Saturday, February 1, 2014

በጎንደር የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራር እና የቅስቀሳ ቡድን አባላት በፖሊስ ታሰሩ


ጥር 22/2006 (BlueParty Ethiopia)
እስካሁን 14 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በጎንደር የታሰሩ ሲሆን ከታሰሩት ውስጥ አራት ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮች ይገኙበታል፣
1. ጌታነሀ ባልቻ (የድርጅት ጉዳዮች ሃላፊ)
2. ብርሃኑ ተ/ያሬድ (የሀዝብ ግንኙነት)
3. ዮናታል ተስፋዬ (የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ)
4. ይድነቃቸው ከበደ (የህግ አማካሪ)
ሁለት ሹፌሮች እና አንድ ፊልም አንሺም (Cameraman) ከታሳሪዎቹ ውስጥ ናቸው፣ በአሁኑ ስዓት ታሳሪዎቹ በወረዳ ሁለት ፖሊስ ጣብያ ሲገኙ ጌታነሀ ባልቻ (የድርጅት ጉዳዮች ሃላፊ) እና አግባው ሰጠኝ ወደ ጎንደር ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ተወስደዋል።
ጥር 25 2006 ዓ.ም. የኢትዮ ሱዳን ድንበር ማካለልን ህገወጥነት በተመለከተ በጎንደር መስቀል አደባባይ የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ ከአዲስ አበባ የተጓዘው የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ ሉኡካን ቡድን በዛሬው እለት በጎንደር ከተማ በቅስቀሳ ላይ እንዳሉ ከፍተኛ እንግልት እየደረሰባቸው ሲሆን ጎንደር የገባው ቡድን በጠቅላላ በእስር ላይ ይገኛል፡፡ የቅስቀሳው አባላት በጎንደር ከተማ እና በተለያዩ ቦታዎች ቅስቀሳውን እንደጀመሩ የፓሊስ አባላት ፈቃድ ስለሌላችሁ መቀስቀስ አትችሉም ያሏቸው ሲሆን አባላቱም በህጉ መሰረት ማሳወቅ እንጂ ማስፈቀድ የሚጠበቅብን ስላልሆነ ለሚመለከተው አካል ያሳወቅን በመሆናችን ህጋዊዎች ነን በማለታቸው ፓሊስ በማዋከብና በመደብደብ ጎንደር ከተማ በሚገኘው ሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ በመውሰድ በአሁኑ ሰአት ከፍተኛ መጉላላትና እንግልት እያደረሱባቸው ይገኛል፡፡ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችም ፖሊሶቹን ምን አደረጓችሁ በማለት እና ይህ ጉዳይ የኛም ጉዳይ ነው በማለት አባላቱን ከፖሊስ ለማስለቀቅ የተቻላቸውን ያደረጉ ሲሆን ፖሊስም ሐይል በመጨመር ህዝቡን በዱላ በማባረር የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራር እና የቅስቀሳ ቡድኑን እንዲሁም የጎንደር የፓርቲው መዋቅር አባላትን ጨምሮ አስረዋቸዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የጎንደር ነዋሪ ህዝብ የፖሊስ ጣቢያውን በመክበብ የታሰሩት እንዲፈቱ እየጠየቀ ሲሆን ሰልፉ በተያዘለት ቀን እንዲደረግ ለማድረግ ሌላኛው የሉኡካን ቡድን ከአዲስ አበባ በዛሬው እለት መንቀሳቀሱ ታውቆአል፡፡
A protest call in Gonder, Ethiopia

ማንነት (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም )


መስፍን ወልደ ማርያም
ኅዳር 21/2006
በ1996 ዓ.ም. የክህደት ቁልቁለት በሚል ጽሑፌ ውስጥ ‹‹ማንነት ምንድን ነው፤ በሚል ንዑስ ርእስ ስር ከገጽ 98 ጀምሮ በተቻለኝ መጠን አፍታትቻለሁ፤ የሪፖርተር ጋዜጠኛ ይህንን ለማንበብ ጊዜ አላገኘም፤ ወይም የተገለጠለት ዱሽ ቅንጫቢ በቅቶት ይሆናል፤ የምጠቅሰውም ለሱ ሳይሆን ለሌሎች ነው፡፡Prof. Mesfin Woldemariam : is an Ethiopian Human Rights activist and philosopher
በቅርቡ በፌስቡክ ላይ አንድ አውቀቱ ይሁን ጤንነቱ፣ ወይም ኪሱ የተቃወሰበት ሰው በትግርኛ ስለማንነት ጽፎ ነበር፤ ከዚህ በፊትም ጽፎ አስተሳሰቡ ሁሌም የተወላገደ በመሆኑ አልፌው ነበር፤ አሁን ደግሞ ሲጽፍና በአንዳንድ የሱ ቢጤዎች አበጀህ! አበጀህ! ሲባል ሳይ አደገኛነቱን ተገነዘብሁ፤ አንዱን ጎባጣ ሀሳብ ቶሎ ካላስተካከሉት ብዙ ጎባጦችን ያፈራል፤ የተጣራና ቀና የሆነ ሀሳብን ለመግለጽ በጣም ያስቸግራል፤ ማሰብ መጨነቅን፣ ማበጠርን፣ ማጣራትን ይጠይቃል፤ አፍ እንዳመጣ መልቀቅ ቀላል ነው፤ በተለይ የሚዳኝ ከሌለ!
በመጀመሪያ ሀሳብን ለመግለጽ የተመረጠው ቋንቋ ጠበብ ያለና የተፈለጉ አድናቂዎች ዘንድ ለመድረስ ብቻ ከተፈለገ ሀሳቡም እንደቋንቋው ለተወሰኑ ሰዎች የተመጠነ ይሆናል፤ በዚህ ዓይነት የቀረበው ቅንጣቢ ሀሳብ በሌላ ቋንቋ ሊተረጎም አይቻልም፤ ደንቆሮነትን ማጋለጥ ይሆናል፤ ለምሳሌ በትግርኛ ‹‹ኢትዮጵያዊ ዝበሃል መንነት የለን፤›› የሚለውን ‹‹ኢትዮጵያዊ የሚባል ማንነት የለም፤›› በማለት፣ በእንግሊዝኛ ደግሞ ‹‹There is no identity called Ethiopian.›› ተብሎ ሊተረጎም ነው፤ እንግዲህ ይህ አወቀች፤ አወቀች ሲሏት መጽሐፉን አጠበች እንደተባለችው ሴትዮ፣ ወይም ደግሞ አላዋቂ ሳሚ እንትን ይለቀልቃል! የሚባል ነው፤ ‹‹ኢትዮጵያዊ ዝበሃል መንነት የለን፤›› ብሎ በትግርኛ የጻፈው ሰው የአለማወቁ አዘቅት ዓለምን በሙሉ የሚያናጋ መሆኑን አልተገነዘበም፤ (አሜሪካን፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ኢጣልያን … የሚባል ማንነት የለም ሊለን ነው፤) የመንደር ማንነትን በሁለት እጆቹ ይዞ፣ አእምሮውን በመንደር ማንነት ጨቅጭቆ በየፓስፖርቱ ላይ የማንነት መግለጫ ተብሎ የተሰየመውንና በዓለም አቀፍ ደረጃ የታወቀውን ማንነት ካደው፡፡
በፍጹም ያልገባውን የፈረንሳዩን ፈላስፋ፣ የሩሶን ሀሳብ አበለሻሽቶ ከቆሻሻ መጣያ ውስጥ ያገኘው ቡትቶ ሊያደርገው ይከጅላል! ከጥራዝ-ነጠቅም አጉል ጥራዝ-ነጠቅ! ትግራይን የመገንጠል ዓላማ ያለው ሰው በእውነትና በግልጽ ዓላማውን ቢያራምድ በበኩሌ አልደግፈውም እንጂ አልቃወምም፤ መብቱ ነው፤ ነገር ግን በሰንካላ አስተሳሰብና በተንኮል ወጣቶችን ለመመረዝ የሚፈልገውን ሰው አጥብቄ እቃወማለሁ፤ ትግራይን እንደኤርትራ ካስገነጠለ በኋላ እንደኤርትራ ለትግራይም የኢትዮጵያዊነት ማንነትንን ማገድ ይቻላል፤ ከዚያ በፊት ግን ተንኮል ይቅር፡፡
ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት የሚደረገው ሙከራ አዲስ ኤደለም፤ ኢጣልያኖች በሰፊው ዘርተውት የሄዱት ጉዳይ ስለሆነ የአባቶቻቸውን ውርስ የሚከተሉ ዛሬም ይኖራሉ፤ ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት ብዙ ገንዘብና ሌላም የሚከፍሉ ብዙ የተለያዩ ድርጅቶች መኖራቸው የታወቀ ነው፤ ዱሮ የኢጣልያ ወኪሎች ተጠቅመውበታል፤ ዛሬ ደግሞ ሌሎችም ተጨምረው ያንኑ ተልእኮ የሚያራምዱ አሉ፤ በየዋህነት እንደበፊቱ እንዳናስተናግዳቸው እንጠንቀቅ!

ልፋ ያለው በሕልሙ ዳውላ ይሸከማል! ጠርናፊና ተጠርናፊ (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም )


ጥር 2006
ሰሞኑን እንደአዲስ ሆኖ የሚወራው ስለጥርነፋ ነው፤ ጥርነፋ ከዲያብሎስ ፋብሪካ የወጣ የክፋትና የጭቆና መሣሪያ ነው፤ ሰዎችን በመጨቆንና በማሰቃየት፣ ምቾትና እንቅልፍ በማሳጣት፣ ፍርሃትንና ስጋትን በማሰራጨት ሕዝብን ለጥ-ጸጥ አድርጎ ለመግዛት የሚፈልጉ ጠርናፊዎች፣ አምባ-ገነኖች፣ ጨቋኞች፣ አፋኞች፣ ዘራፊዎች፣ ወሮበሎች፣ ምድራዊም ሆነ ሰማያዊ ሕግ የማይገዛቸው፣ አምላካቸው አድርገው የሚያገለግሏቸው ሎሌዎችን በሆዳቸው ገዝተው የሚያሰልፉ ናቸው፤ እንኳን የገጠር ልጆችና አኛም የአዲስ አበባዎቹ መሰንከል ምን እንደሆነ እናውቃለን፤ እንስሳትን (በቅሎዎችንና አህዮችን፣ አንዳንዴ በገግና ፍየልም) የፊት እግር ከኋላ እግር ጋር በአጭር ገመድ እያሰሩ እንደልባቸው እንዳይንቀሳቀሱ ማድረግ ነው፤ ሀብት በመሆናቸው ቢጠፉ ባለቤቶቹ ይጎዳሉ፤ ስለዚህ በየአካባቢያቸው ያለውን እየጋጡ ችለው እንዲኖሩ ለማድረግ ቀላሉ ዘዴ መሰንከል ነው፡፡Prof. Mesfin Woldemariam : is an Ethiopian Human Rights activist and philosopher
ለሰውም ቢሆን ዓላማውም ዘዴውም አንድ ነው፤ ልዩነቱ የሰው ልጅ እንቅስቃሴው አካላዊ ብቻ ሳይሆን አእምሮም መንፈስም ስላለው መሰንከሉ አካላዊ ብቻ አይሆንም፤ እንዳያስብ አእምሮውን ማፈን ግዴታ ይሆናል፤ ለአምባ ገነኖች ችግር የሚመጣው የሰዎች አእምሮ ሲያስብ ነው፤ ያሰበውንም መናገርና መጻፍ ሲጀምር ነው፤ ‹‹መጥፎ ሀሰብ››፣ ማለትም ለጨቋኞቹ የማይበጅ ጥሩ ሀሳብ በንግግር፣ በጽሑፍ፣ በራድዮና በቴሌቪዥን ቢተላላፍና ብዙ ሰዎች ቢሰሙት አገር ይረበሻል፤ ሰው ሁሉ ሽብርተኛ ይሆናል፤ አገዛዙ ሕዝቡን ለመሰንከል ብዙ ዘዴዎች አሉት፤ በስም ማጥፋት እንዳልከሰስ ዘዴዎቹን አልናገርም፤ ነገር ግነ ክፉ እንቅልፍ ይዞት የሄደ ካልሆነ በቀር የማያውቃቸው የለም፤ የማያውቅ ካለ በየቤቱ እየመጡ ይተዋወቁታል፡፡
ወያኔ የትግራይን ሕዝብ አንድ ለአሥር ጠርንፎ ከሃያ ዓመታት በኋላ ውሉ ጠፋበትና ጥርነፋው ላላ! የቂል ነገር ለትግራይ ያልተሳካውን ጥርነፋ በቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይም ለመዘርጋት አቅዷል ይባላል፤ የወያኔ መሪዎች በአዲስ አበባ ቤቶችን አፍርሰው መንገድ ከሠሩ በኋላ ባቡር ትዝ ሲላቸው መንገዱን አፍርሰው ሀዲድ ለመሥራት ይሞክራሉ፤ ጥርነፋ በትግራይ እንዳልሠራ እያዩ በቀሩት ክልሎች ያሉትን ሰዎች ለመጠርነፍ ይፈልጋሉ፤ ጭንቅላተቸው ውስጥ ያለው ምንድን ነው ያሰኛል፤ እንኳን እንዲህ መክሸፉ በተግባር እየታየ ይቅርና ማሰብ ለሚችል በሀሳብም ደረጃ የከሸፈ ነገር ነው፤ እንስሳትን መሰንከል ቀላል ነው፤ ጉልበትን በበለጠ ጉልበት ማሸነፍ ነው፤ መናገርን መሰንከል ግን አይቻልም፤ ምላሱ ቢቆረጥበትም ሰው ሌላ መንገድ ይፈልጋል፤ በደርግ ዘመን ከኤንሪኮ በር ላይ የማይጠፋ ወፍራም ድሪቶ የሚለብስ ዲዳ ሰው ነበር፤ አንዳንድ ቀን ያየውን ‹‹ሲያወራ›› አንዳንዶች ያስይዘናል በማለት ይሸሹት ነበር፤ ያያቸው ወታደሮች መሆናቸውን በራሱ ላይ መለዮ በእጁ ያሳይና ሹመታቸውን ደግሞ በትከሻው ወይም በክንዱ ላይ እያመለከተ ሰዎችን ጨረሷቸው ለማለት በእጁ አፉን ጥርግ ያደርጋል፤ እኛ እንደሰማነው ወታደሮቹም እየገባቸው በየጊዜው ይደበድቡት ነበር፡፡
ማሰብን መሰንከል ደግሞ ከመናገርን ወይም መጻፍን ከመሰንከል የበለጠ አስቸጋሪ ነው፤ ለኢጣልያ የገበረው ባንዳ ሁሉንም አየነው፤ አማኑኤል ደግ ነው፤ እያለ የኢጣልያኑን ቄሣር አሞገሰና በጊዜው በላበት፤ በኋላ የአጼ ኃይለ ሥላሴ አገዛዝ ሲመለስና ሲቋቋም ባንዳው ተገልብጦ ኢየሱስ ክርስቶስን ማለቴ ነው አለ! ሰምና ወርቅ የሚባለው የተፈጠረው ሀሳብን የመግለጽ መሰንከልን ለማክሸፍ ነው፤ ማሰብን መሰንከል እስካልተቻለ ድረስ ሀሳብን መግለጽን መሰንከል አይቻልም፡፡
የሰንካዮችን ጭንቅላት አልፎ ሊሄድ የማይችል አንድ ታሪክ ደጋግሞ ያረጋገጠው ነገር አለ፤ ልፋ ያለው ዳውላ ይሸከማል፤ እንደሚባለው ጨቋኞችና አፋኞች እንደእንስሳ ለሆዳቸው ብቻ የሚገዙ ታማኝ አገልጋዮችን እየመለመሉ ዙሪያቸውን ያጥራሉ፤ ነገር ግን የሆዳሞቹ አገልጋዮች በሀሳብ ወረርሺኝ ሲመታና ሲነቃ አፋኞች ማሰብን ለመሰንከል ባለመቻላቸው የራሳቸው ታማኝ አገልጋዮች ይገለብጧቸዋል፤ ይህ የታሪክ እውነት ቢገባቸው ማሰብን መሰንከል መሞከሩ ቀርቶ ሀሳብን መግለጽንም ለመሰንከል አይሞክሩም ነበር፤ ምክንያቱም ማሰብ በሚቻልበትና ሀሳብን በነጻነት መግለጽ በሚቻልበት አገር ሀሳብ አይፈነዳም፤ ሀሳብ እንደሚፈነዳ፣ ከፈነዳም በኋላ እንደወረርሺኝ መንደር ሳይመርጥ፣ ጎሣ ሳይመርጥ፣ የቋንቋና የሃይማኖት ልዩነት ሳያግደው፣ ሀሳብ ብቻ ሊያግደው የሚፈልገውን ኃይል ሁሉ በዘዴ እያሽመደመደ ይንቀለቀላል፤ ይስፋፋል፡፡
አብርሃም ሊንከን አለ እንደሚባለው ‹ጥቂት ሰዎችን ሁልጊዜ ማታለል ይቻላል፤ ሁሉንም ሰው ለጥቂት ጊዜ ማታለል ያቻላል፤ ነገር ግን ሁሉንም ሰው ሁልጊዜ ማታለል አይቻልም፤› ለጥቂት ጊዜ የታለሉት ማታለልን ይማሩና ያታልላሉ! የተኙ መስለው ያሸልባሉ፤ የሚያለብሱ መስለው ያራቁታሉ፤ የሚያከብሩ መስለው ያዋርዳሉ፡፡
በመጨረሻም ተጠርናፊዎች ጠርናፊዎች ይሆኑና መክሸፍ ይቀጥላል! ጠርናፊም እስኪጠረነፍ ሌላ ነገር አላስተማረም፤ ተጠርናፊም ራሱን ከጥርነፋ እስኪያወጣ የተማረው ሌላ ነገር የለም፤ ማስረጃ ከተፈለገ ተቃዋሚ በሚባሉት ቡድኖች ውስጥ ሞልቶአል!!
መጨረሻም በኢጣልያ የአገዛዝ ዘመን አምስት ለአንድ ጥርነፋ ማለት አንድ ኢጣልያዊ ለአምስት አበሻ ማለት ይሆንና አንድ ጠርናፊና አምስት ተጠርናፊዎች በቋንቋና በባህል የማይግባቡ፣ በታሪክም ሆነ በማኅበረሰብ ኑሮ ዝምድና የሌላቸው፣ የወደፊቱም ሕይወታቸው በተረጋገጠ የበላይነትና የበታችነት ደረጃ የተወሰነ ስለሚሆን ጥርነፋው ትርጉም ያለው ሊመስል ይችላል፤ አምስት አበሻ ለአንድ አበሻ መጠርነፍ ግን በጠርናፊም ሆነ በተጠርናፊ በኩል ብርቱ የማሰብ ችግር (ከመንግሥተ ሰማያትም ቢሆን አመጣሃለሁ! ያለው ሰውዬ ዓይነት) ከሌለ በቀር ከንቱ ነው፤ በቀላሉ አንድ ለአምስት በማድረግ ዓላማውን መገልበጥ ይቻላል! አንድና አምስት ስድስት ነው፤ እንዲሁም አምስትና አንድ ስድስት ነው፤ ሁለትና አራት ስድስት ነው፤ ሦስትና ሦስትም ስድስት ነው፤ በነዚህ ቁጥሮች ውስጥ ሰው የምንለው ማንን ነው? ከብት የምንለው ማንን ነው? ሁሉም ሰዎች ከሆኑ ጠርናፊና ተጠርናፊ አይኖርም፡፡

ይድረስ ለዶክተር ታደሰ ብሩ – ባሉበት! (ነፃነት ዘለቀ፣ ከአዲስ አበባ)


ነፃነት ዘለቀ (ከአዲስ አበባ)
ከምቸገርባቸው ነገሮች አንዱ ለምጽፋቸው መጣጥፎች ርዕስ ማውጣት ነው፡፡ አንዳንዴ ርዕሴና በጽሑፌ ውስጥ የማነሳው ጉዳይ አልገናኝ ይሉብኛል – ልክ እንደአሁኑ፡፡ ዛሬና አሁን ለዶክተር ታደሰ ብሩ የምለው አንድም ነገር የለኝም፡፡ ነገር ግን እሱ አሁን በትምህርት ብልጭታ የኢሳት ቆንጅዬ ፕሮግራሙ ላይ ባነሳው የእስታስቲክስ ጉዳይ  እኔም አንድ ቀን እተነፍስበታለሁ ብዬ እዝት ስለነበር ያን ስላስታወሰኝ ርዕሴን ለሱ መታሰቢያ አደረግኋት፡፡ ደርባባው ታዱ የሥራ-ፈት ኤፍኤሞቻችንን ቋንቋ ልጠቀምና “እወድሃለሁ፤አከብርሃለሁ” – ባለህበት ይመችህ፡፡(ኤፍ ኤሞችን የማልወዳቸው አዘናጊ ስለሆኑ ነው፤ በተለይ ወጣቱን በእግር ኳስ ጨዋታ ሱስ እያሰከሩ፣ በአይሬ የጫት ዙርባ እያመረቀኑ፣ በፆታዊ ወሬ ምድረ ሴሰኛን እያነሆለሉ፣ በትርኪ ምርኪ ወሬ ማኅበረሰቡን እያጃጃሉ ወያኔያዊ ተልእኮኣቸውን በመወጣት ላይ ስለሚገኙ ነው፡፡ በተለይ ያቺ ሙግድ አፍማ … ቆይ ብቻ፣ ይንጋማ! ልክ ልኳን ያልነገርኳት እንደሁ ቁጭ ብዬ ተኝቻለሁ፡፡)Dr. Tadesse Birru ESAT journalist
በዚያ ላይ የወያኔ  የስለላ መረብ ጋማ ኢንተርናሽናል ከተባለ የእንግሊዝ የስለላ ቴክኖሎጂ አፍላቂ ባለዬ ድርጅት በገዛው አንድ የቴክኖሎጂ ውጤት የታዴ ኮምፒውተር በስለላ ቫይረስ መጠቃቱን በዚያው ኢሳት የዜና ዕወጃ ስለሰማሁ በእግረ መንገድ እግዜር ያጽናህ ለማለትም ነው፡፡ እነዚህ ወያኔዎች ግን በርግጥም ይሠሩትን አጥተዋል ማለት ነው – ሶልዲ አሰከራቸውና እሚሆኑትን አሳጣቸው፡፡ እንዴት ነው ነገሩ? እኛ እዚህ ኑሮ እንትኗን አፈንድዳብን እምንቀምሰውንና እምንልሰውን አጥተናል፤ እነሱ ከድሃው ሕዝብ በሚዘርፉት ገንዘብ ወንበራቸውን ለማስጠበቅ በውድ ዋጋ የስለላ ሶፍትዌሮችን ይገዛሉ – ዓለመኞች ናቸው፤ ግፈኞችም ጭምር! ይህን ዕኩይ ተግባራቸውን ያጋለጠው ፕራይቬሲ ምንትስ የተባለው ድርጅት እንደታዘበው እነዚህ ሰዎች ከድሃ ሕዝብ ጉሮሮ እየነጠቁ ይህን ውድ ዕቃ መግዛታቸው በርግጥም የገቡበት ክፉ አጣብቂኝ ቢኖር ነው ብሎ መጠርጠር ይቻላል፡፡ አባታቸው ሰይጣን ይሁናቸው ከማለት ውጪ ምን ይባላል?
(በነገራችን ላይ ለዕድገታችን ቀን ከሌሊት የሚለፉልን የአፍሪካ መሪዎች በዚህ ሣምንት አዲስ አበባ ላይ ለስብሰባ ተቀምጠዋል፡፡ መንገድ እየተዘጋጋ መንቀሳቀስ አቅቶናል፡፡ እነሱ ባይኖሩ ኖሮ – ባይሰበሰቡልንም ኖሮ ምን ይውጠን ነበር? ስብሰባውን እየተው ሸቀጥ የሚያጋብሱም ገጥመውኛል፤ ለሴትና ለሸቀጥ እንዲሁም በመብል በመጠጥ ከርሳቸውን እየሞሉ በጭቁኖች ገንዘብ እንደልባቸው ለመዝናናት የሚመጡት ይበልጣሉ – ሌላ ምን ቁም ነገር ሊሠሩ ዱሮውንስ፡፡ ፍሬፈርስኪ ለሆነ ስብሰባ ከአፍሪካ ድሆች በግድ የሚዘረፈው ገንዘብ አለመላው ሲከሰከስ ለሚታዘብ ጤናማ ወገን ያሳዝናል፡፡ አንድ የሰማሁት አስገራሚ ነገር አለ፤ እነዚህ የአፍሪካ አለኝታዎች ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ የአፍሪካ ኅብረት የተባለው ሥራ-ፈት ድርጅት ከግለሰቦችና ከድርጅቶች ለእንግዶቹ ማጓጓዣ መኪና ይከራያል፡፡ ያስገረመኝ ነገር ታዲያ ወያኔ የሠረገበት ይህ ድርጅት መኪና የሚከራየው ከወያኔዎች እንጂ ከሌላ አለመሆኑ ነው፡፡ ሾፌር የሚቀጠረውም ከወያኔው ዘውግ ብቻ እንደሆነ ውስጥ ዐዋቂ ሰሞኑን አረዳኝ፤ ለዚህች ለሣምንት ሥራም አድልዖ ይፈጸምባታል፡፡ ገቢው ከፍተኛ ስለሆነ ለማንም ከወያኔዎች ውጪ ለሆነ ግለሰብና ድርጅት አይሰጥም፡፡ እነሱው በነሰው ያለውን ሁሉ ይቀራመቱታል፡፡ አሁንስ የበይ ተመልካችነታችን ጠርዝ ለቀቀ፡፡ አይ፣ በጣም ተናደድኩ፡፡
እንደአንዳንዶች ሃሜት በርግጥም ይሉኝታ ከሰሜን ተጠራርጎ ወጥቷል ማለት ነው? ሰሜን ተወልጃለሁ፤ ሰሜን አድጌያለሁ፤ ሰሜን ኖሬያለሁ፤ ያኔ እንዲህ ያለ ይሉኝታቢስነት አላየሁም፡፡ አሁን ምን እንደመጣብን አላውቅም፤ ይህ ዘረኝነት ከምን እንደመነጨ መመርመር አለበት፡፡ ዐይን ያወጣ ዘረኝነት ነው እየታዬ ያለው፡፡ መሌ ገሞራው ስለህዳሴው ግድብ አንድ ወቅት እንዲህ አለ፡- “መሃንዲሶቹም እኛው፤ የገንዘብ ምንጮቹም እኛው፤ ምናምንቴዎቹም እኛው …”፡፡ እኔ ደግሞ እላለሁ፡-  ከሳሾቹ እነሱ፣ ዳኞቹ እነሱ፣ ፍርድ አስፈጻሚዎቹ እነሱ፤ ሻጮቹ እነሱ፣ ገዢዎቹ እነሱ፤ ባለሥልጣኖቹ እነሱ፣ በፍጥነትና በጥራት ተስተናጋጆቹ እነሱ፤ ጨረታ አውጪዎቹ እነሱ፣ ጨረታ ተወዳዳሪዎቹ እነሱ፣ ጨረታ አሸናፊዎቹ እነሱ፤ ኮንታራት ሰጪዎቹ እነሱ፣ ኮንትራት ተቀባዮቹ እነሱ፣ ኮንትራት አዳሾቹ እነሱ፤ ሕንጻ ተቋራጮቹ እነሱ፣ ሕንፃና የገበያ ማዕከላት ባለቤቶቹ እነሱ፣ ፋብሪካና ኢንዱስትሪ ገምቢዎቹ እነሱ፣ አየር ኃይሎቹ እነሱ፣ አየር ወለዶቹ እነሱ፣ አየር አብራሪዎቹ እነሱ፤ ሹዋሚዎች እነሱ፣ ተሸዋሚዎች እነሱ፣ ሰላዮቹ እነሱ፣ ተሰላዮቹ እኛ፤ ባለገንዘቦቹ እነሱ፣ ከግብርና ከቀረጥ ነፃ ሆነው የሚነግዱ እነሱ፣ ግምባርና ኪስ ቦታዎችን እያደኑ የሚይዙና የሚሸጡ የሚለውጡ እነሱ፣ ከሕግ በላይ ሆነው ማንም ላይ እሚያሽቃንጡ እነሱ፣ ገና ጡት ሳይጥሉ ቱጃር ሆነው በመቶ ሺዎች የሚገመት ብር በአንድ አዳር በየዳንኪራ ቤቱ ሲከሰክሱና በገንዘባችን ሲሸራሞጡ የሚያድሩ እነሱ፣ ጠግበው የሚዘፍኑና እንደኬንያ ማታቱ አደንቋሪ ሙዚቃ ሌሊት ከየቤታቸውና ከየመኪኖቻቸው  ሙዚቃ  እስከጣራ እየከፈቱ እንቅልፍ የሚነሱን እነሱ፣ … በችጋርና በችግር የምናንቋርር እኛ፣ የነሱን ዕዳ የምንከፍል እኛ፣ የምንታሠር የምንሰደድ እኛ፣ ከትምህርትና ከዕውቀት ዓለም ወጥተን ወደምድራዊ ሲዖል የተጣልን እኛ፣ የምናቀምሳቸውን ምናምኒት አጥተን ልጆቻችንን በርሀብ አለንጋ የምናስገርፍ እኛ፣ የትውልድ መርገምት የተሸከምን እኛ፣ … አፄ ቴዎድሮስ ያናደዱትን ካህናት ሰብስቦ “አንድሽ አንባቢ አንድሽ ተርጓሚ ሆነሽ መንግሥቴን ታውኪያለሽ…” ያለው ለካንስ ወዶ አልነበረም፡፡ ወያኔም የተለያዬ ካባ እየለበሰች አባት ዳኛ ልጅ ቀማኛም እየሆነች በኢትዮጵያ ላይ ታሪካዊ ሚናዋን መጫወቷን ቀጥላለች፡፡ ማን ተይ ብሏት? ማንንስ ፈርታ? (አንዱ አንዱን “ሚስትህ ወንድ ወለደች?” ብሎ ቢጠይቀው “ማንን ወንድ ብላ!” አለው አሉ፡፡) ወያኔ እያጠራቀመችው ያለችው ታሪካዊ ዕድፍ የሚያመጣባትን ዕዳ ግን ከፍላ የምትጨርሰው አይመስለኝም፡፡ የፈጣሪ የጽዳት ቀን ሲመጣ ምን ይውጣት ይሆን? ክበበው ገዳ፡- “ወዮልሽ አንቺ ኮሜዲ ሆይ…” ያለው በተወራራሽ ለወያኔም ይሠራል፡፡
(Literally, almost all privileges and benefits that Ethiopia has in her meager store, within or without her ever-shrinking border, willy-nilly belongs to TPLFites; Oh, shame on them! What a curse has descended upon these crooked creatures, and by extension, upon us, the oppressed majority? I wish I had a chance to examine the essence of the gray mud they are supposed to carry in their skull; I hope its content must be the same as that of the hyenas’ and pigs’ brain. They have fallen in love with MONEY and have gone crazy with this blind love. There is no JOKE; they do everything and anything to get MONEY. They have already evicted most of OTHERS from any ETHIOPIAN income generating means. They have convinced themselves that they are the sole owners or possessors of this ill-fated nation. Wonderful!  They have controlled virtually everything. There is a rumor that some of them have gone as far as owning their own minting machine which is why the circulation of Birr has become uncontrollably rampant especially in the hands of TPLFites; am not lying; what I am talking is the stark truth. Most of them are joining the camp of billionaires, while on the other hand, we the majority of OTHERS are obliged to join the camp of absolute poverty where there is nearly nothing for survival. The gap between the rich (in this specific case the TPLFites) and the poor is beyond explanation; there is no word (of any language on earth) to explain the discrepancy between THEM and US. Life in Ethiopia is skyrocketing in an alarming manner. The life style of THEIRS and OURS, i.e., the difference between THEM and US, is terribly shocking. Since the time this dichotomy, the ‘THEM’ and ‘US’ duality, has come onto the surface of this country, the ‘THEM’ group has boldly been committing all sorts of crimes and mischievous acts under the sun to impoverish the ‘US’ bloc.)
ታደሰ ብሩ በግሩም ሁኔታ እያቀረበው የነበረው አንዱ ሀገራዊ ችግር በእስታትስቲክስ ረገድ ሀገራችን ቀደም ካለ ጊዜ ጀምሮ የምታሳየውን “ዕድገት” ነው፡፡ እናንተዬ በርሀብና በጦርነት እንዲሁም አረመኔና አውሬ መንግሥታትን በማፍራትና በመሸከም ብቻ ሳይሆን በውሸትም አንደኛ ሳንሆን እንቀራለን? ምን ዓይነት ጉድ ነው? ይሄ ቤተ መንግሥት አንድ መቶና ሁለት መቶ ሰባቶችን ካልተጠበለ ከገባበት አባዜ በቀላሉ የሚፈወስ አይመስለኝም፡፡ አንድ የበቃ ባህታዊ ተፈልጎ ድርሣነ ሚካኤልን ይድገምበትማ እባካችሁ፡፡ አድምጥ ልንገርህ፡-
ደግሞ ለውሸት አለው ድካ፤
አምሳ ሰው ገዳይ ባንድ አማሪካ፡፡
ይህ ሥነ ቃል የቋንቋ መምህራን ስለ ግነት ሲያስተምሩ በረጂም ዘመን ትውፊት  ከደለበው ቃላዊ ሥነ ጽሑፋችን የሚመዙት አንዱ የንግግር ማጉሊያ ፈርጥ ወይም የጨዋታ ማድመቂያ ሰበዝ ነው፡፡ እውነት ነው – ውሸት ድካ ወይም ድንበር የለውም፡፡ ድንበሩ የተናጋሪው ኅሊና ብቻ ነው፡፡ ኅሊናውን መጠቀም የማይፈልግ ወገን፣ ኀሊናውን ለገንዘብ ወይም ለጥቅምና ለተለዬ ዓላማ የሸጠ ሰው እውነትን ሽምጥጥ አድርጎ ሲክድ ቅር አይለውም – የበሽታ ከሆነ እንዲያውም አንዳንዴ ምናልባትም ሁልጊዜ፣ መዋሸቱን ላያውቀው ይችላል – መረገም ነው፡፡ መዋሸትም ይባል ማጋነን በግለሰብ ደረጃ የጥፋት አድማሱና ክብደቱ ቀለል ስለሚል ምንም አይደለም ሊባል ይችላል፤ በሀገር ደረጃ ሲሆን ግን የሀገርን ኅልውና እስከመፈታተን የሚደርስ አደጋና ችግር ሊፈጥር ይችላል፤ በኛ ሀገር በተለይ በመንግሥት ደረጃ መረጃን ማንሻፈፍና በቤተ ሙከራ የተፈበረኩ ቁጥሮችን በሚዲያ መዝራት እንደሱስ ሳይጣባን አልቀረም፡፡ “እውነትን ተናግሮ እመሸበት ማደር” የ‹ፋራው ዘመን› ብሂልና የ‹ፋራዎች› ተረት ሆኗል፡፡
ውሸት ዓይነቱ ሊለያይ ቢችልም ሁሉም ውሸት እውነትን ለማፈን እስከዋለ ድረስ ማንም ይዋሸው ማን ያው ውሸት ነው፤ ጉዳቱም ከፍተኛ ነው፡፡ በግለሰብ ደረጃ እኔም አንተም እንዋሻለን – ቀላልም ከባድም ውሸት፡፡ “እኔ አልዋሽም” ብሎ የሚመፃደቅ ሰው ካለ እርሱ የመጨረሻው ውሸታም ነው – ግን ስንዋሽ መልክ ውሸታችን መልክ ያለው እንዲሆን መጣር የሚኖርብን ይመስለኛል – እንደወያኔና ሚዲያው የለዬለት ቀዳዳና ቱሪናፋ መሆን አይኖርብንም፡፡ በልማድ ለደግ ነገር – ለምሳሌ የተጣሉ ሰዎችን ለማስታረቅ – መዋሸት መልካም እንደሆነ ሲያንስ ለክፋት እንደማይሰጥ ሰዎች ሲናገሩ ይደመጣሉ፡፡
እዚህ ላይ በኩሸት፣ በውሸትና በእውነት መካከል ያለውን ልዩነት ልብ ማለት ሳያስፈልግ አይቀርም፡፡ ኩሸት ትንሽ እውነት ይዞ ምናልባትም ከባዶም ተነስቶ አንድን ሰው ማጋነን ወይም ማሽበልበል ነው – ለምሳሌ ባልዋለበት ጦር ሜዳ እንዳሸነፈ፣ ባልታጠቀው መሣሪያ ልክ እንደሶምሶን(ሳምሶን) መቶዎችን እንዳረገፈ፣ ወዘተ. በመኳሸት ፈሪን እንደጀግና፣ ንፉግን እንደቸር፣ ጨካኝን እንደሩህሩህ የሚያደርጉበት ሥነ ምግባራዊ ብልሽት ኩሸት እንደሚባል መምህራን ይናገራሉ፡፡ በመሠረቱ ውሸትም ኩሸትም በብዙ ነገር ይመሳሰላሉ፡፡ ጊዜ ለመቆጠብ ወደ ሀገራችን ይሉኝታቢስ እስታትስቲክስ እንለፍ፡፡
በመንጌ ጊዜ ነው፡፡ መንጌ ገሞራው በኢትዮጵያ ያለው እራሽ መሬት (arable land) ምን ያህል እንደሆነ ተጠንቶ ይቅረብልኝ ይልና ለግብርና ሚኒስቴር ትዕዛዝ ያስተላልፋል፡፡ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱም በተዋረድ ይህን ትዕዛዝ ለአሥራ አራቱም ጠቅላይ ግዛቶች ይልክና በቶሎ ተጠንቶ እንዲቀርብለት ያዛል፡፡ ከየክፍለ ሀገሩ “መረጃው” ቀረበ፡፡ ማዕከላዊ ፕላን ይባል በነበረው የስብሰባ ቦታ የሚኒስትሮች ጉባኤ ይዘጋጃል – ጥቁሩ ነብር አራስ ሲሆን እፊቱ የሚገኝን አሽትሬይና እስክርቢቶ በደመ ነፍስ እያነሣ ወዳናደደው ባለሥልጣን ይወረውር በነበረበት ዘመን መሆኑ ነው፡፡ የግብርና ሚኒስትሩ ተራው ይደርስና ሪፖርቱን በንባብ ማሰማት ይጀምራል፡፡ … ሰውዬው በሀገሪቱ ውስጥ ያለውን ለእርሻ ተስማሚ የሆነ የመሬት የቆዳ ስፋት ሲናገር ከሞላ ጎደል ሁሉም ተሰብሳቢ በሣቅ ይፈነዳል፡፡ ለካንስ በቀረበው እስታትስቲካዊ መረጃ መሠረት ከየጠቅላይ ግዛቱ የመጣውና አንድ ላይ የተደማመረው ሊታረስ የሚችለው የመሬት ስፋት ከጠቅላላው የሀገሪቱ የቆዳ ስፋት በልጦ ኖሯል! የኛ አስታስትስቲክስ እንግዲህ እንዲህ ነው፡፡ “የኛ ስታይል እንዲህ ነው!” የሚል የቀልድ ዘፈን አለ፡፡ ያስ ዱሮ ነው፡፡ አሁን ብሶ ቀጠለም አይደል? ይሄ ቆርጠህ ቀጥል የምንለው የውሸት ሀድራ ከመንግሥታችን እንዲወገድ በርትተን እንጸልይ ግዴላችሁም፡፡ ግን ግን እኮ ያልዘሩት አይበቅልምና እኛም እንደነሱው ቆርጠህ ቀጥል እንሆን እንዴ?
በቁሙ የሞተ የእስታቲስቲክስ መሥሪያ ቤት ያላት ኢትዮጵያ ብቻ ለመሆኗ ሌላ ባያውቅ እኞች እናውቃለን፡፡
በግንቦት 97 ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ በብዛት ወጥቶ መሪዎቹን የመረጠበት ወቅት ነበር – የምርጫውን ውጤት ያልተቀበለው ወያኔ ሥልጣኑን በኃይል እንደያዘ ቀጠለ እንጂ፡፡ ያኔ በወያኔ መንግሥት የቀረበው የመራጭ ብዛት 26 ሺህ አካባቢ ነው፡፡ ውሸት ነበር፡፡ ውሸት መሆኑን የምንረዳው የቀጣዩን የ2002ዓ.ም ምርጫ ተመዝጋቢ ቁጥር ስናይ ነው፡፡ በ2002 መረጃን መፈብረክ ተፈጥሮው የሆነው ወያኔ  ለምርጫ የተመዘገበውን የሕዝብ ቁጥር 32 ሺህ አደረሰውና አሣቀን – እኔ ጥርሴን ተወቅሬ ነበር በሣቅ የፈነዳሁት፡፡ ይታያችሁ – ሕዝብ በነቂስ በወጣበት ምርጫ የተመዝጋቢው ቁጥር አነሰ፡፡ ሕዝብ ተስፋ ቆርጦ እቤቱ በተሰበሰበበትና ከወያኔው ጋር በጥቅምና በዓላማ የተቆራኙ አንዳንድ ዜጎች ውር ውር ባሉበት የምዝገባ ወቅት ቁጥሩ ተነረተና 32 ሺህ ደረሰ፡፡ ምን ትሉታላችሁ? የእስታትስቲካዊ መረጃው ሲነፋ(ሲያብጥ) ወያኔን የሚጠቅም ከሆነ ነፊዎቹ አንድም የይሉኝታ አጥር ሳይገድባቸው ሰማይ ያደርሱታል፤ ትዝብት ግዛዕምዛ አያውቁም፡፡ ዋናው ዓላማቸው የላይኞቹን ማስደሰት ብቻ ነው፡፡ የእስታትስቲክሱ መረጃ መጫጫት መንግሥታቸውን የሚያስደስት ከሆነ ደግሞ ለምሳሌ “ከመቀሌ አዲስ አበባ ያለው ርቀት መቶ ሜትር ነው” ብለው በዓይነቱ ልዩ የሆነ መረጃ እስከመስጠት በሚደርስ ድፍረት አዲስ እስታትስቲክስ ከመፍጠር አይመለሱም – “ዋሽ ቢሉኝ እዋሻለሁ፤ ንፋስ በወጥመድ እይዛለሁ” ያለው ባላገር እንዴት ብልህ ነበር፡፡ አንዱ ወያኔን በውሸት ፈጠራ የሚስተካከል ልጅ ደግሞ አባቱን “አባዬ፣ እስኪ ውሸት አስተምረኝ” ብሎ ይጠይቀዋል አሉ፡፡ አባትም በእሺታ ይቀበለውና ማስተማሩን ሊጀምር “ልጄ፣ እዚያ ሰማይ ላይ በነጫጭ በሬዎች ሰዎች እህል ሲያበራዩ ይታዩሃል?” ይለዋል ወደሰማዩ አንጋጥጦና ሌባ ጣቱን ወደተባሉት ሰማይ ላይ እህል ወደሚወቁት ሰዎች ቀስሮ፡፡ ልጅም ቀበል ያደርግና “ውይ ውይ አባዬ …” ብሎ ይጮሃል – ዐይኖቹን በእጆቹ ከድኖ፡፡ አባት ይደነግጥና “ምን ሆንክ ልጄ ምን ነካህ” ይለዋል፡፡ የውሸት ሥልጠና ኮርስ ከመመዝገቡ ትምህርቱን የጀመረው ታዳጊ ወያኔ “ውይ አባዬ፣ የጭዱ ብናኝ ዐይኔ ውስጥ ገባ!” ይላል፡፡ አባትም “አሃ፣ አንተንማ ውሸት ማስተማር አልችልም፤ ከኔስ በልጠህ የለም እንዴ” ይለውና ኮርሱን ‹ድሮፕ› አድርጎ የኤግዘምሽን ቅጽ እንዲሞላ ይመክረዋል – እንዲህ እየተቀላለዱ ነው የወያኔን ዘመን ሸውዶ ማለፍ ወንድምዬ ፡፡ እባክህን በነካ እጄ አንድ የወያኔን ባሕርይ የሚያሳይ ሌላ ረቀቅ ቀልድ ልንገርህና ትንሽ ዘና በል፡፡ …
አንድ ጉልበተኛ ጨቡዴና አንድ የኔ ቢጤ ኮሣሣና ፈሪ የሆኑ ሁለት ጓደኛሞች ወደ አንድ ቦታ በመጓዝ ላይ እንዳሉ መንገዳቸው ላይ አንድ ጥቁር ነገር ቁጭ ብሎ ከሩቅ ያያሉ፡፡  ይሄኔ ጨቡዴው “አየኸው ያንን በግ?” ይለዋል – ለአቅመ ደካማ ጓደኛው፡፡ ፈሪ ጓደኛም  “የቱን በግ?” ብሎ ይጠይቀዋል፡፡ “እዛ ጋ ቁጭ ያለው ጥቁር በግ” ይለዋል እሱ ከሩቅ አይቶ ከነምንነቱ የለዬውን ጥቁር በግ ጓደኛው ከነአካቴው ምንም ነገር አለማየቱን ተገንዝቦ በመደነቅ፡፡ “እንዴ፣ አሞራውን ነው እምትለኝ?” ይለዋል፡፡ “የምን አሞራ አመጣኽብኝ! በግ ነው እንጂ” በማለት ጡንቻውን ጭምር እያሳዬ በኃይል ሊያሳምነው ይሞክራል፡፡ በዚህ መሀል ወዳጨቃጫቂው ነገር እየቀረቡ ሲሄዱ ያ በጉልበተኛው ጓደኛ ጥቁር በግ የተባለው ነገር ይበራል፡፡ ይሄኔ ደካማ ጓደኛ “ይሄው፣ በግ አይደለም – አሞራ ነው አላልኩህም? በረረልህ፡፡ ” ቢለው “በረረም አልበረረም በግ ነው ብዬሃለሁ በግ ነው!” ይልና ዐይኖቹን እያጉረጠረጠ ያስፈራራዋል፡፡ ደካማ ጓደኛ ምን ምርጫ አለው? “እሺ ይሁንልህ በግ ነው” አለውና ከጡጫው ተረፈ፡፡ እኛስ ምን ምርጫ አለን? ምርጫችን “ወያኔ ፍጹም ዴሞክራሲያዊ ነው፤ ዘላለማዊ ክብር ለሕዝብ ለተሳዋው ጠቅላይ ሚኒስትራችን፤ የኢሕአዴግ ዕድሜ ዘላለማዊ ይሁንልን፤ ወያኔ ከጠፋ ኢትዮጵያ ትበታተናለች፤ ወያኔ ከወረደ ልማታችን ይደናቀፋል፤ ወያኔ ከጠፋ ዘረኝነት ተመልሶ ኢትዮጵያን ድምጥማጧን ያጠፋዋል፤ ከኢሕአዴግ ጋር መጪው ዘመን ጨለማ ማለትም ብሩህ ነው፤ ቀኝ መንገደኛው መኢሶንና ማለቴ ሽብርተኛው ግንቦት ሰባትና ሰማያዊ ፓርቲ ለተፋጠነው ልማታችን ፀርና አሸባሪዎች ናቸው …” እያሉ መፈክር ማሰማት ነው፡፡
እነመንግሥቱ እነመለስ  እነሂትለር እነሙሶሎኒ እነኢዲያሚን እነሳዳም እነአላሳድ እነሁሉም እነዚህን በእናታቸው ማኅጸን ቢጨነግፉ የሚሻላቸው ሰብኣዊ ፍጡራንን የመሰሉ ሰዎች ሁሉ ባሕርያዊ ተፈጥሯቸው አንድ ነው፤ አንድኛቸው የሌላኛቸው ቅጂ ናቸው፡፡ አባ ጉልቤዎች በመሆናቸው የሚያስቡት በአንጎል ሳይን በጡንቻ ነው – ሁሉም አምባገነኖች ከፍ ሲል በተቀመጠው ምሳሌ እንዳየነው ጨቡዴ ናቸው፡፡
ወደእስታትስቲክሳችን እንመለስ፡፡ በ1997 ሚያዝያ 29 ቀን ለወያኔ ድጋፍ የወጣው ሰው ብዛት በወያኔ ሚዲያ ሲገለጽ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ነበር፡፡ በማግሥቱ ሚያዝያ 30 ለቅንጅት የወጣው ሠልፈኛ ግን በአሥር ሺዎች የሚገመት ነበር – አሁንም በወያኔ ሚዲያ፡፡ ይህን ምን እንለዋለን ? የሰዎች ተፈጥሮ አስቸጋሪ ነው፡፡ በተለይ የወያኔ በቁጥርና በመረጃ የመጫወት ልምድ እጅግ የሚያሣፍር የሚያስቅም ነው፡፡
የአዲስ አበባ ሕዝብ ቁጥር ማነስ ለወያኔ የሚጠቅም ሆኖ ከተገኘ 500 ሊሆን ይችላል፡፡ የገጠሩ ሕዝብ ብዛት ለወያኔ የሚጠቅም ሆኖ ከተገኘ ከሀገሪቱ ሕዝብ ቁጥር በእጅጉ በልጦ እስታትስቲካዊ መረጃው ሊለጠጥ ይችላል፡፡ ወያኔ አዲስ አበቤዎችን ስለማይወዳቸው ቁጥራቸውን ሁልጊዜ እንደቀነሰው ይኖራል፡፡ አሁን ድረስ የአዲስ አበባ ሕዝብ ቁጥር ከሁለት ሚሊዮን እምብዝም አይበልጥም – በወያኔ ግምት ወይም ቆጠራ፤ ወያኔ ሲዋሽ ትንሽም አፈር አይልም – ይገርመኛል፡፡ ሁለት ሚሊዮን ማለት እኮ የመርካቶ ሕዝብ ብቻውን ሊሆን ይችላል፡፡ አዲስ አበባ በኔ አነስተኛ ግምት ከስምንት ሚሊዮን ያነሰ ሕዝብ አይኖርባትም ባይ ነኝ፤ እምዬ አዲስ አበባ  በጣም ብዙ ሕዝብ ይኖርባታል፡፡ ነገር ግን የአዲስ አበባን ሕዝብ ምርጫ ዋጋ ለማሳጣትና ከሀገሪቱ አጠቃላይ የሕዝብ ቁጥር አንጻር አቅልሎ ለማሳየት ሲፈልጉ ለከት የሌለው እስታትስቲካዊ ውሸት ይዋሻሉ፡፡ እስታትስቲክስ ማለት ባጭሩ የመንግሥት የውሸት ፋብሪካ ማለት ነው ቢባል ትክክል ነው፤ ሠራተኞቹ ደሞዝ የሚከፈላቸው መንግሥትን የሚያስደስት ውሸት ለመጠፍጠፍ ነው፤ የሕዝብ አንጡራ ሀብት በብዙ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በከንቱ እየባከነ እንደሆነ መገመት አይከብድም፡፡ የአፍሪካ መንግሥታት በተለይም የኛዎቹ ካልዋሹ ሥልጣናቸው የሚረጋላቸው አይመስላቸውም፡፡ የወያኔን ሚዲያ ስትከፍቱ ውሸቱ በቲቪው መስኮት አልፎ ወደዬስሜት ሕዋሳታችሁ ይገባና ያጥወለውላኋል፤ ሊያስታውካችሁም ይደርሳል፡፡ ሌላው ቀርቶ ሰዓትም ይዋሻሉ፡፡ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ሆኖ እያለ እነሱ ሁለት ከአምስት ሊሉ ይችላሉ፡፡ ኢትሬድ ማለት እውነት እሚያቅረው ነጋ ጠባ እንደጣቃ የሚቀደድና የውሸት ቱሪናፋ የሚያሰራጭ የወያኔ ብስናት ነው፡፡ የወያኔ መሥሪያ ቤት ሁሉ በውሸት መረጃ የተጥለቀለቀ የተሳሳተና የተጋነነ እስታትስቲክሳዊ አሃዝ በመስጠት ታችኛው ላይኛውን ለማስደሰት አደግድጎ ያለበት ሁኔታ ነው የሚታየው – በነሱው አገላለጽ፡፡ ሰዎች በውሸት መረጃ እንዴት እንደሚደሰቱ አይገባኝም – “አለባብሰው ቢያርስ ባረም ይመለሱ” እየተባለ በሚተረትበት ሀገር ውስጥ ይህን ያህል በውሸት መለከፍ የሚያሳዝንም የሚቆጭም ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታ ነው፡፡ እውነቱን ልቦናቸው እያወቀው በመዋሸት የመደሰት ተፈጥሮ እንደምን እንደተጠናወታቸው ሲያስቡት ይጨንቃል – የመፍትሔው መራቅ ደግሞ ይበልጥ ያበሳጫል፡፡ ከዚህ ከውሸት ዓለም የምንወጣበት ጊዜ ናፈቀኝ፡፡ እዚህም ውሸት፣ እዚያም ውሸት፡፡ ትልቁም ውሸት ትንሹም ውሸት፡፡ የግሉም ውሸት የመንግሥቱም ውሸት፡፡ በተናጠል ውሸት – በቡድንም ውሸት፡፡ በንግዱ ውሸት በፖለቲካውም ውሸት፡፡ በሃይማኖቱም ውሸት በኢኮኖሚውም ውሸት፡፡ ውሸት – ግነት – ውሸት፤ ዕብለት – ቅጥፈት – ጉራ – ዕብሪት ፤ አቤት ያንት ያለህ!!

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት መተማ አካባቢ ጥቃት ፈፀመ


የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር የአገራችን ኢትዮጵያን ዳር ድንባር ለሱዳን ለማስረከብ ሽር ጉድ እያለ የሚገኘውን የወያኔን አገዛዝ ጸረ-አገርና ጸረ-ህዝብ እንቅስቃሴ በመቃወም በመተማ አካባቢ ልዩ ስሙ ዘባጭ ባህር በተባለ ቦታ ከወያኔው 24ኛ ክፍለ- ጦር ጋር በጥር 21- 2006 ዓ.ም ከቀኑ 6 ሠዓት ላይ ባደረገው ውጊያ 14(አስራ አራት) ገድሎ 12(አስራ ሁለት) አቁስሏል።Ethiopian freedom fighters
በመተማና አካባቢው በተደጋጋሚ በአርበኛው ጥቃት እየተፈፀመበት የሚገኘው የወያኔው ቅጥረኛ ሠራዊት ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው እየፈረጠጠ መሆኑ ሲታወቅ በደረሰበትም ጉዳት ማካካሻ ይሆነው ዘንድ ሰላማዊውን ነዋሪ በእናንተ ምሽግነት ነው እየተመታን ያለነው በሚል እንግልት እያደረሱበት መሆኑ ታውቋል።
በተያያዘ ዜና በጭልጋ ወረዳ ጫቁ የተባለ አካባቢ ነዋሪዎች ከብት፣በግና ፍየል በአካባቢው የወያኔ ታጣቂዎች እየታረደ እየተበላባቸው መሆኑ ታውቋል።
በዚሁ አካባቢና አጎራባች ወረዳዎች የወያኔው ተላላኪዎች ተደጋጋሚ ንብረትን የመዝረፍ ሂደት የተቆጣው ነዋሪ ለምንድን ነው ንብረታችንን የምትዘረፉት ምን አደረግናችሁ ብለው ሲጠይቁ እናንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ደጋፊዎች ፣መንገድ መሪዎች እንዲሁም ስንቅ አቀባዮች ናችሁ የሚል ምክንያት የሰጧቸው መሆኑ ታውቋል።
ሕዝቡም እኛ የአርበኛው አባልም ደጋፊም አይደለንም ከፈለጋችሁ እነሱን ተከታትላችሁ መዋጋት ትችላላችሁ እኛን ምን አድርጉ ነው የምትሉ? ሲሉ ምሬታቸውን ቢገልፁም እንግልቱ እንዳላበራ ዘጋቢያችን ካደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል።
ዘጋቢያችን አክሎ እንደገለፀው የወያኔው ተላላኪዎች በሕዝቡ ላይ እያደረሱ ያለው እንግልት ያስቆጣቸው ብዛት ያላቸው የአካባቢው አርሶ አደሮች የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኛች ግንባር ሠራዊትን እየተቀላቀሉ መሆኑን አስታውቋል።
በሌላ ዜና የአማራ ክልል ፀጥታ ዘርፍ ሃላፊ የሆነው ሙሉጌታ ወርቁ የተባለው ግለሰብ በክልላችን ቢሮዎች በሙሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰዎች ተሰግስገዋል በሚል ምክንያት ሰሞኑን በየወረዳው ፅ/ቤት የማፅዳት ዘመቻ በሚል ከፍተኛ ስብሰባ እያደረገ መሆኑ ታውቋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ተደጋጋሚ ጥቃት እያሰጋው የመጣው ሆድ አደሩ የአማራው ክልል ባልስልጣናት ሕዝቡን በተለያየ ምክንያት ማሰቃየቱ ሳያንሰው የራሱ ታማኝ የሆኑ ቅጥረኞቹ ላይ እምነት በማጣት የሚያደርገውም የጠፋበት መሆኑ ግልፅ እየሆነ መምጣቱን አመላካች እንደሆነ የዚሁ ችግር ሰለባ ልንሆን እንችላለን ያሉ ወገኖች ጠቁመዋል።
በይበልጥ አማራዉን በማይወክሉት የወያኔ አገልጋዮች እየተሰቃየው ያለው ሕዝቡ ሲሆን ፣ እነሱም ሕዝቡ ከጎናችው አለመኖሩን በመረዳታቸው የተፈጠረው ክፍተት በፈጠረባቸው ጭንቀት የመንግስት ሠራተኛውንም ሆነ ነጋዴውን ማመሱን እንደቀጠሉበት ለማወቅ ተችሏል።

በጎንደር ክ/ሃገር ሳንጃ ወረዳና አካባቢው ሕዝብን ሲያሰቃይ የነበረው የልዩ ሃይል አዛዥ ሻለቃ ቀለሙ ክብረት ተገደለ

ግለሰቡ የተገደለው በጥር 21-2006 ዓ.ም ከቀኑ 12 ሰዓት ላይ በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰርጎ ገቦች ማሰሮ ደንብ የተባለ ቦታ በጥይት ተደብድቦ ቆስሎ ወዲያውኑ ወደ ጎንደር ቸቸላ ሆስፒታል ቢወሰድም በማግስቱ ማለትም በጥር 22-2006 ዓ,ም ህይወቱ አልፏል።
ይህ ግለሰብ በወረዳው የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን የአርበኞች ደጋፊ ናችሁ በሚል ሲያሰቃይ የነበረ ሲሆን፣ ብዙ ንፁሃን ግለሰቦችን በድርጅቱ ደጋፊነት ስም እየፈረጀ እንደገደለ ፣ እንዳሰረና እንዲሰደዱ ሲያደርግ የነበረ መሆኑ ይታወቃል ። ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ግለሰቡ ከድርጊቱ ታቅቦ ሰላማዊ ኑሮውን እንዲኖር ካልሆነ ግን አስፈላጊው እርምጃ እንደሚወሰድበት የፅሁፍ መልዕክት የደረሰው ቢሆንም ሊታረም ባለመቻሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰርጎ ገቦች እርምጃ እንዲወስዱበት ተደርጓል።
በጎንደር አካባቢ ምንም አይነት ወታደራዊ እርምጃ በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት ሲወሰድ የአካባቢውን ሕዝብ ማንገላታቱ የተለመደ ቢሆንም ሻለቃ ቀለሙ ክብረት ከሞተበት ከትናንት ጀምሮ ግን በህዝቡ ከፍተኛ ስቃይ እያደረሰበትና ገዳዮቹን ታውቃላችሁ እናንተ ናችሁ እየደበቃችሁና ቀለብ እየሰፈራችሁ የምታስጨርሱን በሚል ብዙ ሰዎች እንደታሰሩ ታውቋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ወታደራዊ መምሪያ በበኩሉ ወደፊትም ቢሆን ወያኔና ተላላኪዎቹን ከዚህም በከፋ ሁኔታ አይቀጡ ቅጣት እንደሚቀጣ አስታውቆ ሕዝቡም ከመሬቱና ከንብረቱ እየተፈናቀለ መኖሩ ያበቃ ዘንድ ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት ጎን በመሰለፍ ይህን አፋኝ ስርዓት ለመገርሰስ የበኩሉን አስተዋፅዖ ማበርከት እንዳለበት ጥሪውን አስተላልፏል።
የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር

New Journalist Association Established in Ethiopia


by Betre Yacob
Ethiopian journalists have successfully established a new nation-wide non partisan and independent professional association, which is unique of its kind. The first general assembly meeting of the association was colourfully held yesterday on 30 January 2014 in Addis Ababa.Ethiopian journalists established non partisan and independent professional association
The new association, Ethiopian Journalists Forum (EJF), is intended to protect and promote Ethiopian journalists and media practitioners, and devoted to promoting the freedom of speech and press freedom.
Ethiopia is one of the lowest-ranking countries in the world with regards to press freedom, and is the highest jailor of journalists.
According to Amnesty International, only during 2011 and 2012, over 100 journalists and political activists were arrested and prosecuted on charges of terrorism and related offenses, for exercising their rights to freedom of expression.
The general assembly meeting of the association was held in the presence of the representatives of Ethiopian Charities and Societies Agency, which has the mandate to give legal certificate to new associations and charity organizations.
Besides the founding members, the meeting was attended by representatives from the US and UK embassies in Addis Ababa.
The half day meeting was concluded electing the official leadership of the association and approving its constitution.
Ethiopian Journalists Forum (EJF) is not the first association to have been established in Ethiopia, but the 9th. There are other 8 journalists’ association operating in the country.
But they all are accused of being loyal to the regime and of failing to play their role. Many journalists claim that none of the associations have done anything to bring about change on the deteriorating press freedom and safety of journalists.
As a result, the EJF has been welcomed by many journalists, who are in dire need of protection. Its formation has been good news to those who wish to see an independent institution, which is loyal only to the journalists and lays its foundation on solid principles.
Many hope that the association is a best framework to work against the deteriorating press freedom in the country and bring about change on the safety of journalists.
The EJF is open to anyone involved in journalistic profession. It registers members under three categories, which are “Ordinary Membership”, “Associate Membership”, and “Honorary Membership.”
Currently, the association has 30 founding members drawn from different media institutions. They work in newspapers, magazines, and in the new media, as reporter, editor, subeditor, columnist, author, contributor, and photographer.