiopian governments and the international community reflect their despair, and feelings of helplessness, anger and betrayal.”
Many older people said the developments in Ethiopia could tip the region into a crisis because climate change had made them more vulnerable. The lake was already much smaller than it was 30 years ago and villages like Impressa Beach, Lokitoenyala and Nachukui used to be under water, said locals. Rains are unpredictable and temperatures and wind have increased.
“These water grabs will disrupt fisheries and destroy other ecosystems upon which local people depend,” said Lori Pottinger, International Rivers’ Africa campaigner. “Local people have not been consulted about the project nor informed about its impacts on their lives.”
Both the Kenyan and Ethiopian governments have strongly backed the dam, which they maintain will increase development by providing more electricity.
The Ethiopian government this week strongly rejected claims that the dam would harm Lake Turkana. A spokeswoman said: “The dam will provide a regular flow of water to Lake Turkana, which gives the possibility of providing a water supply throughout the year, whereas the lake is currently short of water in the dry season. The regular flow of water will also improve the aquatic life of Lake Turkana, providing a better livelihood for people living round the lake.
“The project … is instrumental in forging regional integration – the Gibe III dam will have a role in the realisation of close economic cooperation between Ethiopia, Kenya and the countries beyond. Kenya [will] obtain more than 300MW of electricity from Ethiopia.
“Campaigners are consciously trying to distort all these positive developments … in order to incite misunderstanding between the fraternal countries of Ethiopia and Kenya.” she said.
The Kenyan government was invited to respond to the report but has so far declined.
Suggestions for action by the communities ranged from using force to stop the dam, persuading the the Kenyan government to stand up for the people of Turkana and Marsabit, pressing for donors to withdraw funding and requesting compensation.
Source: The Guardian