Sunday, December 8, 2013

ሚሚ ስብሃቱ ጠረጴዛ ምን ያደርግላታል?


ከዳዊት ሰለሞን
mimi sibehatuጠረጴዛ ከመመገቢያነት፣ለመጻፊያ ማስደገፊያነትና ከቁሳቁስ ማስቀመጫነት በተጨማሪ በዙሪያው በሚኮለኮሉት ወንበሮች የተነሳ ሰዎችን በአንድነት መሰብሰብ በመቻሉ የሐሳብ መንሸራሸሪያ መድረክ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡በጠረጴዛ ዙሪያ የሚቀመጡ ግለሰቦችና ቡድኖች በፊት ለፊታቸው በተዘረጋው ጠረጴዛ ላይ ሐሳባቸውን፣አመለካከታቸውንና አይዶሎጂያቸውን ያቀርባሉ፡፡የተጣሉ፣ልዩነት ያለባቸው ወገኖችም በጠረጴዛ ዙሪያ ቅራኔያቸውን ለማጥበብ ይደራደራሉ፡፡

ኔልሰን ማንዴላ እና ኢትዮጵያ!!

ተጨማሪ ማስታወሻዎችና ከኢትዮጵያ የወሰዱት ሽጉጥ መጨረሻ

የነጻነት ታጋዩ ኔልሰን ማንዴላ በ95 አመታቸው ከዚህ አለም ሲለዩ፤ የተለያዩ አገሮች እንደየራሳቸው ግንኙነት የራሳቸውን ታሪክ ሲያወሩ ነበር። የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ሃዘናቸውን ሲገልጹ ከማንዴላ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት በመግለጽ ነበር። እኔ በምኖርበት አትላንታ ከተማ ዜናው ሲቀርብ፤ ኔልሰን ማንዴላ አትላንታ በመጡበት ወቅት፣ ከነአንድርው ያንግ ጋር ሆነው የማርቲን ሉተር ኪንግ ማዕከልን ስለመጎብኘታቸው ነበር – ዋናው ዜና። ሁሉም አገር ስለማንዴላ የየራሱ ትዝታ አለው። ኢትዮጵያውያንም ስለኔልሰን ማንዴላ የራሳችን ታሪክ እና ትዝታ አለን። እናም ማንዴላ የዛሬ 51 አመት ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ስለነበረው ጉዳይ በማውጋት ታሪካችንን እንጀምራለን።
Nelson Mandela, the revered statesman who emerged from prison after 27 years
በዳዊት ከበደ ወየሳ
Nelson Mandela and Col Tadesse
የኔልሰን ማንዴላ አሰልጣኝ ከነበሩት መካከል፣ ኮሎኔል ታደሰ አንዱ ነበሩ። ይህ ፎቶ ማንዴላ እና ኮ/ል ታደሰ (በሗላ ጄነራል) ለመታሰቢያ የተነሱት ነው
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር የነበሩት አቶ ከተማ ይፍሩ በ1962 ዓ.ም አራተኛው የፓን አፍሪካ ስብሰባ በኢትዮጵያ እንዲደረግ ጃንሆይን ፍቃድ ጠየቁ። ጃንሆይ በጉዳዩ ተስማሙና በፌብሩዋሪ 1962 ዓ.ም የአፍሪካ ታዋቂ የነፃነት ታጋዮች ወደ ኢትዮጵያ መጡ። ከእነዚህም መሃከል ሚስተር ኦሊቨር ታምቦ፣ ሚስተር ሮበርት ሙጋቤ፣ ሚስተር ኬኔት ካውንዳ እና ሚስተር ኔልሰን ማንዴላ ይገኙበታል። (በኋላ ላይ እነዚህ ወጣት ታጋዮች የየአገራቸው ፕሬዘዳንት ሆነዋል) ይህ ጉዞ በተለይ ለኔልሰን ማንዴላ በህይወታቸው ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጡት ነው።
ኔልሰን ማንዴላ እንደጻፉት…. ስለቼ ጉቬራ፣ ማ ኦ እና ፊደል ካስትሮ ስራዎች አነበብኩ። ለህዝባቸው ነጻነት ያደረጉትን ትግል ተመለከትኩ። ከዚህ ሁሉ በላይ ግን ኢትዮጵያውያን የደፈጣ ተዋጊዎች፤ ሙሶሊኒ ያስታጠቃቸውን የጣልያን ወታደሮች ድል ያደረጉበትን ታሪክ ለማወቅ በጣም ጓጓሁ። በመሃል ደግሞ ድርጅታችን ከሰላማዊ ትግል ጋር የትጥቅ ትግል ማድረጉ ስለታመነበት፤ እኔ ይህን ጉዳይ እንድመራ ትዕዛዝ ተሰጠኝ። ይህ የህቡዕ ጦርም ኡምኮሆንቶ ተብሎ እንዲጠራ ተወሰነ። ኡምኮሆንቶ ማለት፤ የጦር ጫፍ ማለት ሲሆን፤ አፍሪካውያን ለነጻነታቸው ሲዋጉ የቆዩት በጦር ስለሆነ ነው።
እናም ድሮ አቢስንያ ተብላ ወደምትጠራው የአሁኗ ኢትዮጵያ ለመሄድ ተዘጋጀሁ። ኢትዮጵያ ከክርስቶስ ደት በፊት የነበረች አገር ናት። እንዲያውም ከንጉሥ ሰለሞን እና የሳባ ንግስት የሚወለደው ቀዳማዊ ምኒልክ አገሪቱን መርቷል። ኢትዮጵያ ብዙ ጊዜ በአውሮፓውያን ብትወረርም፤ ሁልጊዜ ህዝቡ ጦርነት እያደረገ ያሸንፋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነጻነት እና ብሄራዊ ስሜት የተወለደባት አገር ናት። ከሌሎች የአፍሪካ አገሮች በተለየ መልኩ ወራሪዎችን ሲዋጉ ቆይተዋል። ዳግማዊ ምኒልክ ጣልያኖችን ድል አድርገው ቢመልሱም፤ ጣልያን ለሁለተኛ ግዜ አገሪቱን በወረረች ግዜ ግን ሁኔታዎች የከፉ ነበሩ።
ሙሶሊኒ የጣልያን ወታደሮች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው ጦርነት ሲያደርግ የ17 አመት ልጅ ነበርኩ። ድርጊቱ ፋሽስቶችን እስከመጨረሻው እንድጠላቸው ነበር ያደረገኝ። ምንም እንኳን ንጉሥ ኃይለ ስላሴ በጦርነቱ ምክንያት አገር ለቀው ቢሄዱም፣ ህዝቡ በአርበኝነት እየተዋጋ አገሪቱ በ1941 እንደገና ነጻነቷን አስመልሳለች። ኢትዮጵያ በኔ ውስጥ ሁልጊዜ ልዩ ስፍራ አላት። የአፍሪካዊነት የዘር ሃረግ ግንዴ የተተከለባት አገር ትመስለኛለች።
ከአክራ ወደ አዲስ አበባ ጉዞ ባደረግንበት ወቅት ስሜታዊ ያደረገኝ ጉዳይ ተፈጠረ። ከአክራ ወደ ካርቱም መጥተን፤ ከካርቱም ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ገባን። ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ስንገባ፤ ፓይለቱ ጥቁር መሆኑን አይቼ ደነገጥኩ። በህይወቴ ሙሉ ጥቁር ሰው አውሮፕላን ሲነዳ አይቼ ስለማላውቅ ተሸበርኩ። ‘ጥቁር ሰው እንዴት አውሮፕላን ሊነዳ ይችላል?’ እያልኩ ደጋግሜ ራሴን ጠየኩ። በኋላ ግን ሲገባኝ፤ የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ ስርአት አስተሳሰባችንን ጭምር ቀይሮታል። ሳናውቀው አፍሪካዊ ዝቅ ያለ እና አውሮፕላን ማብረር የሚችለው ነጭ ብቻ ነው’ የሚል ስሜት እንዲያድርብን ሆኗል ለካ። አውሮፕላኑ በሰማይ ላይ ማንዣበብ ሲጀምር ጭንቀቴን ትቼ ስለኢትዮጵያ መልክዐ-ምድር ማንበብ ጀመርኩ። በመንገዳችን ላይ የማስብ የነበረው… ኢትዮጵያውያኑ በነዚህ ተራሮች እና ጫካዎች ውስጥ ተደብቀው እንዴት ከጣልያን ጋር የደፈጣ ውጊያ ያደርጉ እንደነበር ነው።
ጥቂት አስፋልት መንገድ ያላት አዲስ አበባ፤ ከመኪኖች ይልቅ በግ እና ፍየል በየመንገዱ ሞልተው ይታያሉ። ቤተ መንግስቱ፣ እኛ ያረፍንበት ራስ ሆቴል፣ እንዲሁም ሌሎች ህንጻዎቿ ከጆሃንስበርግ የህንጻ ጥበብ ጋር ሲተያይ ብዙም አይማርክም። በዲሞክራሲም ቢሆን ኢትዮጵያ በምሳሌ ተርታ የምትሰለፍ አገር አይደለችም። ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሉም በንጉሱ ብቻ የምትመራ አገር ናት።
ከአፍሪክ ኮንፈረንስ መክፈቻ በፊት ወደ ትንሿ ከተማ፣ ደብረ ዘይት ሄደን ነበር። በከተማው አንድ አደባባይ አለ። እዚህ አደባባይ ላይ ከነበረው ድንጋይ ላይ እኔና ኦሊቨር ቁጭ ብለናል። ድንገት ግን ከርቀት የሙዚቃ ድምፅ ሰማን። ወደኛ ሲቀርብ የጥሩንባ እና የድራም ድምጽ እንዳለበት አወቅኩ። በኋላ ላይ እንዳየሁት ለካስ ወታደራዊ የሙዚቃ ባንድ ኖሯል። ከሙዚቃው ባንድ ቀጥሎ የብዙ ሰዎች እግር መሬቱን እየደቃ ሲመጣ ሰማሁ። በመቶዎች የሚቀጠሩ ጥቁር ወታደሮች ናቸው። ከፊት የሚመራቸው መኮንን የሚያብረቀርቅ ሰይፍ ይዟል። ወታደሮቹ የተወለወለ ጠመንጃቸውን እንደያዙ በልዩ ስሜት ይራመዳሉ። ፊት መሪያቸው ድንገት በአማርኛ አንድ ነገር ሲነግራቸው፤ ሁሉም እኩል አንድ ድምጽ አሰምተው፤ ፊታቸውን ወደ ንጉሥ ኃይለ ስላሴ አዙረው ሰላምታ በመስጠት አለፉ።
በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ በጥቁር ሰው የሚመሩ ጥቁር ወታደሮች ተመለከትኩ። የተሰበሰቡት ሰዎች የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ናቸው። ሁሉም ጥቁሮች ናቸው። ራስ የሚያዞር ስሜት ውስጥ ገባሁ። አንድ ቀን አገሬ ውስጥ እንዲህ አይነት ነጻነት እንደምመለከት ተስፋ ከማድረግ ሌላ የምለው ነገር የለም ነበር።
የኔልሰን ማንዴላን ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ ያሰናዱት የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አቶ ከተማ ይፍሩ ነበሩ። በወቅቱ በአፓርታይድ የዘረኝነት ቀንበር ስር የነበረችው ደቡብ አፍሪካ ጥቁር ዜጎችዋ ያለፈቃድ አገሪቱን ለቀው እንዳይወጡ የሚያዝ ህግ አውጥታ ነበር። ይህ ህግ ለኔልሰን ማንዴላ ጉዞ አስቸጋሪ  ሁኔታን ፈጠረ። በመሆኑም አቶ ከተማ ይፍሩ ለኔልሰን ማንዴላ የኢትዮጵያ ዲፕሎማት መሆናቸውን የሚገልፅ ፓስ ፖርት ካዘጋጁላቸው በኋላ ነበር፤ በፌብሩዋሪ 1962 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ የመጡት። ማንዴላ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት፤ ወቅት ወታደራዊ ስልጠና ለማድረግ ነበር ወደ ኢትዮጵያ የመጡት።
በወቅቱ ለኔልሰን ማንዴላ የተዘጋጀው ፓስፖርት ላይ ማንዴላ እንደጋዜጠኛ ሆነው፤ ስማቸው ዴቪድ ሞሳማይ ተብሎ ነበር የተጻፈው። ስሙን የተጠቀሙት ደቡብ አፍሪካ እያሉ አብሯቸው ከነበረው ጓደኛቸው ነው።
ወደ ኢትዮጵያ ስለነበረው ጉዞ እናውጋ። ኔልሰን ማንዴላ Long Walk To Freedom” በሚለው መፅሃፋቸው የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር አየር መንገድ ድረስ መጥተው እንዴት እንደተቀበሏቸው ገልፀዋል። እንዲህ በማለት ይቀጥላሉ ኔልሰን ማንዴላ…
ለንደን የነበሩትን ጓደኞቼን በወዳጅነት ስሜት ተሰናብቼ ወደ አዲስ አበባ- ኢትዮጵያ ተጓዝኩ። እስካሁን ባለው ህይወቴ ለማላውቀው ወታደራዊ ስልጠና ነው የምሄደው። የስድስት ወር ወታደራዊ ስልጠና ለማድረግ በያዝኩት ፕሮግራም መሰረት ነው ወደ ኢትዮጵያ የምጓዘው። አዲስ አበባ ስደርስ መጀመሪያ ተቀብለው ያነጋገሩኝ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ከተማ ይፍሩ ነበሩ። ሞቅ ያለ አቀባበል አደረጉልኝ። ከዚያም “ኮልፌ” ወደሚባለው አንድ የከተማው ክፍል ወሰዱኝ።
የኢትዮጵያ አድማ በታኝ ፖሊስ የሚሰለጥነው እዚህ ኮልፌ የሚባለው ሰፈር ነው። የባታሊዮኑ ዋና መስሪያ ቤት የሚገኘው ከዚህ ነው። አኔ ወታደራዊ የሳይንስ ጥበብ እንድማር የተመደብኩበትም ስፍራ እዚህ ነው። እስካሁን ባለኝ ልምድ ጀማሪ ቦክሰኛ ከመሆን ውጭ ስለጦር ሜዳ ፍልሚያ የረባ እውቀትም የለኝም። አሰልጣኜ መቶ አለቃ ወንድሙ በፍቃዱ ይባላል። በጣልያን ወረራ ግዜ የደፈጣ ተዋጊ የነበሩ ልምድ ያላቸው ወታደር ናቸው።
በአዲስ አበባ መውሰድ የጀመርነው የስልጠና ፕሮግራም ጥብቅ ነው። ከጠዋቱ 2፡00 ሰአት እስከ 7፡00 ሰዓት ድረስ ስልጠና ላይ እንቆያለን። ከዚያ የምሳ ሰዓት ነው። ከዚያ ከሰዓት ከ8፡00 እስከ 10፡00 ስልጠናው ይቀጥላል። ከ10፡00 ሰዓት በሁዋላ እስከምሽቱ ድረስ ስለ ወታደራዊ ሳይንስ የንድፈ ሃሳብ ገለጻ ይደረግልናል። ይህንን ስልጠና የሚያደርጉልን ኮሎኔል፤ የፖሊስ ረዳት ኮሚሽነር ናቸው። በንጉሱ ላይ የተደረገው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ እንዲከሽፍ ትልቅ አስተዋፅኦ አድርገዋል።
በስልጠናው የአውቶማቲክ መሳሪዎች እና የሽጉጥ አጠቃቀምን ተማርኩ።
መጀመሪያ ኮልፌ ከዚያም ከኮልፌ 50 ማይልስ የምትርቅ ቦታ ከወታደሮቹና ከንጉሱ የክብር ዘበኛ አባላት ጋር ሄጄ የኢላማ ተኩስ ተለማመድኩ። የሞርታር ተኩስና እንዲሁም የቦንንብ አሰራሮችን፤ ፈንጂዎችን የማክሸፍ ዘዴንም ተማርኩ። አሁን እያደር ወታደር እየሆንኩ ስሄድ ይታወቀኛል። እንደ ወታደር ማሰብ ለመድኩኝ። ወታደር መሆን እንደ ፖለቲከኛ ከማሰብ የሚለይበት የራሱ መንገድ አለው።
እዚህ ቦታ ላይ በጣም የወደድኩት ጠዋት ተነስተን የምናደርገው የማለዳ ጉዞ ነው። ጠመንጃ፣ ጥይትና ጥቂት ውሃ እንይዛለን። እናም በተሰጠህ ጊዜ ውስጥ ያንን ርቀት ተጉዘህ የታዘዝከውን ፈፅመህ መድረስ አለብህ። በዚህ ወታደራዊ ጉዞ የአገሪቱን ገጠራዊ ክፍሎች ለማየት እድሉን አገኘሁ። የመሬቱ አቀማመጥ በጣም ቆንጆ ነው። ጥቅጥቅ ያለ ደንና ከፍተኛ ቦታዎችን አየሁ። ገጠሩ በጣም ሁዋላ ቀር ነው። ሰዎች በእንጨት መቆፈሪያ ነው የሚያርሱት። ምግባቸውም ትንሽና በቀላሉ የሚዘጋጅ ነው። እቤት የሚጠመቅ ቢራ ወይም ጠላ አላቸው፤ ኑሯቸው እዚህ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ካሉ መከረኞች ጋር ተመሳሳይ ነው። መቼም ደሃ ሰዎች የትም ቢኖሩ ኑሯቸው አንድ አይነት ነው፤ ብዙም አይለያዩም።
በስልጠናዬ ወቅት ኮሎኔል ታደሰ ብዙ ጉዳዮችን እያነሱ ያስተዋውቁኛል። ስለ ደፈጣ ውጊያ፤ ሃይል እንዴት ማዋቀር እንደሚቻል አንድን ጦር እንዴት ማዘዝና መምራት እንደሚቻል፤ በጦር ውስጥ ወታደራዊ ስነ ስርአትን ለማስፈን ምን ማድረግ እንደሚገባ ያስተምሩኛል።
አንድ ምሽት እራት ላይ ለደቡብ አፍሪካ ትግል ምን አይነት ጦር እንደሚያስፈልገንና የሰራዊቱ ባህሪ ምን መሆን እንዳለበት አጫወቱኝ። “ይኸውልህ ማንዴላ… አንተ የምትመሰርተው ነፃ አውጪ ሃይል እንጂ መደበኛ ጦር አይደለም። የናንተን ጦር ሰዎች የምትቀርፅበት ስልት ከመደበኛው ጦር አሰራር የተለየ ነው። አንተ መመስረት ያለብህ ነፃ አውጪ ጦር ነው። በትግል ላይ ስትገባም የምትመራቸው ተከታዮችህ ፍፁም እርግጠኝነት እንዲሰማቸውና ሁሉም ሃሳብህን እንዲከታተሉ ማድረግ መቻል አለብህ። ይህ በመደበኛው ጦርም ውስጥ ያለ ነው። ከስራ በሁዋላ በእረፍት ሰዓትህ ማድረግ የሚገባህ ግን ከመደበኛው ደንብ ውጪ ይለያል። አንተና የመጨረሻው ተራ ተዋጊ እኩል መሆናችሁን የሚያሳይ አቀራረብ ሊኖርህ ይገባል። የሚበሉትን ትበላለህ፤ የሚጠጡትን ትጠጣለህ። ምግብህን ወደ ግል ክፍልህ መውሰድ የለብህም። እራስህን ገለል አታድርግ፤ እዚያው አብረሃቸው ሁን።” አሉኝ። የኮሎኔልን ሃሳብ ተረድቻለሁ። ሃሳቦቹ የሚደነቁና መልዕክት ያዘሉ ናቸው። እንደነዚህ ያሉ ቁም ነገሮችን በየፕሮግራሙ መሃል ይነግሩኝ ነበር።
ወደ አዲስ አበባ የመጣሁት ለስድስት ወር ስልጠና ነው። ስምንት ሳምንት እንደሆነኝ ግን ከድርጅቴ ‘የአፍሪካ ኮንግረስ’ አንድ የቴሌ ግራም መልዕክት ደረሰኝ። ባስቸኳይ ወደ ደቡብ አፍሪካ እንድመጣ የሚጠይቅ ነው። የዚያን ጊዜ የነፃነት ትግሉ መፋፋም ጀምሯል። እናም የግንባሩ አዘዥ እዚያው ቦታው ላይ መገኘት ስላለበት ነው የጠሩኝ። ኮሎኔል ታደሰ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ካርቱም የምሄድበትን መንገድ ቶሎ አዘጋጁልኝ። ስንሰነባበት አንድ ሽጉጥና ሁለት መቶ ጥይት ስጦታ አበረከቱልኝ። ስለ ስልጠናውም ሆነ ሰጡኝ ትምህርት ትልቅ አክብሮት እንዳለኝ ገለጽኩና ጉዞዬን ጀመርኩ። መሳሪያ ተሸክሞ ረዥም መንገድ መጓዝን ብለማመድም የተሰጠኝ መሳሪያ ከባድ ነው። ሁለት መቶ ጥይት ጀርባ ላይ መታጠቅ ህጻን ልጅ በጀርባ እንደማዘል ነው የሆነብኝ።
ኔልሰን ማንዴላ ደቡብ አፍሪካ ከገቡ በኋላ ሽጉጡንና ጥይቶቹን ለአንድ ለሚያምኑት የኤ.ኤን.ሲ አባል አሳዩት። የት እንደደበቁት ግን ማንም አያውቅም። (የሽጉጡን መጨረሻ በስተበኋላ ላይ እመለስበታለሁ)
ኦገስት 5 ቀን፣ 1962 ላይ… ኔልሰን ማንዴላ ወደ ደቡብ አፍሪካ ከገቡ ጥቂት ሳምንታት በኋላ ጥብቅ ፍተሻ ተደረገባቸው። ከጦር መሳሪያው በስተቀር የኢትዮጵያ ዲፕሎማት መሆናቸውን የሚገልጽና የአቶ ከተማ ይፍሩ ፊርማ ያለበት ፓስፖርት ተገኘባቸው። በኢትዮጵያ መቆየታቸውን የሚገልጽ የጃንሆይ ማስታወሻና የኢትዮጵያው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አቶ ከተማ ይፍሩ አነስተኛ ፎቶ ነበር። እነዚህን ጨምሮ 173 መረጃዎች በሪቮንያ የአፓርታይድ ችሎት ላይ ቀረበባቸው – 1963።
እነዚህና ሌሎች መረጃዎች በሪቮንያ ፍርድ ቤት ቀርቦ በኔልሰን ማንዴላ ላይ የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው፤ በዚሁ አመት በ1963 ሮቢን ደሴት ላይ ወደሚገኘው ወህኒ ተወረወሩ።
ከብዙ ውጣ ውረድና የ27 አመታት ትግል በኋላ ማንዴላ ከእስር ተፈቱ። እናም ከእስር በኋላ መጀመሪያ ከጎበኟቸው አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ነበረች። በፓስፖርታቸው ላይ ያሉት የመጀመሪያ ቪዛዎችም የሚያሳዩት ይህንኑ ነው። መጀመሪያ ከጎበኟቸው አገሮች መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ሆነች። በኋላ ላይ በመጽሃፋቸው ላይ ሲጽፉ፤ “ኢትዮጵያ በኔ ውስጥ ልዩ ስፍራ አላት። በፈረንሳይ፣ በእንግሊዝ እና በአሜሪካ ያደረኳቸው ጉብኝቶች ቢደመሩ እንኳን፤ በኢትዮጵያ ከነበረኝ ቆይታ አይበልጡም።” በማለት ለኢትዮጵያ ያላቸውን ልዩ ስሜት ገልጸዋል። (በነገርዎ ላይ የኔልሰን ማንዴላን የህይወት ታሪክ የሚገልጽ፤ ትልቅ ፊልም ተሰርቷል)
Nelson Mandela with Mengistu Haile Mariam
ኔልሰን ማንዴላ ከእስር ከተፈቱ በሗላ መጀመሪያ ኢትዮጵያን ሲጎበኙ በወቅቱ ፕ/ት መንግስቱ ሀይለማርያም አቀባበል ሲያድርጉላቸው
ኔልሰን ማንዴላ ከእስር ቤት ከወጡ በኋላ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ተመለሱ። በወቅቱ እነ ጄነራል ታደሰ ብሩ በህይወት አልነበሩም። ጊዜውም ተለውጧል። ቆየት ብሎ ኔልሰን ማንዴላ በህይወት ካገኟቸው ሰዎች መካከል አቶ ከተማ ይፍሩ አንዱ ነበሩ።
ከሰላሳ አመት በፊት  አብረው የተነሱት ፎቶ ማንዴላን ለእስር እንዳላበቃቸው፤ አሁን ግን በነፃነት እንደገና ተገናኝተው የመታሰቢያ ፎቶ ለመነሳት በቁ። (አቶ ከተማ ይፍሩም ከጥቂት አመታት በፊት አልፈዋል)
ከመሰናበታችን በፊት… የሽጉጡን ነገር እንጨዋወት። ኔልሰን ማንዴላ ከኢትዮጵያዊው በወቅቱ ኮ/ል ታደሰ ብሩ (በኋላ ጄነራል) የተቀበሉትን ሽጉጥ፣ 200 ጥይት እና የወታደር ዩኒፎርም ሊሊስሊፍ በተባለው እሳቸው ከመታሰራቸው በፊት ይኖሩበት በነበረው ቦታ ቀብረውት ኖሯል።
ማንዴላ ከተፈቱ በኋላ ይህንን ስፍራ ለመጎብኘት ሄዱ። ከዚያም ለብዙ አመታት በትግሉ ውስጥ የነበረውንና እዚህ ስፍራ የሚኖረውን ባልንጀራቸውን፤ “ሽጉጡስ?” ሲሉ ጠየቁት።
ሰውየው በማንዴላ ድንገተኛ ጥያቄ ተደናግጦ፤ “የምን ሽጉጥ?” አለ። ኣካባቢው የነበሩ ሰዎች በሙሉ በሁኔታው ግራ ተጋብተዋል። “ድሮ የምንጠቀምበት ኩሽና የታለ?” አሉ። ባልንጀራቸው አሁን ህንጻ ወደተሰራበት የድሮው ኩሽና ወሰዳቸው።
“ከዚህ ኩሽና ሃያ እርምጃ ላይ ነው፤ ሽጉጡንና ጥይቶቹን የቀበርኳቸው” አሉና ሃያ እርምጃ ለመራመድ ተዘጋጁ። ሆኖም ሃያ እርምጃ ከመሙላቱ በፊት አንድ ትልቅ ግንብ ከፊታቸው ተደቀነ። ከግዜ በኋላ መሬቱን ገዝቶ፣ ቤት ሰርቶ የሚኖረው የቦቢ ላንሃም የድንጋይ ግንብ ነው። ስለዚህ ማንዴላ ከመታሰራቸው በፊት የቀበሩት ሽጉጥ፤ አሁን በሌላ ሰው ግቢ ውስጥ እንደሚገኝ ይገመታል።
የቤቱ ባለቤት የሆነው ቦቢ ላንሃም ግቢው እንዲቆፈር ቢጠየቅ፤ “265ሺህ የእንግሊዝ ፓውንድ ከከፈላችሁኝ ብቻ ነው የምፈቅድላችሁ” አላቸው። ገና ለገና መኖር አለመኖሩ ላታወቀ ሽጉጥ ይህን ሁሉ አንከፍልም ብለው ነገሩን ተዉት።
ሆኖም ኔልሰን ማንዴላ ከመሞታቸው ሁለት አመታት በፊት “ሽጉጡ ተገኘ?” ብለው ጠይቀው፤ አለመገኘቱ ተነግሯቸው በወቅቱ አዝነው እንደነበር ተገልጿል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የአገሪቱ ቅርስ ጠባቂ ሙዚየም በጉዳዩ ውስጥ ራሱን በማስገባት የባለቤትነት ጥያቄ አቅርቦ የኔልሰን ማንዴላ ቤተሰቦች በመቃወማቸው ነገሩ አወዛጋቢ እንደሆነ ቆይቷል። ይህ ሽጉጥ ከመሬት ውስጥ ተቆፍሮ ሳይወጣ 2 ሚሊዮን ዶላር ተገምቶ ነበር። አሁን ከማንዴላ ሞት በኋላ ደግሞ ዋጋው በ እጥፍ ሊጨምር ይችላል። የሆኖ ሆኖ ግን ከቦቢ ግቢ በቀር የ-ሊሊስሊፍ ግቢ ተቆፍሮ እስካሁን ምንም አልተገኘም።
በመጨረሻም በዚህ እንሰናበት።
የኔልሰን ማንዴላ የልደት ቀን ሲመጣ፤ ተማሪዎችን ጨምሮ ህዝቡ በሙሉ ልደታቸውን ያከብራል። ለኔልሰን ማንዴላ ትልቁም ትንሹም “ማዲባ ሃላላ፣ እንወድሃለን አባባ” እያሉ ይዘምሩላቸዋል። እኛም “ማንዴላ እንኳን ተወለዱልን” ለማለት በልደት ቀናቸው አገር ምድሩ የሚያዜምላቸውን መዝሙር እንጋብዛቹህ።
Madiba, Halala
Happy birthday to you!
Happy birthday to you!
Happy birthday dear Tata!
We love you Tata
We love you Tata
Nelson Mandela. Ha hona
Ya tshwanang le wena (there is no like you)
Yeep yeep!
Hooray!
እኛም በዚሁ ስንሰናበት፤ አንድ ነገር ለማለት ወደድን። አሁን የውሸት ወይም ድራማዊ ለቅሶ ሳይሆን፤ የእውነት ሃዘን የምናይበት ጊዜ ይሆናል።
ነፍስ ይማርልን!

What Ethiopian leaders should learn from Mandela?


by Markos Abiy
THE theme running through Nelson Mandela’s life was “his unshakeable belief that one human being can change the course of history dramatically for the better”, writes David Blair in the Daily Telegraph.
THE theme running through Nelson Mandela’s life.
Blair writes, Mandela was “perhaps the only global hero” in an age where ubiquitous scepticism makes people unwilling to canonise public figures.
But Mandela was much more than a politician (although he was a skilled one). “In a bitterly divided South Africa,” writes Blair, “Mandela won the love of almost all his compatriots.”
Mandela’s life struggle, principles, values, politics, leadership and even passage were full of lessons.
The Ethiopian political leaders could learn from his exemplary life of commitment to the cause of liberating his people from racial subjugation; his life of service to South Africa and Africa in general.
Mandela did not exploit his idolisation and the love of his people to build a financial empire for himself, he didn’t privatise public enterprises and sell them to himself or his party,he didn’t make his country land locked with 80 million people. He didn’t apply divide and rule policy. He didn’t use his public life for private gains. he didn’t cheat elections and won 99.6%.
What made him remarkable and unique was that he was a politician who managed to remain untarnished by the messy compromises of power. Indeed, his image was even boosted by the manner in which he left office, stepping down voluntarily after only one rely.
Ethiopian leaders will not imbibe the Mandela example. They would rather follow Mohammed gaddafi and Hosni mubarak.
Ethiopian leaders should learn from Nielson Mandela to create distinctive values and never forget where they are from. They should also learn true forgiveness and love, never to be vindictive.
He was a ruler who believed in serving his people, in giving them and not taking from them. He left when the ovation was loudest. His love for his country, his honesty, integrity, fearlessness, sense of justice and fair play, are things to emulate. He was a complete leader. Indeed Mandela was a gift of God and greatest son of Africa.
He chose to be a man of the people. That has bought him the honour that wealth cannot acquire. The question to the Ethiopian leaders is ‘What would they want to be remembered for?’

Mandela’s colossus legacy versus Ethiopia he once loved


by Robele Ababya
Nelson Mandela glorified Ethiopia in these immortal words
The indisputable Great Statesman Nelson Mandela glorified Ethiopia in these immortal words in 1961 at a conference in Addis Ababa:  “Ethiopia has always held a special place in my own imagination and the prospect of visiting attracted me more strongly than a trip to France, England and America combined. I felt I would be visiting my own genesis, unearthing the roots of what made me an African. Meeting the emperor himself would be like shaking hands with history.”
He has now gone home to his final resting place leaving behind him enduring legacies. This Icon of Apartheid will at his new home find Menilik II of Ethiopia – the Icon Victor in the famous Battle of Adwa over Italy, the victory that has become a lasting beacon of hope for all black colonized people struggling for freedom and independence in Africa and in the Diaspora.
At their heavenly home, the beloved Mandela will narrate to Menilik the sad saga of apartheid policy in Ethiopia that been in effect for the last 23 years of dictatorship of TPLF leaders shunning the exemplary peace and reconciliation legacy he (Mandela) has left behind for all African countries to emulate. He will also tell the Monarch that: His Statue was saved from removal by popular anger; the tri-color – Green, Yellow and Red – Ethiopia Flag is disgraced; sellout or mismanagement of all vita national assets is rampant.
Glowing Tributes to Mandela
World leaders and dignitaries on our globe have affirmed Madeba’s enviable qualities as a Great Leader by crowning him with deeply moving accolades with gratitude, which he so richly deserves. Here below are few tributes gathered from Aljazeera and BBC media:-
  • President Obama said in a televised White House address held shortly after the death of the 95-year-old was announced, paid solemn tribute to Nelson Mandela, dubbing him “influential, courageous and profoundly good.” The President went on to say:“Through his fierce dignity and unbending will to sacrifice his own freedom for the freedom of others, he transformed South Africa and moved all of us”; “That he did it all with grace, good humor and ability to acknowledge his own imperfections only makes his achievements more remarkable”; “As long as I live I will do what I can to learn from him”. “I am one of the countless millions who drew inspiration from Nelson Mandela’s life,”
  • British Prime Minister David Cameron said: “one of the greatest lights has gone out in the world”; “Nelson Mandela was a hero of our time”.
  • Speaking on behalf of the United Nations, Secretary General Ban Ki-moon hailed Mandela as a “giant for justice” who had inspired freedom movements the world over; “Many around the world were influenced by his selfless struggle for human dignity, equality and freedom. He touched our lives in deeply personal ways.”
  • China’s President Xi Jinping said “Chinese people would always remember his extraordinary contribution to the development of bilateral relations and the cause of human progress”.
  • Australian Prime Minister Tony Abbott said Mandela was “a truly great man”; “Nelson Mandela was one of the great figures of Africa, arguably one of the great figures of the last century”; “As president, I watched in wonder as Nelson Mandela had the remarkable capacity to forgive his jailers”.
  • Bill Clinton said: “Today the world has lost one of its most important leaders and one of its finest human beings.”
  • Nigeria’s President Goodluck Jonathan dubbed Mandela “one of mankind’s greatest liberators”
  • Mexico’s Enrique Pena Nieto said: “Humanity has lost a tireless fighter for peace, freedom and equality.”
  • Brazilian President Dilma Rousseff said: “The example of this great leader will guide all those who fight for social justice and peace in the world.”
  • French Foreign Minister Laurent Fabius called Mandela “a charismatic giant”. “With Nelson Mandela, the father of South Africa has died, the driving force for freedom and for reconciliation,” Fabius said.
  • New Zealand Prime Minister John Key said: “Nelson Mandela was an inspirational leader and a remarkable man”. “For years he symbolized South Africa’s hope for a future free from apartheid”. “He was a force for change, not only in South Africa, but around the world.”
  • The UN Security Council interrupted a meeting on the tribunals for former Yugoslavia and Rwanda and stood for a minute in silent tribute to Mandela.
  • Microsoft founder Bill Gates, who has turned over his business acumen and part of his fortune to battling disease in Africa, said he and his wife had been personally inspired by the statesman. “Every time Melinda and I met Nelson Mandela, we left more inspired than ever. His grace and courage changed the world. This is a sad day”.
  • His fellow Nobel laureate, the Egyptian former head of the IAEA nuclear watchdog Mohamed ElBaradei, declared: “Let freedom reign. Humanity has lost its greatest son”; “In the years since his retirement as South Africa’s elected leader, Mandela became a magnet and an icon for celebrity activists fighting for social causes.”
  • Brazilian football legend Pele declared Mandela “was a hero to me. He was a friend and a companion in the popular fight and the fight for world peace.”
  • “Over the past 24 years Madiba taught us how to come together and to believe in ourselves and each other. He was a unifier from the moment he walked out of prison,” said Archbishop Desmond Tutu.
  • Citizens of RSA dubbed him Father of their Freedom, Founder of RSA, Moral Compass of their  nation.
Above all, Nelson Mandela is a uniquely unselfish Icon for his pursuit of peace and reconciliation with his enemies that had locked him up in prison for 27 years – 18 years of which in the isolated Robben Island in an inhuman condition. He shall forever be remembered for conceiving and successfully implementing the virtue of truth, peace and reconciliation and creating the Rainbow Nation, which we now know as the Republic of South Africa – by far the leading economic and military powerhouse on the African continent.
It would have been a grand welcome-home for Mandela to visit Ethiopia officially or otherwise in the last 22 years. But he did not. In my opinion the visit of apartheid Ethiopia by Great Statesman Mandela would have been contrary to his beliefs of a great unifier.
In closing I would like to ask why the TPLF regime has so far shunned the virtue of peace and reconciliation. The G7 has responded responsibly to the call of the TPLF regime for negotiations; why is the regime dragging its feet to respond? Is it in self-denial that popular uprising is inevitable otherwise? Why did the regime deny the request of the Blue Party to hold memorial services of the 100th anniversary of the death of Menilik II at a public gathering? Is it fear of massive turnout of the people?
The TPLF/EPRDF regime should immediately and unconditionally release all prisoners of conscience including Andualem Aragie, Eskinder Nega, Bekele Gerba, Reeyot Alemu, Leaders of the Ethiopian Muslims et al!
LONG LIVE ETHIOPIA!!! 
rababya@gmail.com