Wednesday, February 26, 2014

ይድረስ ለፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ፡- በኢትዮጵያ ታሪክ ተወቃሾቹ የኦሮሞ ሕዝብና ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ብቻ ነውን እንዴ?!


በዲ/ን ኒቆዲሞስ ዕርቅ ይሁን  - nikodimos.wise7@gmail.com
‹‹ዕርቅና ሰላም የሕይወት ቅመም፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን እንደውለታ ቢስ ለሚቆጥሩ ወገኛ ሁሉ የሚሆን መልስ እነሆ!›› በሚል ርእስ የጻፉትን ጦማር እጅግ የማክበርዎና ኢትዮጵያዊው የምሆን ወንድምዎ ደጋግሜ አነብበኩት፡፡ ፕሮፌሰር በትክክል ተረድቼዎት ከሆነ እርስዎ በጽሑፍዎ ለማስተላለፍ የፈለጉት ዋንኛ መልእክትዎ፣ አንድም ‹‹ዕርቅንና ሰላም መስበክ›› ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ጠላት ወይም ውለታ ቢስ አድርገው ለሚቆጥሩ ወገኛ ሁሉ መልስ ይሆናል በሚል እነሆ ያሉት ጦማር እንደሆነ ነው፡፡
ፕሮፌሰር ለረጅም ዓመት ካካበቱት ዕውቀትዎ፣ በትምህርት ዓለም በሥራ፣ በምርምርና ጥናትዎ ከሕይወት ተሞክሮዎና ልምድዎ በመነሳትና እንዲሁም ዕድሜዎን ሙሉ ከመረመሯቸውና በአካዳሚያው ዓለም አንቱ ከተሰኙባቸው፣ ከበሬታን ካተረፉባቸውና ጥንታዊ የኾኑ መዛግብቶቻችንን በመመርመር እስካሁን ድረስ እያካፈሉን ስላለው ሰፊ የሆነ እውቀትዎ ከምስጋና ጋር ዝቅ ብዬ እጅ እነሳለሁ፡፡ ከገለታዬ አስከትዬ ግን በተለያዩ ድረ ገጾች ከሰሞኑን ባስነበቡን ጽሑፍዎ ማዘኔን ልገልጽልዎ እወዳለሁ፡፡
ይህ ጽሑፍዎ ከዕርቅና ሰላም ይልቅ ጠብንና ኹከትን፣ ከፍቅርና አንድነት ይልቅ መለያየትን የሚዘራ መስሎ ነው የታየኝ፡፡ መቼም ለእንደ እርስዎ ዓይነት ዘመኑን ሙሉ የኢትዮጵያን ጥንታዊ የሆኑ የሥነ ጽሑፍ ሀብቶች ሲመረምር ለነበረ ሊቅ/ምሁር ስለ ኢትዮጵያም ሆነ ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ን  ታሪከ ማስረዳት ‹‹ለቀባሪው አረዱት›› አሊያም ደግሞ ‹‹ልጅ ለአናቷ ምጥ አስተማረች›› እንዳይሆንብኝ እሠጋለሁ፡፡ ቢሆንም ግን ፕሮፌሰር በዚህ ጽሑፍዎ ለዕርቅና ሰላም ይሆናል ብለው ባቀረቧቸው መፍትሔዎች ዙሪያ ጥቂት ሙግቶችን እንዳቀርብልዎ አስገድዶኛል፡
በሙያዬ የታሪክ ተመራማሪ፣ የአርኮዮሊጂና የቅርስ ባለሙያ ነኝ፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት ረገድም ጥንታዊትና ሐዋርያዊት በምትሆን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ን ካሉ ሊቃውንት አባቶቼ እግር ስር ከማያልቀው ዕውቀት ምንጫቸው እጅግ በጥቂቱ ለመጥለቅ ሞክሬያለኹ፤ እስከ ሕይወት ፍጻሜዬም ከእነዚህ አባቶቼ የማያልቀውን ሰማያዊ ዕውቀታቸውንና ጥበባቸውን መጥለቄን እቀጥላለኹ ብዬ አስባለኹ፡፡ እናም ክቡር ፕሮፌሰር በአንዲት ቤ/ን ጥላ ስር መገኘታችንና ሁለታችንም የኢትዮጵያን ረጅም ዘመናት ታሪክ፣ የሕዝቦቿን ገናና ሥልጣኔ፣ መንፈሳዊና ቁሳዊ ቅርሶቿን ለመመርመር ምንተጋ ከመሆናችን የተነሣ በዚህ ጦማሬ ቋንቋ ለቋንቋ፣ አሳብ ለአሳብ እንግባባለን ብዬ እገምታለኹ፡፡
ፕሮፌሰር ‹‹ዕርቅና ሰላም ለሕይወት ቅመም›› ብለው የጻፉት ጽሑፍዎ እንደሚመስለኝ መነሻ ያደረገው ባለፈው ሰሞን በአሜሪካ ሚቺጋን ስቴት የሚኖረው ወጣቱ የፖለቲካ ተንታኝ ጀዋር መሐመድ፣ አንዳንድ በውጭ አገርና በኢትዮጵያ ያሉ የኦሮሞ ልሂቃንና የብሔረሰቡ ተወላጆች ዘንድ ዳግመኛ እንደ አዲስ በሰፊው መከራከሪያ ሆኖ በዘለቀው የኦሮሞ ታሪክ ትንታኔ፣ የሕዝቡ የነጻነት ጥያቄ፣ የኢትዮጵያ ቤ/ን ለአቢሲኒያ/ለነፍጠኛ ገዢዎች ቅኝ ግዛት ዘመቻ ዋንኛዋ አጋር ነበረች በሚሉትና በመሳሰሉት ታሪካዊና ፖለቲካዊ ትኩሳቶች ዙሪያ ሲንሸራሸሩ የነበሩና አሁንም ያሉ አሳቦች ይመስሉኛል፡፡
እርስዎም በዚህ ክርክር መነሻነት ተስበው ይመስለኛል ለዕርቅና ለሰላም መፍትሔ ይሆናል ባሉት ጽሑፍዎ የኦሮሞ ሕዝብ አውዳሚ፣ አረመኔና ጨካኝ እንደሆነ የነገሩን፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን የኦሮሞ ሕዝብ ‹‹ጋዳ›› የሚለው ሥርዓት አንዳንዶች እንደሚሉት አፍሪካ በቀል የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ሣይሆን ሕግ አልባ፣ በጭፍን የሚጓዝ የማፊያዎች ጥርቅም እንደሆነም አስረግጠው ነገሩን፡፡ እነ ጃዋርና ተከታዮቻቸውም በሸሪያ ሕግ ሊገዙንና ሊዳኙን እያቆበቆቡ ያሉ ጠባብ ብሔርተኞች፣ የኢትዮጵዊነት/የአንድነት መንፈስ ነቀርሳና የሰይጣን መልእክተኛ ናቸው ሲሉም ፈረጇቸው፡፡
አስከትለውም የኦሮሞ ሕዝብና ኢትዮጵውያን ሙስሊሞችም አባቶቻቸው በኢትዮጵያ ታሪክ፣ ቅርስና ሥልጣኔ ላይ ላደረሱት ውድመትና ጥፋት ይቅርታ መጠየቅ እንደሚገባቸው ለማሳሰብ ሞከሩ፡፡
ስለ ኦሮሞ ሕዝብ ጭካኔና አረመኔነትም ከአገር ውስጥ ካሉ ጸሐፊዎች እስከ ውጭ አገር የታሪክ ጸሐፊዎችና ተመራማሪዎች ድረስ የመሰከሩት ስለሆነ፣ ‹‹ጩኸቴን ቀሙኝ›› አሊያም ‹‹ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮኻል›› እንዲሉ ካልሆነ በስተቀር ኦሮሞዎች በኢትዮጵያና በክርስቲያኑ ሕዝብ ላይ ላደረሱት አሰቃቂ ግፍና በደል፣ እንዲሁም ወደ አንድነትና ኅብረት እንዲመጡ ላደረጓቸው ንጉሥ ምኒልክ በሀውልታቸው ስር የይቅርታ ጉንጉን አበባ በማኖር ዕርቀ ሰላም እንዲያወርዱና ለባለውለታቸው ለምድራቸው/ለአፈራቸው ልጅ ለጎበና ዳጬም ሀውልት እንዲያቆሙላቸው ምክርዎን ለግሰዋል፡፡
ፕሮፌሰር ጌታቸውን ያህል ታላቅ ምሁርና ላለፉት በርካታ ዓመታት የኢትዮጵያን ታሪክ የመረመሩ ሰው እንዴት የኦሮሞ ሕዝብንና ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን ብቻ ነጥለው በአገሪቱ ላይ ለደረሰው ውድመትና ጥፋት ተወቃሽና ይቅርታ ጠያቂዎች እንዳደረጓቸው ሊገባኝ አልቻለም፡፡ መቼም ፕሮፌሰር ኢትዮጵያ በምትባል ግዛት ይኖሩ የነበሩ የተለያዩ ሕዝቦች በተለያዩ ዘመናት ባደረጉት ጦርነትና የግዛት ማስፋፋት ወረራ የየበኩላቸውን ጥፋትና ውድመት እንዳደረሱ ይስቱታል ብዬ አልገምትም፡፡
ሌላው ቀርቶ በቅርቡ ታሪካችን ዘመን፣ በታሪክ ምሁራን ዘንድ ‹‹ዘመነ መሳፍንት›› ተብሎ በሚጠራው ዘመን በአማራነት ስም የሚጠሩ ገዢዎች፣ መሳፍንትና መኳንንት፣ የጎንደሩ በወሎ፣ የጎጃሙ በሸዋ፣ በትግራይ የእንደርታው፣ በአጋሜ፣ የአድዋው በአክሱም፣ በኦሮሞው ግዛትም የአርሲ፣ የባሌ፣ የሸዋና ወለጋ እያለ እርስ በርሱ እንዳልተላለቀና የአገሪቱን ለከፋ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ቀውሶች እንዳልዳረጉ ለምን የኦሮሞን ሕዝብ ብቻ ነጥለው ወራሪ፣ አውዳሚና ብቻ አድርገው እንደሳሉት በእጅጉ ግራ የሚያጋባ ብቻ ሳይሆን የሚያስተዛዝብም ጭምር ነው፡፡
ፕሮፌሰር በእንዲህ ዓይነት የአንድ ወገን ብቻ የታሪክ አተያይና ትንታኔና እንዲሁም ፍረጃ ዕርቅንና ሰላምን ማውረድ ይቻላል ብለው አስበው ከሆነ ይህንን ጽሑፍ እንካችሁ ያሉት ትክክል አይመስለኝም፡፡ በእኔ እሳቤ በአብዛኛው በአገራችን ታሪክ አንድን ብሔር ወይም ሕዝብ ሆን ብሎ ለማጥፋት ወይም ለመፍጀት የተደረጉ ዘመቻዎች ነበሩ ብዬ ለመውሰድ እቸገራለኹ፡፡ አብዛኛው የታሪካችን ገጽ የሚሳየን ገዢዎች ለሥልጣን፣ በገብርልኝ አልገብርህም ሰበብ የኢኮኖሚ ጥቅምንና የፖለቲካ የበላይነትን ለመውሰድ በነበረ ውድድርና ፍጥጫ በተደረጉ ጦርነቶችና ወረራዎች ብዙዎች ምስኪኖች አምነውበትም ሆነ ሳያምኑበት ጭዳ እንደሆኑ ነው የማስበው፡፡
በተመሳሳይም በአገራችን በአብዛኛው በሙስሊሙና በክርስቲያኑ መካከል ተደረጉ ጦርነቶች ውስጥም ቢሆን ሃይማኖት መሳሪያ ወይም ሽፋን እንጂ ሃይማኖትን ሰበብ አድርገው በተነሱ ተፋላሚዎች የተደረጉት ጦርነቶች ዋና ምክንያት አልነበረም፡፡ ሃይማኖት ሽፋን ነው፡፡ ጠቡና መሠረታዊው ቅራኔ የክርስትና እና የእስልምና እምነት ተከታይ የሆኑትን የኅብረተሰብ ክፍሎች እንመራሃለን ወይም እናስተዳድርሃለን በሚሉት ገዢ መደቦች የሚነሳ የሥልጣንና የኢኮኖሚ ጥቅም ጥያቄ ነበር፣ ነውም፡፡
እናም የአገራችን የፖለቲካ ታሪክ ሂደት ውስጥ የኦሮሞ ሕዝብ እንደማንኛውም የኢትዮጵያም ሆነ የዓለም ሕዝብ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በበጎም ሆነ በክፉ ጎኑ የሚነሳበት ታሪክ ያለው ሕዝብ እንደሆነ ነው የማምነው፡፡ ፕሮፌሰር የኦሮሞ ሕዝብን ብቻ ነጥለው አውዳሚና የጥፋት ልጅ እንደሆነ በጻፉበት ብዕራቸውና ለዚህም መከራከሪያቸው ከጠቀሷቸው የአገር ውስጥና የውጭ አገር ጸሐፍት መካከል ለምን እነዚሁ ጸሐፊዎች በአንጻሩ በኦሮሞ ሕዝብ ላይ የደረሰውን በደልና ግፍ በተመለከተ የተዉትን ምስክርነታቸውን ለመጥቀስ/ለመጻፍ እንዳልደፈሩ ግን ግልጽ አይደለም፡፡
እስቲ ለአብነት ያህል አፅሜ ጊዮርጊስ የተባሉ ጸሐፊ ‹‹የኦሮሞ ታሪክ›› በሚል በተዉልን የታሪክ ማስታወሻቸው ዐፄ ምኒልክና ሠራዊታቸው በኦሮሚያና በደቡብ የአገራችን ክፍሎች ባደረጉት የማቅናት ዘመቻ ወቅት በኦሮሞ ሕዝብ ላይ ስለደረሰው በደልና ግፍ የከተቡትን በጥቂቱ እንመልከት፡፡
በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን ኦሮሞ ሁሉ ተገዛ፣ በአማራ ሕግና ሥርዓት ሔደ፣ ካህናቱ አንድ ኦሮሞ አስተምረው አላጠመቁም፡፡ ይልቅስ ተፊተኛው ቂም የበለጠ ቂም በልቡ አኑረውበት መሬቱን በቀላድ ወሰዱበት፡፡ አንድ ቀላድ የቅስና አንድ ቀላድ የአወዳሽ እያሉ በዚሁ ስብከት ንጉሡን አሳመኑ፡፡ ስለ መንግሥት ያሰቡ መስለው ለንጉሡም አንድ ቀላድ፣ ለወታደር አንድ ቀላድ … መሬቱን ተካፍለው ኦሮሞን እንደ ባሪያ አድርገው ይገዙታል እንጂ የክርስቶስን መንገድ አላሳዩትም፡፡ እነርሱም የእግዝሔርን መንገድ በሚገባ አልተማሩም፣ አስተማሪም ቢመጣም ይከለክላሉ …፡፡
ፕሮፌሰር ጌታቸው የኦሮሞ ወራሪ ኃይል በአማራውና በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ን ላይ ያደረሰውን ግፍና በደል ዘርዝረው የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባዋል ባሉበት ብዕራቸው ለምን ይህንም የኦሮሞ ሕዝብን በደል ወይም የታሪካችንን ሌላውን ገጽ ቦታ አንዳልሰጡት፣ ሊያነሡት ወይም ሊነግሩን እንዳልደፈሩ ግልጽ አይደለም፡፡ ፕሮፌሰሩ መልእክቴ በኢትዮጵያ ምድር ዕርቅና ሰላም ለማውረድ ነው ካሉን ዘንድ ሚዛናዊ በመሆን አንዱን ብቻ ሳይሆን ሌላውንም የታሪካችንን ገጽ ሊያሳዩን በተገባቸው ነበር፡፡ እንዲህ ዓይነቱ የአንድ ወገን ብቻ የሆነ የታሪክ ትንታኔና ዕይታ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ወዴየትኛው የጥፋት መንገድ ይዞን እንደነጎደ በተግባርም ጭምር ዐይተነዋል፡፡
በሌላም በኩል እስቲ እስካሁንም ድረስ ሳስበው ግርም የሚለኝን ከዚሁ ካነሳሁት ርእሰ ጉዳይ ጋር የሚያያዝ አንድ ገጠመኜን እዚህ ላይ ጨምሬ ለማንሳት እወዳለኹ፡፡ ታሪኩ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪ በነበርንበት ሰዓት የኾነ ነው፡፡ በዩኒቨርስቲው ካሉ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች ዘንድ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ጥላ ስር አብረን ያለን ጓደኛዬ በአንድ ወቅት ‹‹ራእይ ማርያም›› ከሚል የጸሎት መጽሐፍ ኮፒ የተደረገ ጽሑፍ ከአንድ ከሌላ ኦሮሞ ብሔር ተወላጅ ጓደኛው ጋር ይዞ በመምጣት እንዲህ አለኝ፡፡
‹‹ይቅርታ፣ ከልቤ አዝናለሁ … በክርስቶስ ኢየሱስ፣ በጌታችንና በመድኃኒታችን ክቡር ደም ፈሳሽነት/ቤዛነት ሁላችንም በአንድ መንፈስ፣ ሰማያዊ ዜጋ ሆነን የእግዚአብሔርን መንግሥት እንወርሳለን ብላ በምታስተምር ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንዲህ ዓይነት ሕዝቦችን የሚለያይና የሚከፋፍል መጽሐፍ መኖሩን እስከዛሬ አላውቅም ነበር፡፡›› በጓደኛዬ ንግግር ውስጥ እልክና ብርቱ የሆነ አንዳንች የቁጭት መንፈስ ነበር የሚነበብበት፡፡ ‹‹… ለመሆኑ ይህን መጽሐፍ አይተኸው ወይም አንብበኸው ታውቃለህ በማለት ‹‹የራእይ ማርያም›› መጽሐፍን አንድ ገጽ ኮፒ እንዳነበው በእጄ ሰጠኝ፡፡ እንዲህ ይላል፡-
… ከስር እስከ ጫፍ፣ ከጫፍ እስከ ስር ድረስ በአምስት ሺሕ ዓመት የማይደረስበት ትልቅ ገደል አሳየኝ፡፡ ያንዱ ነፍስ በአንዱ ላይ ሲወድቅ ዐየኹ፡፡ እኔም ምንድናቸው ብዬ ልጄን (ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ኢየሱስን መኾኑን ልብ ይሏል) ጠየቅኹት፡፡ እርሱም እንዲህ ሲል መለሰላት፡- … አራስ፣ መርገም፣ ደንቆሮ፣ ‹‹እስላም››፣ ‹‹ጋላ››፣ ‹‹ሻንቅላ››፣ ‹‹ፈላሻ›› ጋር የተኙ፣ ፈረስ፣ አህያ፣ ግመል በግብረ ስጋ የሚገናኙ፣ ወንዱም ግብረ ሰዶም ወገሞራ የሚዳረጉ… እነዚህ ሁሉ ኩነኔያቸው ይህ ነው አለኝ …፡፡
በጊዜው ይህን ጉድ ካነበብኩ በኋላ እንዲህ ዓይነቱን ክፋትና እርግማን የሞላበት መጽሐፍ ቤተ ክርስቲያኒቱንና እውነተኞቹን የወንጌል መምህራን የሆኑትን አባቶቻችንን እንደማይወክል ባውቅም ይህ የጸሎት መጽሐፍ ተብዬ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም ታትሟልና በጊዜው የመከራከሪያ አሳብም ሆነ የምሰጠው ምላሽ አልነበረኝም፡፡ ግና ስለ ስለዚሁ የጸሎት መጽሐፍ የኩነኔ ፍርድ ጥቂት ነገሮችን ለማለት ያህል፤ መቼም ሌላ ስምና መልክ እስካልተሰጠው ድረስ በመንፈሳዊው ዓለም አስተምህሮ/ሕግ ካልተፈቀደልንና የእኛ ከሆነችው ሴትም ኾነ ወንድ ውጭ መሔድ ዝሙት ነው፡፡
‹‹ከጋላ›› ወይም ‹‹ከሻንቅላ›› ‹‹ከእስላም›› ወይም ‹‹ከፈላሻ›› ጋር ስለተኛን ወይም ስለዘሞትን የተለየ ነገር ሊሆንም ሊደርስም አይችልም፣ በአምስት ሺሕ ዘመንን በሚያስኬድ ገደል ውስጥም ልንጣልም አንችልም፡፡ ደግሞስ ምን ዓይነት ሕሊና ያለው ሰው ነው ሰውንና እንሰሳን በእኩል ሚዛን አስቀምጦ ፈረስም ተገናኘህ ‹‹ሻንቅላ›› ወይም ‹‹ፈላሻ›› ምንም ልዩነት የለውም ያው ነው በሚል የሚጽፍ፡፡
አንድን ጎሳና ብሔር ለይቶ ከእነርሱ ጋር ከተኛህ እንዲህ ዓይነት ቅጣት ይደርስብሃል/ያገኝሃል ብሎ እንዲህ ዓይነቱን መርገምን፣ ጥላቻንና ክፋትን የተሸከመ ድርሳን ቅድስት፣ ንፅሕትና ርትዕት በኾነች በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም አሳትሞ በማቅረብ፣ ‹‹ፈላሻነቱንም›› ኾነ ‹‹ሻንቅላነቱን›› ወዶና ፈቅዶ ባላመጣው ሰው ሕሊና ውስጥ የጥላቻ መርዝ እንዲረጭና ልቦናው ክፉኛ እንዲቆስል ምክንያት ኾኗል፡፡
ይህ ትናንትና እንደ ዘበትና ቀልድ ያየነውና በጊዜው በይቅርታ መፍትሔ ያላበጀንለት ነገር ይኸው ዛሬ ከታሪካችን ማኅደር እየተመዠረጠ የብዙዎችን ቁስል እያመረቀዘ ቤተ ክርስቲያኒቱንም ኾነ ተከታዮቿን በጥላቻ ዓይን እንዲታዩ ምክንያት ከኾነ ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ እነዚህና ሌሎች መሰል ታሪኮችን ዕድሉ ያጋጠመን ሁሉ ደጋግመን ሰምተናቸዋል፡፡ መፍትሔው ምን ይሁን፣ ምን መላ እንፍጠር ከማለት ይልቅ ያለፈ ታሪክን ማንሳት ምን ይጠቅማል በሚል በማድበስበስ የተውናቸው ክስተቶች እያመረቀዙ በመካከላችን መፈራራትንና ጥላቻን አነገሡብን/አባባሱብን እንጂ መፍትሔ አልሆኑንም፡፡
ብዙዎቻችንን እያከራከረን ስላለው የትናንትና ታሪካችን ርእሰ ጉዳይ ስንመለስም አንድ ማስተዋል ያለብን ነገር ያለ ይመስለኛል፤ ይኸውም አብዛኛው የአገራችን የፖለቲካ ታሪክ በጦርነትና በወረራ፣ በገብር አልገብርም፣ በልግዛህ አልገዛም በተደረገ ግብግብና ጭፍጨፋ በደም የቀላ ታሪክ ነው ያለን መሆኑን፡፡
አንዱ የገዢ መደብ ሌላውን፣ ክርስቲያኑ ሙስሊሙን፣ ሙስሊሙ ክርስቲያኑን ያጠቃበት የጨፈጨፈበት በርካታ ዘመናቶች የታሪካችን አካል ኾነው አብረውን አሉ፡፡ አንዱ አገር የሌላውን አገር በጦርነት በመግጠም ሀብት ንብረቱን በመዝረፍ፣ መሬቱን በመቀማት፣ በምርኮና በባርነት በማጋዝ ያሳለፍናቸው የታሪካችን ቁስሎች በፍቅር ዘይት ለስልሰውና በዕርቀ ሰላም ፈውስ አግኝተው መፍትሔ ካላገኘን አንድ ብሔርን/ሕዝብን ወይም ሃይማኖትን ብቻ ነጥሎ እንደ ጥፋተኛና አውዳሚ አድርጎ ማቅረብ ወደምንናፍቀው የዕርቅና የሰላም ምንገድ ያመጣናል ብዬ አላስብም፡፡
ደግሞስ አማራው ከኦሮሞው፣ ኦሮሞው ከትግሬ፣ ወላይታው፣ ከጉራጌው፣ ሐረሪው፣ ከአፋር በደም፣ በአጥንት በተዛመደ፣ በቋንቋ፣ በሃይማኖትና በጋራ ታሪክ  በተሳሰረ ሕዝብ መካከል ብሔርና ጎሳ ለይይቶ መወቃቀሱ ጥቅሙ ምንድን ነው፡፡ ትርፉስ ለማን ነው?! በእርግጥም ለእውነተኛው ዕርቀ ሰላም ቀናውን መንገድ ካላመቻቸን ላለፉት ሃያ ዓመታት ታሪክንና ሃይማኖትን ሽፋን አድርገው እየተካሔዱ ያሉ የቂም በቀል ዘመቻዎች ፍፃሜያቸው እጅግ አስፈሪና አሳፋሪ እንደኾኑ ነው የታዘብነው፡፡
በሃይማኖትና በብሔርተኝነት ስም በአዲስ አበባና በሌሎች ክልል ከተሞች ቦግ እልም እያለ ያለውና ተዳፈኖ ያለው የረመጥ እሳት ሊያስከትለው የሚችለውን አደጋ ከወዲሁ መፍትሔ ካላበጀንለት (ያው እስከ ዛሬ ድረስ በአርባ ጉጉ፣ በበደኖ፣ በአርሲ ነገሌ፣ በወተር፣ በቤሻንጉል ጉሙዝ፣ በጅማ … የደረሰው አሰቃቂ እልቂት፣ ጥፋትና ውድመት ሳይዘነጋ) ይህ ዓለም ሁሉ የሚያደንቀውና የምንኮራበት፣ በቋፍ ያለው ለዘመናት አብረን በፍቅርና በወዳጅነት የቆየንበት አኩሪ ታሪካችን በነበር ልናወሳ የምንገደድባቸው ጊዜያቶች ሩቅ ሊኾኑ እንደማይችሉ በርካታ ማሳያዎችን መጥቀስ የሚቻል ይመስለኛል፡፡
ያለፈው ሰሞን የእነ ጃዋር መሐመድና የኦሮሞ ወንድሞቻችን ኦሮሞነትን ከኢትዮጵያዊነት ነጥለው ያቀረቡበት ትርክትና የትናንትና ክፉ የታሪክ ጠባሳችን፣ በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ላይ ያላቸውና እያንጸባረቁት ያለው ቁጣ፣ ቅያሜና ዛቻ የነገይቱ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱስ ዕጣ ፈንታ ምን ሊሆን ይችላል ብለን እንድንጠይቅ፣ እንድንሰጋ ያስገድደናል ብዬ ለማለት እደፍራለኹ፡፡
አገሪቱን እያሥተዳደረ ያለው መንግሥትም ለጉዳዩ መፍትሔ ከመስጠት ይልቅ ያለ ቅጥ ያራገበው የብሔር ፖለቲካ ወላፈኑ እራሱንም ጭምር እየለበለበው እንደሆነ እያየን ነው፡፡ ‹‹ካፈርኩ አይመልሰኝ›› በሚል ግትርነትና ዕድሜዬን ያራዝምልኛል በሚል እንዲሁ በአገም ጠቀም የተወው የጎሰኝነት/የዘረኝነት ጉዳይ ነገ መዘዙ ከየት እስከ የት ሊመዘዝ እንደሚችል መገመት የሚያዳግት አይመስለኝም፡፡ ትናንትና በሆነው በሚያኮራው ታሪካችን ተከባብረንና ተዋደን፣ አሳፋሪና ክፉ ጠባሳ የተዉብንን የታሪካችንን ምዕራፍ ደግሞ በይቅርታ ዘግተን በፍቅርና በመቀባበል መኖር ካልተቻለን የሚጠብቀን ዕድል ጥላቻ፣ መከፋፋት፣ ጠላትነት፣ መለያየት … ብቻ ነው ሚሆነው፡፡
ይህ እንዳይሆንብን፣ ይህ ክፉ ነገር እንዳይደርስብን ቆም ብለን ማሰብ ያለብን ጊዜ ላይ ያለን ይመስለኛል፡፡ እንደ ፕሮፌሰር ጌታቸው ያሉ የዕድሜ ባለፀጋዎችና ምሁራን፣ የታሪክ ተመራማሪ ምሁራኖቻችንና የፖለቲካ መሪዎችም ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ወደ ፍቅር፣ ሰላምና አንድነት የሚመጡበትን ቀና የሆነ መንገድ በማመቻቸት አገሪቷን ከተደቀነባትና ካዣንበባት ጥፋት ሊታደጓት የትውልዱንም ልብ በፍቅር ዘይት አልስልሰው ለይቅርታ/ለዕርቀ ሰላም ሊያዘጋጁት ጊዜው አሁን ይመስለኛል፡፡
ከሁሉም በላይ ደግሞ የሃይማኖት አባቶችና መሪዎች ከእኔ ይበልጥ ከእኔ ይበልጥ የፉክክር መንፈስ ወጥተው ለአገርና ለሕዝብ የሚሆን የዕርቀ ሰላም መልእክት ይዘውልን ሊመጡ ይገባቸዋል፡፡
ነገሥታትን/መንግሥታትንና ክፉ መሪዎችን በመገሠጽ፣ በሕዝቦች መካከል ፍቅርንና ሰላምን፣ በአገራችንም ብሔራዊ ዕርቅን በማስፈን ሐዋርያዊ ተልዕኮአቸውንና መንፈሳዊ ግዴታቸውን ለመወጣት ጊዜው አሁን ነው፡፡ አሊያ ግን ዕርቅንና ሰላምን ያወርዳሉ ያልናቸው አባቶቻችንም እርስ በርሳቸው ተለያይተውና ተወጋግዘው፣ ለነገ ህልውናችን በሚል ሰበብ የፖለቲከኞችን ጉያ የሚመርጡ ከሆኑ፣ ከእውነትና ከፍትሕ ጎን ለመቆም መንፈሳዊ ድፍረትና ወኔ ከተለያቸው እንዴት ባለ መንገድ ነው ፍቅርንና ዕርቅን ሰብከው አገሪቱንም ሆነ ትውልዱን ከጥፋትና ከሞት መንገድ ሊታደጉት የሚችሉት?!
በታሪካችን ለኾኑት ስህተቶች በግልፅ ይቅርታ ተጠያይቀን ዕርቅ ማውድ ካልቻልን አስቸጋሪ ነው፡፡ የሚሻለው መነጋገርና መግባባት ነው፡፡ እንደ እውነቱም ከኾነ ትናንትና ለኾነው በደል እውቅና መስጠት ሳይቻል ዕርቅ ዕርቅ የሚለው ነገር ከጉንጭ አልፋ ወሬነት የሚያልፍ ፋይዳ ይኖረዋል ብዬ አላስብም፡፡ ዛሬ እንደገና ከበርካታ ዓመታትም በኋላ ተመልሶ እነ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ እነ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ የምኒልክ ጦር በአያቶቻችን ላይ ያደረሰውን በደል አንረሳውም ወደሚል አዙሪት መልሶ እየከተታቸው ያለው ይኸው በይቅርታ ያልተወራረደው ታሪካችን ጥሎብን የሔደው ክፉ አበሳና ጠባሳ ይመስለኛል፡፡
እናም እንደ ፕ/ር ጌታቸው ያሉ ምሁራንና የዕድሜ ባለጠጋዎች የአንድ ወገን ታሪክን ብቻ በማጉላት ሳይሆን ሚዛናዊነት ባለው መልኩ ታሪካችንን በማቅረብ የሁላችንም የጋራ ቤታችን በሆነች ኢትዮጵያችን ተስማምተን፣ ተዋደን፣ ተፋቀርንና ተከባብረን የምንኖርባት አገር እንድትኖረን የታላቁን የሰላምና የይቅርታ አባት የኔልሰን ማንዴላን ዓይነት ሚና በመጫወት የትውልድ ባለውለታ ይሆኑ ዘንድ በእኔና በትውልዴ ስም አደራ እላለሁ፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!!

በህዝባዊ ሰልፉ ለኦሰካር ሽልማት ከታጨው አደባባይ ምን እንማር


በአብራሃም ዘታዬ ከ ጀርመን
ተቃውሞንም ሆነ ድጋፍን ለመግለጽ ወደ አደባባይ መውጣት የተለመደ ነገር ነው። በኢትዮጵያ ታሪክ የ አዲስ አበባው መስቀል አደባባይን ብንመለከት እንኳ ያላስተናገደው ሃይማኖታዊ ፖለቲካዊ ማህበራዊ ክንውን የለም። እነዚህ ክንውኖችን በበላይነት የዘመሩባቸው የዘፈኑባቸው የቦተለኩባቸው ግለሰቦች የተለያየ በጣም የማይስማሙ ርዕዮተ አለማት አቀንቃኞች ነበሩ ናቸውም። የኮሚኒስት አስተሳሰብ የነበራቸው የቀድሞዎቹ መሪዎች ኮሎኔል መንግስቱና  መለስ ዜናዊ በመስቀል አደባባይ አንዱ አንዱን ረግመውበታል። በዝነኛው የ1997 ቱ ምርጫ ሚያዚያ 29 ኢህአዴግ በማግስቱ ሚያዚያ 30 ደግሞ ዋና ተፎካካሪ የነበረው ቅንጅት ማንነታቸውን አሳይተውበታል። አላማው ለየቅል ነበር።
ከአዲስ አበባ ወጣ ስንልም ህዝቡ  በአደባባይ ወጥቶ ድጋፉን ወይም ተቃውሞን የሚገልጽባቸው አደባባዮች ሞልተዋል። የሚቃወመዉም ሆነ የሚደግፈው ሰው ግን ከዛ ቦታ የሚገኘው ለ አንድ ቀን ለዛውም ለሰልፉ በተፈቀዱት ጥቂት ሰዓታት ብቻ ነው። የመስቀል ደመራ ተደምሮ  እሳቱን ለኩሶ እጣኑን አጭሶ ጸሎቱ ሰማይ ይድረስ አይድረስ ሳያረጋግጥ ተቃጥሎ ሳያልቅ ደመራው ወዴት እንደወደቀ  ሳያይ እሽቅድምድሙ ቶሎ ቤት ለመግባት ነው። ይህን በዩኔስኮ በ አለም ቅርስነት የተመዘገበ የመስቀል ደመራ በዓል ለማነፃፀሪያ ተጠቀሰ እንጂ  በዚህ ጽሁፍ ለመጠየቅ የምፈልገው  የፖለቲካ ጥያቄን ህዝቡ ለመጠየቅ ተሰብስቦ  አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ምላሽ ሳያገኝ  አደባባዩን ለምን ሰው ይለቃል ለማለት ነው።
አስረጂ
በአማራ ክልል የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የብአዴን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አለምነው መኮንን በአማራ ህዝብ ላይ የሰነዘሩትን ዘለፋ በመቃወም  የባህር ዳር ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ  ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ በቅርቡ ተደርጓል።
“ብአዴን የአማራውን ሕዝብ አፍኖ መግዛት ያቁም”  “የኢህአዴግ አምባገነን አገዛዝ ሰልችቶናል”  “የህዝብን ክብር የደፈሩት አቶ አለምነህ መኮንን ለፍርድ ይቅረቡ”  እና መሰል አገዛዙን ያስበረገጉ  መፈክሮች ተሰምተዋል። እጅግ የሚደነቅ ሰልፍ ነበረ።ጮሆ ግን ከመመለስ ይልቅ ቢያንስ ይሄ ለ አፉ መረን የሌለው ሰው ከስልጣን ካልወረደ ህዝቡ ከ ባህርዳሩ ሰልፍ አንበተንም  ቢልስ ለማለት ወደድኩ። ጠቅላላ መንግስቱ ይውረድ ብሎ መጠየቅም ባይሆን ይሄን አንድ ግለሰብ ከስልጣን የማባረር ስራ ለ ክልሉ የሚቀል ሰለሆነ ከስራ ለጊዜውም ቢሆን አግደነዋል ካላላችሁን አንላቀቅም ማለት ይችል ነበር ህዝቡ። አንድን ተራ ግለሰብ ማባረር ከተላመድን ሌላውም ይቀጥላል።
UDJ Bahirdar demonstration
የግድ የሌላ ሃገር ተሞክሮ መዘርዘር አለበት እንዴ?
ለረጅም ሰዓታት ፥ ለቀናት ለውጥ ካልመጣ ላይሄዱ ከሰልፍ አደባባይ እግራቸውን አጣብቀው ነጻነትን ሰንቀው የታገሉ የድል ባለቤት የሆኑ የሌሎች ሀገራት ታሪክን ካስፈለገ እነሆ
የቱኒዝያ ተሞክሮ
መንግስታቸው በሙስና ተጨማልቆ  የመናገር ፥ የፖለቲካ ነጻነት ተነፍጎት ስራ ዕጥነት ተንሰራፍቶ በኑሮ ውድነት ማቆ ይኖር የነበረው የቱኒዚያ ህዝብ የስርዓት ለውጥ ያመጡት ባንድ ወር  ጊዜ (10 December 2011 – 14 January 2011) ያለማቋረጥ ባዳረጉት ህዝባዊ አመጽ ነው።
የቱኒዝያን ተሞክሮ አይተው የተነሱት ሊብያውያን 42 ዓመት ጫንቃቸው ላይ የነበረውን ሙአመር ጋዳፊን ለማውረድ የፈጀባቸው  6 ወር ብቻ ነው።ትግሉ በ17 February 2011 ተጀምሮ በ 23 August 2011 ጋዳፊ ተገደለ።
በህዝባዊ ሰልፉ ለኦስካርሽልማትየታጨው  “አደባባይ” 
ግብጻውያን ሆስኒ ሙባረክን ፌብራሪ 2013 ያስወገዱት ለ 17 ተከታታይ ቀንና ሌሊት በካይሮ ታህሪር ስኩየር ባደረጉት ሕዝባዊ ሰልፍ ነው። ሙባረክን አስወግዶ ስልጣን የያዘውንም ሙስሊም ብራዘር ሁድ ስብስብ ተረኞቹ ጁላይ 2013 ሲያስወግዷችውም በተቃውሞ የስልፍ ቦታቸው በታህሪር ስኩየር ቀን ተሌት ሳይለዩ ደጅ የጠኑት ከአንድ ሳምንት አይበልጥም። ይሄ ሁሉ ድራማዊ ሽግግር የመጣው ደሞ ሳይታክቱ በሰልፍ ቦታቸው በመገኘታቸው ነው።“ዘ ሰኩዬር”   የሚል ዶክመንታሪ ፊልም ተሰርቶለት (የታህሪር አደባባይ አብዮት) በቅርቡ  የ 2014 ለ ኦስካር ሽልማት የታጨውም በዚሁ ነው ። www.cnn.com/2014/02/11/opinion/egypt-revolution-anniversary
በመጪው ማርች 2 2014 አካዳሚ አዋርዱን ከመቀበሉ በፊት  ፊልሙ ዘ ፒፕልስ ቾይስ ዶኩመንታሪ አዋርድ  በ ቶሮንቶ 2013 ኢንተርናናል ፊልም ፈስቲቫል   እና የ2013  ዘ ኦዲየንስ አዋርድ በ ሰንዱንስ ከተማ   አሸናፊ የሆነ ነው።
http://www.youtube.com/watch?v=twB2zAOzsKE
እንግዲህ የኛ መስቀል አደባባይ ሳይሆን የደመራ በዓል ነው በ ዩኔስኮ የ አለም ቅርስ ሆኖ የተመዘገበው። ለምን  ሰለነጻነታችን ሰለሃገራችን አንድነት የምናቀነቅንበት ይኸው አደባባይ ሆኑ ሌሎች ብሶት መተንፈሻ ቦታዎቻችን ከምናደርገው እንቅስቃሴ ጭምር ለምን ለ አለም አቀፍ ሽልማት አልታጨም? ዶክመንታሪ ፊልም ሆኖ የዶክመንታሪ ፊልም አዋርድ ማግኘቱ ይቅርና ሰልፋችንን መቅረጽስ ይፈቀድልናል ወይ? ከ ውጪ አድናቂዎቻችን ፊልም ሊሰሩልን የሚመጡት እኛ እንደግብጻውያን ጣህሪር አደባባዮቻችንን ቀን ተሌት በማጨናነቅ ነጻነታችንን ስናፋጥን ብቻ ነው። ከ ትንሹ በ የ አዳራሹ የምንደልቀው የነጻነት ዕጦት ድቤ እስከ ታላላቅ የ አደባባይ ተቃውሞ ነጋሪቶቻችን ድረስ ምን ያህሉ የ ገዢዎቻችንን ጆሮ በሱት? ምን ያህሉ የ አለም አቀፍ ተቋማት ሚዲያዎችን ቀልብ ሳበ?
የ አንድ ቀን ጩኸት ብቻ ሆኖ ማለፉ ሊያንገበግበን ይገባል። የተባለውን ብቻ የሚሰራው ሃይል ማርያም ደሳለኝ እኮ ነግሮናል ላንሰማ ቹ ነገር ለየ እሁዱ  ሰላማዊ ሰልፋች ሁ የፖሊስ ጥበቃ መመደቡ ሰለቸን ብሎ።
ጸረ አማራ አቋም እንዳለው በግልጽ ስድብ ያሳወቀውን ብ አ ዴ ን /ኢህ አዴግ ን በመቃወም አንድነት ፓርቲ እና መኢአድ በጋራ የጠሩት የባህርዳር ደማቅ ሰልፍ ሰልፍ ብቻ ሆኖ በማለፉ ይበልጥም ኢህ አዴግ ተቃዋሚዎች በባህር ዳር አስፈራርተው ለቀቁኝ ብሎ ይደሰታል። ሆኖም ዛሬም በማግስቱ እዛው ሰልፋችንን ባናቋርጥ ከምር አገር ጥሎ ይጠፋ ነበረ ያልለመደው ጠንካራ ተቃውሞ ሰለሚሆንበት።
የዩክሬን ተሞክሮ
ወቅታዊ ከሆነው በ አውሮፓ የዩክሬን ተቃውሞም የምንማረው ቀን ተሌት የሚታገሉለት ህዝባዊ አመጽ እያሸነፈ መምጣቱን ነው። በዋና ከተማው ኪየቭ በሚገኘው ኢንዲፐንደንስ ስኩየር ዩክሬናውያን በ አንድነት መንግስት ካልተለወጠ አንንቀሳቀስም ብለው ለነጻነታቸው ዋጋ ከፍለዋል። የህዝብ ተመራጭነቱን ያስመሰከረው ፓርላማ ያንኮቪችን ለማስወገድ የተስማማው ህዝቡ ለ አንድ  ሳምንት ያህል ሳይታክት በ አደባባዩ ባሳየው መስዋዕትነት ነው።
ከ  10 ዓመት በፊትም የቡርትካናማ አብዮት ተብሎ የሚታወቀውን ያካሄዱ ናቸው። የሚገርመው  ምርጫ በድጋሚ እንዲካሄድ በተጠራው  በዚህ ቡርትካናማ አብዮት  ለሁለት ወራት ከ22 ኖቬምበር 2004 እስከ 23 ጃኑዋሪ  2005  በዛው አደባባይ ጠይቀው ዛሬ ያስወገዱት ያንኮቪች ያኔ ምርጫውን ፍርድቤት አጽድቆለት  ሲያስተዳድራቸው የነበረ ነው።
ህዝብ መሪውን በ አደባባይ ይመርጣል ህዝብ መሪውን በ አደባባይ ተቃውሞ ያባርራል።
ለማጠቃለል
የቱኒዚያ የግብጽ የ ዩክሬን ህዝብ መጀመሪያ ለሰላማዊ ሰልፍ ወጥተው  ይጠይቁና ሲቀጥል ወደ ህዝባዊ አመጽ አምርተው ከሚሰበሰቡበት አደባባይ ላፍታም ውልፍት ሳይሉ ስለታገሉ መሪዎቻቸውን ቀይረው የየጊዜውን ነፃነት ምን እንደሚመስል አወዳድረዋል።እኛ 40 ዓመት በላይ ያወዳደርነው አለመታደል ሆኖ ክፉና አምባገነን ገዠዎችን ነው   ዲሞክራሲያዊ ስረዓት በ ሃገራችን ለመገንባት ከ ሰላማዊ ሰልፍ እና ከ ህዝባዊ አመጽ በተጨማሪም ህዝባዊ አድማ እና ህዝባዊ እምቢተኛነት ልንከተለው የሚገባን ቀላል የትግል ስልቶች ናቸው።
ኢትዮጵያውያን በሃገር ቤት የሚያካሂዷቸው ሰልፎች ላይ ፍት ሃዊ መልስ ካላገኙ ከ አደባባይ ባይነቃነቁ መንግስት ያልተለመደ ነገር ስለሚሆንበት ይደነግጣል፥አለም አቀፍ ትኩረትም እናገኛለን።
ኢትዮጵያውያን በውጪ አገር ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸው፥ መንግስት አንቀጥቅጥ ምክክር በ የ አዳራሹ ማሰማታቸው እንኩዋን ሌላ አለም አቀፍ ትኩረት ሊያገኝ በዛው ሃገር ያሉ ኢትዮጵያዉያን ጥሪውን የማይሰሙበት ሁኔታ አለ።የተቀናጀ የተደራጀ ፖርታል ማስፈለጉ ይሰመርበትና በሰው ሃገር ምላሸ እስከምናገኝ ሳንታክት ማሳሰብ ያሰፈልጋል።
የጎን ጥቆማ
አለም አቀፍ ትኩረት የሳበው የ አውሮፕላን ጠለፋ እንኳ አእምሮው በተነካ ግለሰብ ድርጊት ነው ብለው የስዊዝ ሚድያዎች አራግበውታል። ጥያቄው ምን ያህል ተከላክለነዋል ነው። በሚሉትም መንገድ ቢሆን የሃገር ቤቱ የመኖር የመንቀሳቀስ ነጻነት ዕጦት ጨርቅ ያስጥላል ለማለት ማፈር የለብንም።  ማራገብ ከተነሳ ፓይለቱ ኮምፒተሩን ሲከፍት ካሜራውን የሚሸፍነው የወያኔ ደህንነት በሚያደርገው የኢንተርነት የኮምፒተር ስለላ ግራ በመጋባት  ነው ማለት ይቻላል ።
በአሜሪካና በ አንግሊዝ ያሉ የፖለቲካ አቀንቃኞቻችን ጋዜጠኞቻችን ኮምፒተር በ ወያኔ ቫይረስ ሲጋለጥ ለምን የተቃውሞ ሰልፍ እንዳልተጠራ ይገርማል።ለ አዕምሮ ጭንቀት የዳረገውም የነዚህ ወገኖቹ ና የሱም መሰለል ይመስላል። ጉዳዩን ያጋለጡት ፕራይቬሲ ኢንተርናሽናል እና ሲተዘን ላብ የተባሉ አለም አቀፍ ተቋማት ምስክርነታቸውን የሰጡን ሰለሆነና የተጀመረውን ክስ ለማገዝ  ከተቻለ ለብቻው ሰልፍ ይጠራበት ካልሆነም በሌላው ሰልፍ ታከን ድምፃችንን እናሰማ የኛንም የቴክኖሎጂ ነጻነት የኛንም ደሕንነት ጠብቁልን ለማለት ያመቻል ። ፊንፊሸር ስፓይ እና ፊንስፓይን ለፀረ ህዝብ መንግስታት የሚሸጠው ጋማ  ግሩፕ ካምፓኒን ሆነ በሰው ሃገርም የሚሰልለንን ወያኔን ለመቃወም ቦታው ምቹነቱ  በውጪ ባሉ ኢትዮጵያውያን ያደላል። ነግ በኔ ብለን ድርጊቱን አለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲያውቀውና እንዲያወግዘው ማድረግ አለብን።
አብርሃም  ዘታዬ   ከጀርመን
zeabraham@gmail.com

በአባይ ግድብ ጉዳይ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር እየተነጋገርኩ ነው አለች


ዋሽንግተን ዲሲ፤ የካቲት 18/2006 (ቢቢኤን) ፦ አራት ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ዶላር ይፈጃል የተባለዉ ግድብን እንገነባለን በማለት የኢትዮጵያ መንግስት በቦንድ ስም ገንዘብ ለመሰብሰብ ያደረገዉ ሙከራ እምብዛም አለመሳካቱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ መንግስት የግንባታዉ ፕሮጀክት ሰላሳ አራት ከመቶ ተጠናቋል ቢልም ግብጽ ባሰማችዉ ተቃዉሞ የግድቡ ግንባታ መስተጓጎሉን የመገናኛ ብዙሗን ዘግበዋል።Rile river facts and information in Amharic
የኢትዮጵያ ዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሆኑት አቶ አለማየሁ ተገኑ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ “ኢትዮጵያ ችግሩን ለመቅረፍ ከሱዳን ጋር ዉይይት ጀምራለች” ሲሉ ገለጸዋል። ግብጽን ወደ ዉይይቱ ሒደት ለማምጣት እየተጣረ መሆኑን የገለጹት ሚኒስቴር ሒደቱ ምን እንደሚመስል ግን ያመላከቱት ነገር የለም።
ሱዳንና ግብጽ ከግድቡ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ኢትዮጵያ ብትገልጽም፤ ሁለቱ አገራት ግን ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ ሲሰጡ አልተስተዋልም። ግብጽ ሰማኒያ ከመቶ የሚሆነዉ የዉሃ ሐብቷ ከአባይ እንደሚመጣ ይታወቃል፤ የአባይን ጉዳይ እንደ ህልዉና ስለምትመለከትዉ የህዝብ ድጋፍ የሌለዉ የመላኒየሙ ግድብ እንደምን ዉጤታማ ይሆናል የሚለዉ ጉዳይም አጠያያቂ እየሆነ ነዉ።
ግድቡን ለመገንባት እስከ ሐያ ሺ የሚደርሱ ኢትዮጵያዉያን መፈናቀላቸው የታወቀ ሲሆን 70 ሚሊዮን ኩቢክ ሜትር ዉሃን ያከማቻል ተብሎ የተነገረት ግድብ ከፈነዳ ከፍተኛ የዉሃ መጥለቅለቅ ሊፈጥር ይችላል የሚል ስጋት አለ።
ኢትዮጵያ ግድቡ በአዉሮፒያኑ ቀመር 2017 ሲጠናቀቅ እስከ ስድስት ሺ ሜጋ ዋት የሚደርስ የኤለክትሪክ ሐይልን ለማመንጨት ብቃት ይኖረዋል ትላለች። ይህ ዉጥን ከግድቡ ባላንጣዎች ከሱዳናን ግብጽ ብቻ ሳይሆን” አባይ ከመገደቡ በፊት የመብት ጥሰቱ ይከበር” ከሚሉ ኢትዮጵያዉያንም ጭምር ጽኑ ተቃዉሞ እየገጠመዉ ነዉ። ኢትዮጵያ ከፕሮጀክቱ ዋነኛ ባላንጣ ከግብጽ ጋር በቀጥታ መነጋገር ሲገባት፤ ከሱዳን ጋር ዉይይት መጀመሯ ለምን እንደሆነ የዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴሩ ግልጽ አላደረጉም።
በተያያዘ ዜናም ጠቅላይ ሚኒስቴር ሐይለማሪያም ደሳለኝ ቀደም ሲል በህዳር 24/2006 ወደ ሱዳን ተጉዘዉ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸዉንና ህወሃት የተመሰረተበትን 39ኛ አመት ለማክበር የሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኡመር ሐስን አልበሽር በየካቲት 11/2006 ወደ መቐሌ መጓዛቸዉን ይታወቃል።ይህ ከወትሮ የተለየ ቁርኝት እንደምን ተከሰተ በማለት ጥያቄ የሚያነሱ ወገኖችም አሉ።
የሱዳን የዉጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አሊ አልቀርዲ በህዳር 23/2006 ኢትዮጵያና ሱዳን ያላቸዉን የድንበር ልዩነት አስወግደዉ መስማማታቸዉን ይፋ አድርገዋል።
ኢትዮጵያ ድንበሯን ለሱዳን ቆርሳ ለመስጠት መስማማቷ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያለዉ ብቻ ሳይሆን ህወሃት በስልጣን ለመቆየት የተቃዋሚ ሐይላትን ለመግታት አጎራብች አገራትን እየደለለ ነዉ የሚሉም አሉ።ህወሃት ስልጣኑ በህዝብ ከተወሰደ ሐብትን ወደ አጎራባች አገሮች አሽሽቶ ለመደላደል የሚያደርገዉ ሴራ ይኖራል በማለት ጉዳዩን ከመልካዓምድራዊ የፖለቲካ አለመረጋጋት ጋር የሚያይዙም አሉ።
አንድንድ ተንታኞች ደግሞ አባይን መገደብ የሚለዉ ሐሳብ ሶስት ዲሞክራሲያዊ ያልሆኑ አገራት አንባገነናዊ መንግስቶች በስልጣን ላይ ለመቆየት የሚያደርጉት ወከባ ነዉ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በግድቡ ስም ገንዘብ ሲሰበስብ፤ ሱዳንና ግብጽ ደግሞ ብሔራዊ የሆነ ስጋት እንዳንዣበበ በመስበክ ህዝብን የሚያደናግሩበት ትርኢት ነዉ ይላሉ።
ቀድም ሲል ባሶንዳ በሚባለዉ የሱዳን የጠረፍ ከተማና አካባቢ 77 ኢትዮጵያዉያን በሱዳናዉያን መገደላቸዉን ቢቢኤን ዘግቦ ነበር ።ይህ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት እንዳለዉ ባይታወቅም፤ የሚታወቀዉ ነገር ግን የኢትዮጵያ ዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሆኑት አቶ አለማየሁ ተገኑ የአባይ ግድብ አስመልክቶ ከሱዳን ጋር ዉይይት መኖሩን መናገራቸዉ ነዉ።
በሱዳን ስለሞቱት 77 ኢትዮጵያዉያን የሚናገር ይኖር ይሆን?የኢትዮጵያ እና የሱዳን መንግስታት ስል ድንበር ስምምነት፣የጋራ ስለሆነ ደህነነትና ጥበቃ፣ህገወጥ የሆነ የሰዎች ዝውዉርን ስለመግታት፣የኤለክትሪክ ሐይልን ስለመጋራት፣የአባይን ግድብን አስመልክቶ ስለሚደረጉ ዉይይቶች ብቻ ነዉ እየገለጹ ያሉት።

ሰሞነኛ ጉዳዮችን በወፍ በረር አንቀጾች ስንቃኛቸው


ይሄይስ አእምሮ (ከአዲስ አበባ)
(yiheyisaemro@gmail.com)

መግቢያ
“እግዚአብሔር የሚጠላቸው ስድስት ነገሮች አሉ፤ እንዲያውም እርሱ የሚጸየፋቸው ሰባት ናቸው፤ እነርሱም፡- ‹በንቀት የሚመለከት ዐይን፤ ሐሰት የሚናገር ምላስ፤ ንጹሖች ሰዎችን የሚገድሉ እጆች፤ ክፉ አሳብ የሚያፈልቅ አእምሮ፤ ወደ ክፋት ለመሮጥ የሚቸኩሉ እግሮች፤ በውሸት ላይ ውሸት እየጨመረ የሚናገር ምሥክር፤ በወዳጆች መካከል ጠብ የሚያነሣሣ ሰው› ናቸው፡፡” ምሳሌ 6፣ 16 – 19
ከአፍ ከወጣ አፋፍ ነው
አለምነው መኮነን የተባለው የወያኔ እንደራሴ በአማሮቹ ሀገር እምብርት ዋና ከተማ ባሕር ዳር ላይ በዝግ ስብሰባ ተቀምጦ በወሻከተው ነገርና መዘዙ ሳቢያ ብዙ እየሰማን ነው፡፡ ሰውዬው ጅል መሆን አለበት – አለዚያም ወፈፌ፤ ከአፍ የወጣ ነገር የትም ሊደርስ እንደሚችል ካጣው እውነተኛ በሽተኛ ነው፤ ከተራበ ለጠገበ አዝናለሁ መባሉ ይህን ዓይነት ዕብሪት ለመግለጥ ነው፡፡ ወያኔዎች ሊታወሱም ሆነ ሊረሱ የማይፈልጉ ዕንቆቅልሾች መሆናቸውን በሰሞኑ ድርጊታቸው መገንዘብ ይቻላል፡፡ በአሁኑ ኢትዮጵያዊ መቼት አማራን መሳደብ ትርጉም የሌለውና የደረቀ ወንዝን እንደመሻገር የሞተ ፈረስን እንደመጋለብ ያለ ዶንኪሾታዊ የጀብደኝነት ፉከራና ሽለላ  ነው፤ ስንትና ስንት ወቅታዊ ጠላት እያለ አርፎ የተቀመጠን ምሥኪን ወገን በጠላትነት ፈርጆ በተደጋጋሚ ኅሊናን ለማቁሰል መጣደፍ የዕድሜ ማራዘሚያ ክኒንን በከንቱ ውጦ እንደመጨረስ ያለ ሞኝነት ይመስለኛል፤ ወያኔዎች ሆይ! ያደርሳችኋል ግዴላችሁም – በኔ ይሁንባችሁ – እስከዚህን ቅጥ አምባራችሁ አይጥፋ፤ ጥጋባችሁን እንደምንም ቻል ለማድረግ ሞክሩ – የዱባ ጥጋብ ካለስንቅ እንደሚያዘምት እናንተም ይህች በሸፍጠኝነትና በሁለገብ ዓለማቀፋዊ ሻጥር የያዛችኋት አዱኛና የመንግሥት ሥልጣን ናላችሁን አዙራችሁ የምትሆኑትን አጥታችኋልና ፈጣሪ የምትቋምጡለትን ዕብሪት አስተንፋሽ እስኪልክላችሁ ባልተቆጠበ ትግስት ተጠባበቁ፤ ፈጣሪ “የነገሩትን የማይረሳ፣ የለመኑትን የማይነሳ” ቸር አምላክ ነውና የምትፈልጉትን የጦር ድግስ ይነፍገናል ብላችሁ ሃሳብ አይግባችሁ፡፡ የዱሮ ጦር ሠራዊት እንደናንተ ጥጋብ ሲወጥረው  ጦር አምጪ እያለ መሬትን ይደበድብ ነበር አሉ፡፡ በምታምኑበት ይሁንባችሁና አማራውን ተውት – ብሶቱን በእህህኣዊ ዕንባው ወደላይና ወደሚመለከተው አካል ያስተላልፍ፡፡ ጓድ አለምነው መኮንን ስማኝ- ቴፕ ሪከርደር እንኳን  የሰጡትን ላለመቀበል አንዳንዴ ያንገራግራል – ችንጊያው ሲጎትት፣ አልማዙ ሲበላ ወይንም ባትሪው ሲያልቅ፡፡ አንተ ግን በአማራው መሀል ተቀምጠህ በጌታዋ እንደተማመነችዋ በግ ቀን በጣለው ሕዝብ ላይ እንዳንዳች የሚቀረና ቅርሻትህን ለቀቅኽው፡፡ ግዴለም፡፡ ግፍን ያላሳለፈ፣ ጡርን ያልሰማ ወደ ደህና ቀን አይወጣምና ይህም ለበጎ ነው፡፡ ለአንተ ግን “መጥኖ መደቆስ ቀድሞ ነበር” ማለትን እወዳለሁ፡፡ አሁን ማጣፊያው ሲያጥርብህና ንግግርህን በማሳመር ሰውን ለማስገልፈጥ እንደዋዛ በወረወርከው ስድብ ሕዝባዊ የተቃውሞ ውርጅብኝ ሲበራከትብህ “የአራት ቀናት ንግግር በኮምፒውተር ተቆርጦ ተቀጥሎ ነው እንጂ የወጣሁበትን ሕዝብ እንዴት ልሳደብ እችላለሁ?” ብለህ በዐይኔን ግምባር ያ’ርገው መሃላ ብትሸመጥጥ የእናቴ መቀነት አሰናከለኝ ዓይነት የተበላ ዕቁብ መሆኑን ልትዘነጋ አይገባም፡፡ አንተ አማራን የተሳደብከው የተማመንከውን ተማምነህ ምናልባትም በተማመከው ኃይል ታዝዘህ ነው ብንል አንሳሳትም፤ የወደፊቱን እንጃህ እንጂ ለአሁኑ ከሽልማት በስተቀር የሚገጥምህ ክፉ ነገር እንደሌለ በደኖንና ዐርባጉጉን በማስታወስ ብቻ በሚገባ እንረዳለን፡፡ ዱባ ካላበደ መቼም ቅል አይጥልም፡፡ አማራ ነኝ የምትለው አለምነውም ሆንክ የሌላ ብሔር አባል ወይም ነጭም ይሁን ጥቁር የማንኛውም የሌላ ሀገር ዜጋ  አንድን ሕዝብ ለመሳደብ ምንም ዓይነት አመክንዮ የለውም፡፡ ቅጽሎች የተፈጠሩት ይህን ዓይነት አወዛጋቢ ሁኔታ ለማስወገድ ነው፡፡ አንተ የትግራይን ብሔር በጅምላ ተሳድበህ ቢሆን ኖሮ በአሁኑ ወቅት ሥጋህ ለጅብ ነፍህን ለጀሃነብ ሰጥተው፤ህ በሣምንታት ውስጥ ተረስተህ ነበር – ምሳሌ ነው – የትግራይ ሕዝብ እንደሕዝብ ባለመሰደቡ የሚቆጨው ሰው ካለ የሸንጎ ፍርድ የሚገባው የመጨረሻ ወንጀለኛ ሰው መሆኑን አጥቼው አይደለም፤ ሕዝብ በደግ እንጂ በክፉ ሊነሣ የሚገባው ኑባሬ አይደለም፤ አልተለመደምም፡፡ ነገር ግን ዘረኛው የወያኔ መንግሥት አማራውን ራሱ ተሳድቦ ስላላረካው ራሱ በሾመውና በአማራነት በፈረጀው ‹ባለሥልጣን› አማራን ሊያሰድበው ወደደ፡፡ ይህ ደግሞ የግፍ ግፍ ነው፡፡ ፈረንጆቹ “adding an insult to injury” እንደሚሉት ነው፡፡ ስብሃት ነጋ፣ ሣሞራ(ሙሃመድ) የኑስና መለስ ዜናዊ አማራን በመሳደብ የሚወዳደራቸው የለም – እስኪሰለቻቸው እየሰደቡ አሰድበውታል፤ ግን ስድብ አይጣበቅ ሆኖ ተቸገሩ፡፡ እንግዲህ የነሱ ስድብና የነሱ የዘመናት ጭፍጨፋ ሊያረካቸው አልቻለም ማለት ነው፡፡ ያሳዝኑኛል፡፡ አንድን ጠላቴ ነው የምትለውን ሰው አንተው ራስህ በጥፍርህም፣ በጥርስህም፣ በጠበንጃህም፣ … በቻልከው ሁሉ ቦጫጭቀኸው እየተንጠራወዘ አልሞትልህ ሲል በከፊልም ይሁን በሙሉ በ“ደም” ይዛመደዋል የምትለውን ሰው ፈልገህ በእጅ አዙር ለማጥቃት መሞከር ከሰይጣናዊነት ሌላ ምንም ሊባል አይችልም፡፡
ስም ይቀድሞ ለነገር
ኃይለመድኅን አበራ ተገኝ ታሪካዊ ሥራ ሠራ፡፡ ወርቃማ ሥራ ሺህ ጊዜ በማንም ቢደጋገም ሊሰለች አይገባም፡፡ እናም እኔም እላለሁ – ይህ ወጣት ብዙ ክፍለ ጦሮች ሊሠሩት የሚከብዳቸውን ታላቅ ጀብድ ሠርቷል – ልክ እንዳገሩ ልጅ እንደአበበ ገላው (‹ሽጉጥ አልታጠቀ መትረየስ የለው፤ ባንደበቱ ገዳይ አበበ ገላው› ተብሎ የተገጠመውም እዚያችው ሥርፋ ለበቀለው ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡) የዚህ ረዳት አብራሪ ስም ራሱ ተናጋሪ ነው፡፡ “የመድሓኒት ኃይል የነጻነትን ቀንዲል ሊያበራልን ተገኘ” እንደማለት ነው – የት ተገኘ? ከዚያችው ጉደኛ ባህር ዳር ከተማ፡፡  ባህር ዳር መድሓኒትም መርዝም የሚበቅልባት ቦታ ሆነች፡፡ መርዝ ያልኩት አለምነውን የመሰለ ሰው እዚያችው ከተማ ውስጥ የተናገረውን ስለተናገረ ነው – እዚያው እከተማው መሀል ይሁን ዳር ላይ ተጎልቶ በማን አለብኝነት አማራን ዘለፈ፤ የምን መዝለፍ ብቻ በጋብቻ ከልክል ስድብ ዶቃ ማሰሪያው ድረስ አስታጠቀው እንጂ! አሁን በሞቴ ከሰደበኝ ስድቤን አምጥቶ የነገረኝ እንዳትሉኝ እንጂ የ“ልጋጋምንና የለሃጫምን ልጅ ማን ያገባል? ከሰባቱ ልጆቼ አራቱ ጉድ ፈላባቸው! ሦስቱስ አለምነውን ቀድመው በማግባታቸው ተገልግለዋል፡፡ ለነገሩ አለምነው ብቻ አይደለም አማሮችን ለማዋረድ ወያዎች መቀመጫ ውስጥ ሄዶ የተወተፈ፤ እነገነት ዘውዴን፣ እነክፍሌ ወዳጆንና ሌሎች ሆዳሞችን በአለምነው ቅርጫት ልንከታቸው እንችላለን፡፡ የእናት ሆድ ዥንጉርጉር ነው፡፡ [“ትልቅ ነበርን ፤ ትልቅም እንሆናለን” - አሁን ከሬዲዮ ሰማኋት፤ ደስ የምትለኝ አባባል!]
ፆመ ኹዳዴ ተጀመረ!
ኹዳዴን የምትፆሙ በተለይ የኦርቶዶክስና የካቶሊክ እምነት ተከታዮች እንኳን ለፆም መያዣው አደረሳችሁ (አብዛኞቹ ካቶሊካውያን የሚፆሙት ክርስቶስ የፆማቸውን ዐርባ ቀናት በመሆኑ የነሱ ፆም መያዣ ገና አልገባም፤ ብሎም ቢሆን እንደባህል ወስደው የኦርቶዶክስን የፆም ይትበሃል የሚከተሉም አሉ – 55 ቀናትን የሚፆሙ – ለቀድሞ የእሥራኤል ንጉሥ  ኃጢኣት ጭምር መሆኑ ነው)፡፡ ፆሙን በሰላም አጠናቅቃችሁ የጌታችንን የመድሓኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ብርሃነ ትንሣኤ ለማየት እንዲያበቃችሁ የኅያው እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ይሁንልን፡፡ ፆምን መፆም ጥሩ ነው፡፡ ጸሎት መጸለይም ጥሩ ነው፡፡ መመጽወት ጥሩ ነው፡፡ መቀደስና እግዚአብሔርን በከበሮና በጸናጽል፣ በእምቢል፣ በበገናና በማሲንቆ ማወደስም ጥሩ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናትን ማነጽና ማሳነጽ ጥሩ ነው፤ እነዚህና መሰል ደጋግ ሃይማኖታዊ ተግባራት ከፈጣሪ ያገናኛሉ – የፋክስ መስመሮች ናቸው፤ እንዴት መከናወን እንደሚገባቸው መረዳት ግን ይገባል፡፡ አለበለዚያ ለቅጽፈት ይዳርጋሉ ብሎ ማስፈራራቱ ከዘመኑ ሃይማኖታዊ ዕውቀት አንጻር ተጠየቃዊ መከራከሪያ ባይሆንም በግንጥል ጌጥነታቸው ግን ነውረኝነታቸውን መጥቀስ ይቻላል፤ ግንጥል ጌጥ አሣፋሪ ነው፡፡ ለሁለት ጌቶች መገዛትም እንዲሁ፡፡ የሚታየኝን እናገራለሁና ለመቆጣት ያቆበቆባችሁ አደብ ግዙ፡፡ ደግሞም እውነትን ተጋፍታችሁ የትም አትደርሱም፡፡ ይህ ጉዳይ ሁለት አንቀጾች ሊሆንብኝ ነው መሰለኝ፡፡
ከገዳይና ዘራፊ መንግሥት ጋር መቀመጫዋን ገጥማ (ወንበር ለማለት አይደለም) አብራና ተባብራ ሕዝቧን የምታስፈጅ ቤተ ክርስቲያን ጸሎትና ምህላዋ ከዳመና በላይ ይቅርና ከዛፍና ከቤት ጣሪያ በላይም አልፎ አይሄድም – ይህን ለማለት ጉዝጓዜ መጽሐፍ ቅዱሱ ስለሆነ ማንም ያንብበውና ይረዳው፤ የጊዜውን መድረስም በእግረ መንገድ ይገንዘብ፡፡ ቀን ከእግዚአብሔር መንገድ ወጥቶ እንደልቡ ሲፏንንና በየእንትን ቤቱ ሲፋልል የሚውል ካህንና ደብተራ ሌሊት በቤተ መቅደስና በቅኔ ማኅሌት በያሬዳዊ ዜማና ወረብ ቃለ እግዚአብሔርን ማሽር ሲያቀልጥ ቢያድር የክርስቶስን አነጋገር ልዋስና – እውነት እውነት እላችኋለሁ አንድም ጽድቅ የለም፤ ልፋታቸው “የከንቱ ከንቱና ንፋስንም እንደመከተል ነው”፡፡ እንዲያውም ካህናትና ጳጳሳት በእግዚአብሔር ላይ እንደሚያሳዩት አመፃና የትዕቢት ጉዞ ቢሆን ኖሮ እስካሁንም ሁላችንም አልቀን ነበር፤ አንዳችንም ባልተረፍን፡፡ ነገር ግን የሚቀልዱበት እግዚአብሔር ትግስቱና የቸርነቱ ብዛት ገደብ የሌለው በመሆኑ ይሄውና “እስካሁን በአማርኛ በመቀደሴ ይጸጽተኛል፤ ከኢሕአዴግ ጋር መጪው ዘመን ብሩኅ ነው፤ ጭቃ ሕዝብ፤ “shoot him!”፣ የህዳሴውን ግድብ ያልደገፈ ኢትዮጵያዊነቱን በራሱ ገፍፎ ጥሏል፤ …” የሚሉ “ብፁኣን”  አባቶችና የነሱን ስም በየቅዳሤው እያወሱ የሚቀድሱ ደናቁርት ቀሣውስት እያሉን በመቻያው ችሎናል፤ አስችሎንማል፡፡ አንድም የበቃ ካህንና የሃይማኖት መሪ በሌለን ሁኔታ ወጉ አይቀርም “ፆም ሊፆም” በቀደም ለት ተያዘ፡፡ ሊያውም ከፋሲካው በበለጠ የሚፆመውም የማይፆመውም ለነፍሱ ሳይሆን ለሥጋው በሚንሰፈሰፍበት የገበያ ግርግር፡፡ ሃይማኖታችን ለሆድና ስለሆድ ወደተለወጠባት የልማድ እምነት ስትቀየር እንደማየት መጥፎ አጋጣሚ የለም፡፡ በኪነ ጥበቡ ይቅር ይበለን፡፡ አንድ አጭር ማሳሰቢያ አለኝ፡- ጆሮ ያላችሁ የማንኛውም ሃይማኖት አባቶች አዳምጡኝ፤  ይበልጡን ለገንዘብና ለተደላደለ ቅንጦተኛ ሕይወት ስትሉ ከእውነቱ መንገድ ወጥታችሁ ለሥጋችሁ ማደራችሁን በግልጥ የምታሳዩበትና የምታሾፉበት ፈጣሪ በራሱ ጊዜ የሚፈልገውን የማስተካከያ እርምጃ መውሰዱ የሚጠበቅና የማይቀርም ሆኖ አሁን ለጊዜው ግን እንዲህ አድርጉ፡- አለሰዓት የምታስጮኹትን ዘመናዊ የድምፅ ማጉያ ነገ ዛሬ ሳትሉ ልጓም አብጁለት፡፡ የታመመ አለ፤ በሥራ የደከመ አለ፤ የአንድኛችሁን ጩኸት ሌላኛችሁ በማረፊያና መተኛ ሰዓት ይቅርና በመደነቋቆሪያው የቀኑ ጊዜም መስማት የማይፈልግ አለ፤ ልክ መሆን አለመሆኑ የራሱ ጉዳይ ሆኖ በምንም ነገር የማያምን ግን በቤቱ በሰላም ተኝቶ ማደር የሚገባው የአንዲት ሀገር እኩል ዜጋ አለ፤ በቤተ እምነቱ እንጂ ቤቱ ድረስ በሚመጣ ሰዓት ያልተገደበበት ረብሻና ሁከት በጸሎት ስም መታወክ የማይፈልግ አለ፡፡ ይህ ሁሉ ከጉዳይ መጣፍ አለበት፡፡ ሁሉም ነገር በሥርዓት መከናወን ይገባዋል፡፡ ባህልንና ሃይማኖትን ተመርኩዞ ዜጎችን ማስጨነቅ ተገቢ አይደለም፤ ፈጣሪም የሚወድላችሁ እንዳይመስላችሁ፡፡ ለርሱ እንዲያውም የአእዋፋትና የዕፅዋት የተፈጥሮ ድምፅና ውዝዋዜ፣ የነፋሳትና የደመናት ዳንኪራና ንፅውፅውታ ከእናንተ በተሻለ የውዳሤና አምልኮት መባዎች ናቸው፤ የነሱ ደረቅና የለበጣ አይደለም – እውነት ነው፡፡ ደግሞም መጽሐፉ “የቄሣርን ለቄሣር፣ የእግዜርን ለእግዜር” ስለሚል በደረቅ ሌሊት ከፍተኛ ድምፅ በሚያወጣ ማይክሮፎን ሀገርን ማናወጥ መብት አይደለም – እንደዚያ አስፈላጊ ከሆነ ከከተማዎች ውጪ በሚገኙ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያን ሕዝብን በጥቅል ሳያውኩ ማከናወን ይቻላል፡፡ በዱሮ ጊዜ ቤተ ክርስቲያናት ሲሠሩ ከመኖሪያ አካባቢዎች ራቅ ይሉ ነበር፤ እንዲያም ሆኖ ኤሌክትሪካዊ ማጉሊያዎች ስላልነበሩ እንደዛሬው ሁከት አልነበረም፡፡ ስለጸሎት ምንነትና ርዝማኔም የክርስቶስን አስተምህሮዎች ደግማችሁ አጢኑ፡፡ እውነቴን ነው የምለው – አሁን አሁን በፉክክርና በደራ በየሽርንቁላው እንደጠላ ቤት በሚቀለሱ የእምነት ቤቶች ሕዝብ እየተረበሸ ነው፤ ብሶቱን ስለማይናገርና ስለሚያፍርም እንጂ ሕዝቡ በዚህም እየተማረረ ከመጣ ሰነባብቷል፤ ለስንቱስ ቀን ጠብቀንለት ይዘለቃል? ከቤተክርስቲያን ግድግዳ በጥቂት ሣንቲ ሜትሮች ወይም በጣት የሚቆጠሩ ሜትሮች ርቀት ላይ የወንደላጤዎች መኝታ ቤት ወይም የተከራይ ሴተኛ አዳሪዎች ክፍል ወይም የጭፈራ ቤት መኖሩን ታውቃላችሁ? ብርሃንና ጨለማ ምን ኅብረት አላቸው? ችግር አለ ምዕመናን፡፡ ብዙ ችግር አለ፡፡ የቋራው መይሳው ካሣ በዳግም ልደታዊ የሂንዱይዝም እምነት መሠረት ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ ተብሎ እስኪመጣ አንጠብቅ፡፡ ተግባራችን መስታውታችን ይሁነንና ራሳችንን በመመርመር  እንደእግዚአብሔር ትዕዛዛት እንጂ እንደሰይጣን ደባ አንጓዝ፡፡ ልበ ወኩልያትን የሚመረምር የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣ አንድ ካህን በሥውርም ይሁን በግልጥ ምን እየሠራ የእምነቱ ትውፊታዊ መገለጫ የሆነውን ጽላት ወይም ታቦት እንደሚሸከምና ቃለ ምዕዳን እንደሚሰጥ ፈጣሪ ሳያውቅ ይቀራል ብሎ የሚያስብ ጅላጅል ቄስ ካለ ከሕዝቡ ንቃተ ኅሊና በእጅጉ የወረደ የንቃት ደረጃ ላይ ይገኛል ማለት ነውና ሣይረፍድበት ራሱን ይፈትሽ – አብረን ስለምንኖር ሙሉ በሙሉ እንተዋወቃለንና … ፡፡ (“ውርድ ከራሴ፤ እኔ የለሁበትም…” እያለች የምትዘፍን ሴት አቀንቃኝ ከአንዱ ኤፍኤም በአሁኒቷ ቅጽበት ትሰማኛለች፡፡) ሕዝቡን አደንቁራ ያስቀረች ሃይማኖታችን መሠረቷን ሳትለቅ ልትታደስ ይገባታል፤ ይህ የሚሆነው ከትንሽ ጀምሮ ነውና እዚህ ላይ የጠቀስኩትን ሃሳብ ልብ የሚል ልብ ይበል፡፡ የተለመደ ቅጥልጣይ ሰው ላይ መለጠፍ የማይሠራባቸው ሁኔታዎች መኖራቸውንም ልብ እንበል፡፡ እውነት ብትመር ብትጎመዝዝም እንደምንም ማወራረድ ነው፡፡ አካሄዳችን የተበለሻሸ ነው፡፡ ይታረም፡፡ በዚያ ላይ “ባለቤቱን  ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ” እንዲሉ ሆኖ ከቄሶቹ ባልተናነሰ በፈጣሪ ላይ የሚዘብቱት ወያኔዎች የማይፈርድባቸው መስሏቸው ከመነሻቸው ጀምረው ሃይማኖትን ለማጥፋት ምን ምን እያደረጉ እንደመጡ የምናውቀው ነው፡፡ ይሄውና በነሱና በተባባሪ የሃይማኖት አባቶቻቸውና ጭፍሮቻቸው የበከተ ዲያብሎሣዊ አመራር የተነሣ ዛሬ ዛሬ በአሥር ሚሊዮን የሚቆጠሩ ምዕመናን ግራ እየገባቸውና መዳን በሃይኖማኖት መለዋወጥ እየመሰላቸው ወደሌሎች የሃይማኖት ዘርፎች እየነጎዱ ነው፡፡ ይንጎዱ፡፡ ሥራቸው ያወጣቸዋል፡፡ እዚያም ቤት እሳት መኖሩን ያላወቁ ማለትም ከሸሹበት ቤት የጠሉት እንከን ወይንም ገመና በሚሸሹበት ቤት የሌለ የሚመስላቸው የዋሃን በሚደርስባቸው ሥነ ልቦናዊና አእምሯዊ እንግልት ለጊዜው ማዘናችን ባይቀርም ሁሉም የሥራውን ማግኘቱ የነበረና ያለ ነውና በዚያ እንጽናናለን፡፡ የሃይማኖተኞች ጠርዝ የለቀቀ ውስልትናና ሃሳዊነት ከዓለማውያን ሶዶም ወገሞራዊ ብልግና ጋር ሲጋጠሙ ለሚፈጠረው አርማጌዴዎናዊ ትዕይንት ዝግጁ ሆነን እንድንጠብቅ  በዚህ አጋጣሚ የጋራ ግብዣ ማስተላለፍ እፈልጋለሁ፡፡ ግን ዛሬ ምን ነካኝ? የጤና ነው ብላችሁ ነው? አሃ፣ በቃ! እስከመቼ?
በሦስት ዓመታት ውስጥ ከ20 እስከ 38 ሚሊዮን ብር ወጪ
እውነተኞቹም ይሁኑ የተጋቦት ወያኔዎች ራሳቸው መርጠው፣ ራሳቸው ሾመውና ራሳቸው መርዘው ለህመም የዳረጉትን የአንድ ክልል ‹ፕሬዚዳንት› ለማሳከም ብዙ ሚሊዮን ብር ከዚህ ምስኪን ሕዝብ ደረቁቻ ካዝና መመዝበራቸውን ሰማን – በአነስተኛ ግምት 20 ሚሊዮን ብር – በከፍተኛ ግምት 38 ሚሊዮን ብር፡፡ የኢትዮጵያ ካዝና መቼም ለዜጎቹ አይሆንም እንጂ ለባለሥልጣናትና ባለሥልጣናት ለሚመሳጠሯቸው የውጭና የሀገር ውስጥ የሥራ ተቋራጮች የወርቅ ጎተራ ነው፡፡ የሀገሬ ባላገር በባዶ እግሩ እየሄደ፣ ጨርቁ አልቆ ራቁቱን በብርድ ቸነፈር እየተሰቃዬ አፍንጫውን ተይዞ ከሚከፍለው ግብር ሰባት ሚሊዮን ብር የሚገዛ መኪና ለባለሥልጣን የሚሰጥባት ሀገር ሆናለች አሉ – ኢትዮጵያ፤ በየመሥሪያ ቤቱ አላግባብ የሚባክነው ገንዘብ፣ ሥራው ከመጠናቀቁና ርክክብ ከመፈጸሙ በፊት የሚፍረከረከው የፈረደበት የመንግሥት መንገድና ሕንጻና በቀላል ብልሽት የሚጣለው ተሸከርካሪና ሌላ ንብረትማ አይነሣ፡፡ እንደመጥፎ ዕድል ሆኖ ሀገራችን ብዙ ታማሚ ባለሥልጣናትን በውድ ወጪ ሊያውም በውጪ ሀገራት በማስታመምም ትታወቃለች፡፡ ጥቂት አብነቶችን ለመጥቀስ ያህል- መለስ ዜናዊ፣ ግርማ ወ/ጊዮርጊስ፣ መሀመድ የኑስ፣ አለማየሁ አቶምሳ፣ ሙላቱ ተሸመ፣ ሥዩም መስፍን እና ሌሎችም ሙትና ቁስለኞች ሁሉ ሞሰብ ገልባጮች ናቸው፡፡ ባለሥልጣኖቻችን ኢትዮጵያቸውን በዕድገትና ሥልጣኔ ወደላይ ስላስፈነጠሯት ለራስ ምታትና ለጉንፋንም ሳይቀር አውሮፕላናቸውን እያስነሱ ከቅርብ ጎረቤት ኬንያ ጀምረው ደቡብ አፍርሪካ፣ ሳዑዲና ታይላንድ እንዲሁም አውሮፓና አሜሪከ ለህክምና ይሄዳሉ፤ ሲፈልጉም ለመዝናናትና ከበሽታቸው ለማገገምም ሊሄዱ ይችላሉ፡፡ እኛ ደግሞ በወባና በርሀብ፣ በስደትና በሙስና እናልቃለን – ሲያስተውሉት ግን በርግጥም ጉደኛ ዘመን ነው እባካችሁን! በነገራችን ላይ ያቺ ዮዲት ጉዲት አዜብ የሚሏት መበለት መቼ ነው የ“ሀዘን” ልብሷን የምታወልቀው? ሀዘኑ ጎዳት አይደል? ቅድም በአንድ ስብሰባ ላይ እኮ ሃሳብ ልትሰጥ ግራ እጇን ስታንከረፍፍ አይቻት ነው – ሳያት ብቻ እንዴት ደሜ እንደሚንተከተክ አትጠይቁኝ፡፡ ባለራዕዩ ሰውዬ በአጽሙ ሀገር መግዛቱን እስኪያቆም ድረስ የምትቀጥል ይመስለኛል፡፡ ሌላውማ ዱሮውንስ ምኑ ቀረባትና! ወይ የሀፍረታችን ምንጭ ብዛት!
ኡክሬን በ3 ወር የሕዝብ አመፅ ድል በድል ሆነች
የምሥራች! ሕዝብ ማለት እንዲህ ነው፡፡ ኡክሬናውያን በሦስት ወር አመፅ በአሥር ዓመት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ለድል መብቃታቸውን እየሰማን ነው፡፡ እልኸኞችና በጣም ጀግኖች ናቸው፡፡ ካለመስዋዕትነት ድል ባለመኖሩ ወደ መቶ የሚጠጉ ዜጎች(88) በዚህ በሰሞኑ አመፅ ተሰውተዋል፡፡ ጽናት ማለት እንዲህ ነው፡፡ የኛ ግን እንደተጀመረ ሳያልቅ ቁጭ ብሎ አለ፡፡ ግን እሱ ባለው ጊዜ ማለቁ አይቀርም፡፡ ያም ማለቂያ ጊዜ የቀረበ ይመስለኛል፡፡ ግን ግን … በዚህስ ላይ ለብቻው ትንሽ እናውራበት …
አንድ ሕዝብ ለተራዘመ ጭቆና የሚጋለጠው ለምንድን ነው?
በእኔ ዕይታ ሀገር በቀል አምባገነን ገዢዎች በሁለት ይከፈላሉ፡- በመጠኑ ማሰብ የሚችሉ ሀገር ወዳድ አምባገነኖችና ከከርሳቸው ውጪ ጭራሽ ማሰብ የማይችሉ ድፍን ቅል አምባገነኖች፤ (እነዚህኞቹ ከድፍን ቅልነታቸውና ከሆዳምነታቸው በተጨማሪ የውጪ ጠላትን ተልእኮ አንግበው ሀገርን ለማፍረስ የሚጥሩ መሠሪዎች ናቸው)፡፡ ሁለቱን በደርግና በወያኔ ልንመስላቸው እንችላለን፡፡ በጭካኔ ረገድ እምብዝም አይለያዩም፡፡ አንዳቸውን የሌላኛቸው ግልባጭ አድርጎ መውሰድ ይቻላል፡፡ በአገዛዝ ሥልት ግን ሰማይና መሬት ናቸው፡፡ ስለደርግ ማውራቱ ለአሁኑ አይጠቅመንም – በወደቀ ላይ ምሣር ማብዛት ለአሁኑ ችግር መፍትሔ አይሆንም፡፡ ወያኔ ክፉ ሽንት ነው፡፡ ወያኔ የክፉ ሽንት ውላጅ ነው፡፡ ቀደምት ጠላቶቻችን በሃይማኖታችን ሠርገው ገብተው ወሩን ሙሉ በዓል፣ ዓመቱን ሙሉ ፆም አፅዋም አድርገው ለ“ንጉሥ አይከሰስ ሰማይ አይታረስ” ተረት እንደዳረጉንና በማይምነት ጥቁር መጋረጃ ጀቡነው ለማስቀረት እንደሞከሩት ሁሉ ወያኔም በትውልድ ገዳይነቱ የሚታወቀውን የትምህርት ሥርዓት ከዘረጋ ወዲህ እንደከብት ለሆዱ የሚጨነቅ ትውልድ እንጂ ለሀገሩና ለኅሊናዊ ዕድገቱ የሚተጋ ዜጋ ሊፈጠር አልቻለም – በአብዛኛው፡፡ አንድ ሕዝብ ደግሞ በመንፈሣዊ ሕይወቱ ማለትም በአእምሯዊ ዕውቀትና በንቃተ ኅሊና የግንዛቤ ምጥቀቱ ወደፊት ካልተራመደ በስተቀር ከዚህም ባለፈ ቢያንስ የነበረውን እንኳን ጠብቆ መቆየት ካልቻለ ለገዢዎች ምቹ ነው፤ ይህ ዓይነቱ ማኅበረሰባዊ መደላድል እንዲፈጠር ደግሞ ጨቋኞች አጥብቀው ይሠራሉ፤ ከጓደኞቿ ተለይታ የምትወጣ ማሽላ አንድም ለወፍ አንድም ለወንጭፍ ሲሳይ እንደመሆኗ ሀገራቸውን የሚወዱና በትምህርት የላቁ ጥቂት ዜጎች ቢኖሩም አንድም ለሞት አንድም ለእሥራት አንድም ለስደት አንድም ለዕብደትና አሊያም ለአንገት መድፋት እየተጋለጡ ሀገር እንደግመል ሽንት የኋሊት ቀረች፡፡ አምባገነኖች ለኅልውናቸው የሚጠቅሙ ሁሉም የክፋት ሰበዞች እንዲለመልሙ ይጥራሉ፡፡ ከነዚህም አንዱ ዘረኝነት ነው፡፡ ዘረኝነት የማይምነት ውጤት ነው፤ ጦጣ ከጦጣ ጋር፣ ነብር ከነብር ጋር፣ ፍየል ከፍየል ጋር … መስተጋብር መፍጠራቸው ተፈጥሯዊ ነው፡፡ በዚህ ስሌት ሰው ከሰው ጋር ኅብረት መፍጠሩ የሚጠበቅ ነው – አንድ ዘር በመሆኑ፡፡ ነገር ግን ሰው ከሰው ጋር መተባበሩና መፈቃቀዱ ቢከብድ ቢያንስ በጥቁርና በነጭ ወይም በቢጫ፣ በሀገርና በክልል ወይም በአህጉር ደረጃ በሚታዩ ቅርበቶች መተባበር ቢኖር የሚታገሱት መለያየት ነው – ከእንስሳት እንደወረስነው ደመነፍሳዊ መለያየት ቆጥረን ማለት ነው፡፡ ከዚህ አልፎ ግን በኢትዮጵያ እንደምናየው የአንድን ዘር የበላይነት በሌሎች ላይ በግልጥ በሚታይ ተግባራዊነት ዐውጆ መንቀሳቀስ ምን ሊባል እንደሚችል ማሰቡ ራሱ ለራስ ምታት ይዳርጋል፡፡ ይህ ዓይነቱ ነገር ታዲያ የፍጹማዊ ማይምነት ውጤት መሆኑ ሊዘነጋ አይገባውም፡፡ በአንድ ሕዝብ መሀል ጤናማና ተፈጥሯዊ የሚባሉ ልዩነቶች አሉ፤ እነዚያ ጠብና ጭቅጭቅ አያመጡም፡፡ ከመንገድ የወጡ ልዩነቶች መረን በለቀቀ ሁኔታ ከተንሠራፉ ግን የአሁኑን የመሰለ ማኅበራዊ ቀውስ በማስከተል የሕዝብንና የሀገርን ኅልውና ይፈታተናነሉ፡፡ ይቅርታ ሁለተኛ አንቀጽ መድገሜ ነው፡፡
ወያኔ ዘመናዊና ጥራት ያለው ትምህርት በኢትዮጵያ እንዳይኖር የሚጥረው ለምን እንደሆነ እናውቃለን፡፡ በተማረና በሠለጠነ ማኅበረሰብ ውስጥ የወያኔን የመሰሉ ማስጠሎ የመንግሥት ሥርዓቶች ለ23 ዓመታት አይደለም ለአንድ ዓመትም ሊቆዩ አይችሉም፡፡ ጉዳዩ የሕዝብ ብዛት አይደለም፡፡ በአንድ ሰው ወይም በአንድ ቡድን ፍላጎት ለመመራት(ለመገዛት) ምቹ ሆኖ የሚገኝ 85 ሚሊዮን ሕዝብ በአንዲት ቀጭን ለበቅ ወይም በቁጣ ድምፅ ብቻ እንደሚነዳ የሃምሳና ስልሳ ከብቶች መንጋን ያህል አያስቸግርም፤ ይህን ዘግኛኝ ሀገራዊ ገጽታ እውን ለማድረግ ደግሞ የአሁኑ ብቻ ሣይሆን የቀደሙት መንግሥታትም የበኩላቸውን ጥረት አድርገዋል፡፡ ወያኔ በተመቻቸለት ጥርጊያ ዘው ብሎ ድንገት ገባና በማን አባት ገደል ገባ የእረኞች ጥንታዊ የማጣያ ዘዴ በትምህርት ያልገፋውን ሕዝብ በማናቆር መርዘኛ ሥርዓቱን ዘረጋ፡፡ ጨካኝ አምባገነናዊ ሥርዓት በመዘርጋት ረገድ 1.3 ቢሊዮን የሚገመተው የቻይና ሕዝብ ዕጣም ከኛው ተመሳሳይ ነው – በኑሮ ተሽሎ መገኘቱ የነፃነትን ጣዕም እንደሚያጣጥም ሊያስቆጥር አይችልም፤ እርግጥ ነው ቻይናውያን በአምባገነን ቻይናውን እንጂ እንደኛ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን በካዱ አጭበርባሪና ህግአልባ ማፊያዎች አይገዙም፡፡ የገዢዎች ዋና የሚጨነቁበት ነገር የአገዛዝ ዘዴን ማወቁ ላይ ነው፡፡ በተለይ ዴሞክራሲ በሌለባቸው ሀገራት መንግሥትና ሕዝብ ማለት ዐይጥና ድመት ማለት ናቸው፡፡ ዐይጦች ከድመት ጥቃት ለማምለጥ ሁልጊዜ ብልህና አስተዋይ መሆን አለባቸው፡፡ ድመት ለዐይጥ ምንም ዓይነት ምሕረት አታደርግም፡፡ ዐይጦች ችሮታና ምሕረትን ከድመት ከጠበቁ የዋህነት ነው፤ የብዛት ጉዳይ ከቁብ ሳይጣፍ፡፡ ድመት በሕይወት የያዘቻትን ዐይጥ ዐይኗን አጥፍታ እንዴት እንደምትጫወትባት አስታውሱ፤ ወያኔም ተቃዋሚዎችን በአጠገቡ አስቀምጦ በቅርብ እየተቆጣጠረ እንዴት እንደሚጫወትባቸውና በሀገሪቱ ዴሞክራሲ ያለ ለማስመሰልም እንዴት እንደሚጠቀምባቸው ልብ በሉ፡፡ በውጪ ያሉትንም ሰው እያሠረገ ሲቻል ለማጥፋት ሳይቻል ለመከፋፈልና ለማዳከም፣ የሕዝብ አለኝታና የብሶት መተንፈሻ የሆነውን ኢሳትንም ለማዘጋት የሚያደርገውን ጥረት ሁሉ አትርሱ፤ እንዳሻው ከሚፈነጭበት የሕዝብ ጫንቃ ላይ ሊያወርደው የሚሞክርን ኃይል ሁሉ ባለ በሌለ ዘዴና ጉልበት ማጥፋት የወያኔ ትልቁ ሥራ ነው – ሌላው ሁሉ ሁለተኛና ሦስተኛ ከፈለገም መቶኛ ነው፡፡ ከጭቆና ለመውጣት ሆ ብሎ የሚነሣ በአግባቡ የተማረና የሠለጠነ፣ ከአጉል ባህልና ከጎጂ ልማድ ነጻ የወጣ፣ ቀናነትን መከባበርንና ትህትናን የተላበሰ፣ በእውነተኛ የሃይማኖት አባቶች የሚመራ፣ ዘረኝነትንና አድልዖዊነትን የሚጠየፍ ማኅበረሰብ መፍጠር ከተቻለ ነጻነትና ዴሞክራሲ ለነዚህ ነገሮች እንደምርቃት ያህል በተፈጥሯቸው ወደሕዝባችን የኅሊናና የፖለቲካዎች ጓዳ የሚገቡ እንጂ ብዙ ትግልን የሚጠይቁ አይሆኑም፡፡ መማርና መሰልጠን ሲባል ደግሞ ለአንድ ወገን ብቻ የሚተው ሣይሆን ለሁሉም ነው፡፡ ሕዝቡ ዘመናዊ ከሆነ አመራሩም ዘመናዊ የመሆን ዕድሉ ከፍተኛ ነው – ያልዘሩት አይበቅልምና አሁን ሥልጣን ላይ ያለው ኃይል አብዛኞቻችንን እንደሚመስል ወይም እንደማይመስል ለማወቅ ትንሽ ራሳችንን የመፈተሸ ሥራ ማካሄድ ሳይኖርብን የሚቀር አይመስለኝም፡፡ አንድ ሕዝብ ከሚገባው በላይ ወይም በታች መሪ አያገኝም የሚባለውን ነባር አባባል መመርመርና ራሳችንን ከዚህ ነጥብ አኳያ ማስተካከል ይኖርብናል፡፡ እኛ ጥሩ ስንሆን ጥሩ መሪ ይኖረናል፤ እኛ መጥፎ ስንሆን ደግሞ መጥፎ መሪ ይገጥመናል፡፡ ፈረንጆቹ “what goes around comes around” የሚሉት “ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት በዳገት ይለግማል” ወይንም “አለባብሰው ቢያርሱ ባረም ይመለሱ” ለማለት ፈልገው ይመስለኛል፡፡ አዎ፣ እኛን እላይ ለማየት ከፈለግን የላዩን ወደኛው አምጥተን ከታችኛው ጋር ማስተያየትና ልዩነታችንን መገንዘብ ይጠበቅብናል፡፡ የላይኛው ከታች እንጂ ከላየ-ላይኛው ጽርሃ አርያም እንደማይወርድ ማወቅ አለብን፤ አራት ኪሎ የምትገቡት በሁኔታዎች አስገዳጅነትም በሉት በሌላ አንተና እርሷ ወይም እገሌና እንቶኔ እንጂ ከጨረቃ ወይም ከማርስ አዲስ ትውልድ ተፈጥሮ አይደለም…፡፡ ባልተማረ ሕዝብ ውስጥ አጋጣሚን እየተጠቀመ ወደሥልጣን የሚወጣው በአብዛኛው ብዙም ያልተማረው ቀጣፊና መልቲው ነው – ይህን ለብዙ ጊዜ አይተን በተግባር አረጋግጠናል፡፡ የቅርቦቹ ተፈሪ መኮንን፣ መንግሥቱ ኃ/ማርያምና ለገሠ ዜናዊ ዲ ኤን ኤያቸው ቢጠና ከሌላው ሕዝብ የሚለዩት የሚቃወሟቸውን ቀድመው በማጥፋት ድፍረትና ጭካኔ የተሞላበት አፋጣኝ እርምጃ በመውሰዳቸው እንዲሁም በሥልጣን ሽሚያ የሚጠረጥሯቸውን ጓደኞቻቸውንና የቤተሰባቸውን አባላት ሳይቀር ከጉያቸው እያወጡ እንደሰውነት ተባይ በጣቶቻቸው በመጨፍለቅ ምንም ዓይነት ሥጋት እንዳይኖርባቸው በማድረጋቸው እንጂ የክሮሞዞማቸው ቁጥር ከእኔና ከአንተ በልጦ ወይም በኢትዮጵያዊነታቸው እነሱ ተሽለው አይደለም፡፡ ይህን የአጭበርባሪዎች መንገድ እስከወዲያኛው የምንዘጋው ታዲያ ብዙው ዜጋ ሲማርና ሲሰለጥን በዚያም ምክንያት እውነተኛ ዴሞክራሲን ለይምሰልና ለታይታ ሳይሆን በማወቅና በሃቅ ስናሰፍን ነው፡፡ መንገድና ሕንጻ ደግሞ የጥቂቶችን ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና እንጂ የብዙኃንን ሁለንተናዊ ዕድገትና ልማት የሚያንጸባርቅ ሊሆን እንደማይችል ተደጋግሞ ተነግሯል፡፡ ስለዚህ ራስን በትምህርትና በዕውቀት እንዲሁም በቀና አመለካከትና አስተሳሰብ ለመገንባት ዘወትር መጣር ይኖርብናል ማለት ነው፤ ከልጆች አስተዳደግና ከቤተሰብ አያያዝ ጀምሮ ብዙ ይጠበቅብናል፡፡ ሕዝቡ ጠሊቅ እንቅልፍ ውስጥ ገብቶ በ“አንተ ታውቃለህ” ብቻ፣ በ“ከዚህ ይብስ አታምጣ” ብቻ፣ በ“ሺም ታለበ መቶ ያው በገሌ” ብቻ … ተወስኖ የሚኖር ከሆነ የጥቂቶች መፍጨርጨር ብቻውን የትም አያደርስም፡፡ ሊያውም ከጥቂቶቹም ውስጥ ብዙዎቹ ድብቅ አጀንዳቸው ለግል ጥቅምና ፍላጎት መሆኑን መገመት አስቸጋሪ ባልሆነበት ሁኔታ፡፡ አንድ ጠብሰቅ ያለ አንቀጽ መሰለሴ ነው፡፡
ማኅበረሰባችን አሁን የሚገኝበትን ቅርጽ ማሰቡ ሊያደክም ይችላል፡፡ አእምሮን ያናውዛል፡፡ ቲቪም ተመልከት፤ ሬዲዮም አዳምጥ፤ ከሰው ጋርም አውራ – ከማንም ጋር ተነጋገር ደርዝ ያለው ነገርና የትምህርትን ውለታ የሚያስታውስ አንድም ነገር ማግኘት እየከበደ ነው፤ አብዛኛው ወሬ ስፖርት፣ ተራ አሉቧልታና ወሲብ ነው፡፡ ጭንቅላትን በሚያፈነዱ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ችግሮች በተወጠረች ሀገር ውስጥ እንደደላው ሰው ሚዲያውና የሰዎች ትኩረት ሁሉ ይበልጡን በትርኪ ምርኪ ነገሮች ተጣብቦ ስታይ የት ነው ያለሁት ትላለህ – እርግጥ ነው ብዙ የጊዜው ሰዎች ጠግበዋልና ለነሱ ዘመኑ ሠርግና ምላሽ ነው፤ ከተሞችንና መዝናኛ ሥፍራዎችን በሞላ ተቆጣጥረዋል፡፡ የብዙዎች መዘናጋት የሚያሳየው ግን አንድም አፈናው በማያፈናፍን ሁኔታ ተባብሶ አፋችንን ሙሉ በሙሉ አዘግቶናል ወይም ሰው ችግሩን ትቶ በዋዛ በፈዛዛ ጊዜውን ለማሳለፍ ወስኗል ማለት ነው፤ ብቻ ሁኔታው በእጅጉ አሳሳቢ ነው፡፡ በዚህ መሀል ኃይለመድኅንን የመሰሉ ጀግኖችን በድንገት ማግኘቱ አጥንትን ዘልቆ የሚያለመልም ተስፋን ማጫሩ በጄ እንጂ ሁኔታዎች አስከፊ ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡ የሀብት ክፍፍሉን ስናይ፣ በቃላት ለመግለጽ የሚከብደውን የኑሮ ውድነት ስንታዘብ፣ በዘረኝነት ላይ የተመሠረተውን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ወታደራዊና ሃይማኖታዊ መዋቅር ስንመለከት፣ የሕዝቡን የንቃተ ኅሊና ደረጃ ስንቃኝ፣ የምሁራንንና የልሂቃንን ዝምታና እረጭታ ስናስብ፣ የወያኔ ፖለቲከኞችን የልብ ድንዳኔና ጭካኔ ስንመለከት፣ የሙስናውን መስፋፋትና የንግዱን መረን ማጣት ስናይ፣ የባለሥልጣናትን ማይምነትና የአስተዳደር ችሎታ ማነስ ስንታዘብ፣ የድህነትን መክፋት ስናስብ፣ የርሀብተኛውን ቁጥር ስናይ፣ በኑሮ ጣጣ ምክንያት በሀሽሽ፣ በመጠጥና በነገር ሰክሮና አብዶ ብቻውን እያወራ የሚሄደውን ዜጋ ስናስብ፣  … እኛንም ዕበዱ ዕበዱ የሚል መጥፎ መንፈስ ሊወርረን ይችላል፡፡ … በነጋዴዎችና ባለሥልጣናት የሙስና ትስስር ከቆዳችን አልፎ ዐፅማችን እንዴት እንደሚገሸለጥ አንድ ምሳሌ ልናገርና ላብቃ፡፡ በነገራችን ላይ የኔ የ4 ሺህ ብር የተጣራ ደሞዝ ቤተሰቤን ማስተዳደር ካቆመ ቆይቷል – ታዲያ እንዴት ትኖራለህ ካላችሁ መልሴ፣ ዘፋኙ “እኔስ እንደምንም … ሰው አልችል አይልም…” እያለ እንዳቀነቀነው እንደሰው ‹ባጀት በማጠፍ›ና ብዙ ነገሮችን አስቦ በመተው ብቻ ነው (ለምሳሌ ሥጋን፣ ወተትን፣ ቅቤን፣ ነጭ ጤፍን፣ ህክምናን፣ መዝናናትን …. ከዝርዝርህ ታወጣና ወይም እንደመስቀል ወፍ በተወሰነ ጊዜ ‹ታያቸውና› መኖር ተብሎ ትኖራለህ – ከዚያም እንደሰው ተፈጥረህ ስታበቃ እንደበግ ኖረህ ትሞታለህ፤ ሞትህም ተብሎ ወግ አይቀርም ዘመድ አዝማድና ጓደኛ እንደነገሩ ያለቅስልሃል ወንድሜ – እንጂ የሉካንዳ ቤት መስኮት ላይ መቆም አይደለም በዚያ በኩል ማለፍም የሞራል ብቃት ላይኖርህ ይችላል – ሕዝቡ እኮ በቁሙ ሞቷል ማለት ይቻላል፤ አብዛኛው ዜጋ የሚኖረው በተዓምርና በምትሃት ይመስላል፡፡ ምናለ በሉኝ ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ሥጋ ቤቶች ሥጋቸውን በነጭ ሱቲ ይሸፍኑና ለማየት ብቻ ሳያስከፍሉን የሚቀሩ አይመስለኝም፤ ለዚያስ አያድርሰኝ)፡፡ የኔ ደሞዝ እኔንና ቤተሰቤን በቅጡ ማኖር ካቆመ ከኔ አምስትና ስድስት እጅ ወደታች የሚገኙ ዜጎች አሁን በሚከፈላቸው በዱሮው ገንዘብ ሥሌት በሣንቲም ደረጃ የሚገመት ደሞዝ እንዴት እንደሚያኖራቸው ይታሰባችሁ፡፡ ማሰብ ደግሞ “እኔ እንትናን ብሆን” ብሎ እንጂ ለራስና ስለራስ ብቻ መሆን የለበትም፡፡ የአርባ ብር የዱሮ ደሞዝ ምን የመሰለ ቪላ ቤት ያሠራ ነበር – ሊያውም ፉሪና ሱሉልታ ሳይሆን አዲስ አበባ መሀል ከተማ፡፡ አርባ ብር አሁን በአንድ ተራ ቡና ቤት ልሙጥ ሽሮ ቢያበላ ነው፡፡ ለአንድ ተራ የሀብታም ነጋዴ ቤት ሊቀረጽ የማይችል የበር ቁልፍ ለመግዛት የኔን ደሞዝ እንደሚፈጅ ሰምቻለሁ – አራት ሺ ብር! ምሳሌ ሆቴል በሚባለው አንዱን ቤቱን ለግርማ ወ/ጊዮርጊስ መኖሪያ በመቶ ሺዎች ብር ለመንግሥት ያከራየው ወያኔ ሰውዬ ሁቴል ቤት ብትገቡ አንድ ክትፎ ብር አራት መቶ ብር ነው አሉ፡፡ እኔ በዚያ ቤት ውስጥ የወር ደሞዜን እንዳለ ባወጣት አሥር ጊዜ ክትፎ መብላት እችላለሁ ማለት ነው፡፡ … ወደምሳሌየ ልሂድ መሰለኝ፡- አንድ የአምስተኛ ክፍል ምሩቅ ነጋዴ ነው፡፡ ዕድሜው ወደሃያዎቹ እኩሌታ ነው፡፡ የሠራው ቤትና ያገባት ምሽት ሌላ ናቸው፡፡ መኪናውን አታንሱት፤ ግራ እጁ ላይ ያለው የውሻ ሰንሰለት እሚያህል የወርቅ ካቴናም እንዲሁ አይነሳ፡፡ በአንድ ጉዳይ ተገናኘንና ሊጋብዘኝ ሆነ – አፈኛ ሰው አንዳንዴ ጋባዥ አያጣም መቼም፡፡ “የሆድ ምቀኛው አፍ ነው” እንደሚባለው ግብዣን ከልክዬ ሆዴ እንዳይቀየመኝ የማላደርገው ጥረት የለምና በደስታ እሺ አልኩ፡፡ አምስት ሰዎች ሆነን ወደርሱ ምርጫ ምግብ ቤት አመራን፡፡ ምን አለፋችሁ – ለኔ ብቻ የወጣውን ሳሰላው ብር 350 ነው – አንድ ኪሎ የፍየል ጥብስና አንድ ጠርሙስ ከግማሽ ጠጅ፡፡ ጠጁ ደግሞ አሁን በብጥሌ ብርሌ ስድስት ብር የሚሸጠው ነፍሱን ይማርና የቤተ መንግሥቱ የጋሽ ድጋፌ ጠጅ እንዳይመስላችሁ – በሊትር መቶ ብር ነው፤ አለፈልኝ ነው እምልሽ የኔ እህት፡፡ የገረመኝ ለግብዣው ያን ያህል ገንዘብ መውጣቱ ወይም እኔ ሠርቼ እየገባሁ የበይ ተመልካች መሆኔ አይደለም፡፡ ያ ወጣት ልጅ ሀሁን ሳያውቅ በሸውራራ የንግድ አሠራር በሚያገኘው ገቢ በወር ከ75 ሺህ ብር በላይ ዕቁብ ይጥላል፡፡ ምቀኝነት የተጠናወተኝ እንዳይመስላችሁ – በፍጹም፡፡ ግን የሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ አካሄድ ወደገደል እየወሰደን መሆኑን ለማሰገንዘብ ያህል ነው፡፡ ለነገሩ ሚስቱ ሦስተኛውን ልጅ ስለወለደችለት ከአልማዝ ጌጥ በተጓዳኝ የ2.5 ሚሊዮን ብር መኪና ገዝቶ በጦፈ ግብዣ ላይ የሸለመ ወያኔ መኖሩንስ ከፋክት መጽሔት አንብቤ የለምን? እንዲህ ዓይነት ነጋዴዎችን አንቀባርሮ የሚያኖረው ደሞዜ ለኔ ባይተርፈኝ ታዲያ ይፈረድበታል ምዕመናን? የሰው ልጅ ግብዝነት ግን ይገርመኛል – በዚህ ዓይነት የውሻቸውን ልደት የሚያከብሩ ከውሻቸው የማይሻል ጭንቅላት ያላቸው ሀብታሞችም እኮ ይኖሩ ይሆናል፡፡ ወይ ሰው ሆኖ የመፈጠር አበሳ! ግን ግን ይህች ሀገር የማን ናት? መንግሥትን ደጀን ያደረጉ ሌባ ነጋዴዎችና ሙሰኛ ባለሥልጣናት እየተመሳጠሩ እስከመቼ ነው በተለይ የተቀጣሪ ሠራተኛውን ኑሮ መቀመቅ እንዳወረዱት የሚቆዩት? እኛስ ወግ ደርሶን ከአኗኗሪነት ወጥተን ማለፊያ ሕይወት የምንመራው መቼ ነው?  እነሱ አንገት ካጡ መብታችንን ማስከበር የምንችልበት መንገድ የለም ወይ? (በነገራችን ላይ በመንግሥት ትምህርት ቤቶች ከሚማሩ ተማሪዎች ከፊሉ ምሣ እንደማይዙ፣ ከነዚሁ ከፊሎች ውስጥ ግማሾቹ በቀን አንዴ እንኳን የረባ ነገር እንደማይመገቡና ከነዚህ ግማሾች ውስጥ ብዙዎቹ ከምግብ ዕጥረት የተነሣ በየክፍላቸው ‹ፌንት› እያደረጉ እንደሚወድቁ የሰማችሁ ይመስለኛል፡፡ ሌላ ሌላውን ቅንጦት እርሱትና በልብስ ረገድ እንኳን በውድ ዋጋ ከስንት አንዴ የምትገዛ ሞተ ከዳ (ልባሽ ጨርቅ) እየተጣጣፈችና መልኳን ከአንዴም ሁለት ሦስቴ እየቀየረች ለበርካታ ዓመታት ትለበሳለች፡፡ ባይገርማችሁ ስገዛት ቢጫ የነበረች አንዲት ጃኬቴ መጀመሪያ ወደቀይነት ከዚያም ወደ አረንጓዴነት አሁን በማብቂያው ደግሞ ወደአመዳምነት ተለውጣለች፤ ሁሉንም ቀለሞች ታዳርስ እንደሆነ ጉዷን አያለሁ በሚል ከመኝታ ሰዓት ውጪ አዘውትሬ በመልበስ  መጨረሻዋን በጉጉት እየተጠባበቅሁ ነው – በእግረ መንገዱም ጓደኞቼ ከሩቅም ሆነ ከቅርብ፣ ከፊት ለፊትም ሆነ ከበስተጀርባ እኔን በአሻጋሪ አይተው በጃኬቴ ለመለየት አይቸገሩም፡፡) ነገ ሩቅ ይመስላል፤ መምጣቱ ግን አይቀርም፡፡ ትንሽ ዕውቀት መጥፎ መሆኑን ከልብ እረዳለሁ፤ ስለዚህም ለእኔ እውነት በመሰለኝና ባመንኩበት ነገር ብዙም ባልተለመደ ግልጽነት “በዘባረቅኋቸው” የግል አስተያየቶቼ የተነሣ ያስቀየምኳችሁ ብትኖሩ በኅያው እግዚአብሔር ስም ይቅር እንድትሉኝ እለምናለሁ፡፡ ሚዲያዎች ጥናቱን ይስጣችሁ – እኔስ ተወረድኩት፡፡
መውጫ፡-  
“ሥጋን ከመግደል አልፈው ነፍስን መግደል የማይችሉትን ሰዎች አትፍሩ፤ ይልቁንስ ነፍስንና ሥጋን በገሃነም  ሊያጠፋ የሚችለውን አምላክ ፍሩ፡፡”  ማቴ. 10፣ 28
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይባርክ፡፡ የነጻነቷን ትንሣኤም በቅርብ ያሳየን፡፡
(ዕለተ የካቲት ገብርኤል 2006ዓ.ም፤ ከሌሊቱ 9፡00 ሰዓት ላይ ተጽፎ አለቀ)

Hailemariam Desalegn’s Confused Statements


by Amanuel Biedemariam
On February 10, Prime Minister Hailemariam Desalegn of Ethiopia gave reporters access and conducted a press conference. The statements of Hailemariam are fraught with inconsistencies and telling that there is a serious leadership vacuum and lack of direction in Ethiopia. The statements lack principle, direction and strategy. The messages are inconsistent and contradictory to previous statements.Prime Minister Hailemariam Desalegn of Ethiopia gave reporters access
On an interview with Africa Confidential January edition, when asked what’s your Eritrea policy? PM Hailemariam Desalegn said,
“Our Eritrea policy is very clear. These two peoples are very friendly; the normalizing of relations, also with the governments, should come as soon as possible. We have accepted unconditionally the rulings [on the border] and so this has to implemented but with a discussion because the implementation process needs something on the ground since it is a colonial rather than a people’s boundary.” Emphasis added.
For a while, Ethiopians have been expressing anger and concern about the border issue between Ethiopia and Sudan claiming that the minority TPLF regime has unlawfully ceded huge chunks of Ethiopian territories to Sudan. The tenet of their argument is that the signatures of Meles Zenawi and Hailemariam Desaleng are unlawful, null and void based on Article 55(12) of Ethiopian constitution which demands accountability and ratification by parliament. On a recent article, “Save Ethiopia From Chopping Block”,  Dr.Alemayehu G. Mariam wrote,
“It is important to understand and underscore the fact that the “agreement” Meles and Bashir “signed”, by Meles’ own description  and admission, has nothing to do with the so-called Gwen line of 1902 (“Anglo-Ethiopian Treaty of 1902” setting the “frontier between the Sudan and Ethiopia”). It also has nothing to do with any other agreements drafted or concluded by the imperial government prior to 1974, or the Derg regime between 1975 and 1991 for border demarcation or settlement. Meles’ “agreement”, by his own admission, deals exclusively with border matters and related issues beginning in 1996, when presumably the occupation of Sudanese land by Ethiopians took place under Meles’ personal watch.”
Citing Wikileaks, Dr. Al Mariam writes,
“Former TPLF Central Committee member and former Defense Minister Seeye Abraha told” American embassy officials in Addis Ababa that in a move to deal with “on-going tensions between Ethiopia and Sudan”, Meles had turned over land to the Sudan “which has cost the Amhara region a large chunk of territory” and that Meles’ regime had tried to “sweep the issue under the rug.”
It is unlikely that the views and efforts of the people of Ethiopia will ever see the daylight vis-à-vis the border agreements that Meles Zenawi or Hailemariam Desalegn signed or concluded since there is no question on the legitimacy of their positions by the international community. International agreements they signed will undoubtedly stand.
In response to those concerns Hailemariam responded,
“The historical border agreement between the two nations dates back to the time of Emperor Menelik II when the Sudan was under the protectorate of the British Empire. There should not be any confusion on the issue since the agreement that was signed then was evaluated and accepted by successive regimes that came after Menelik’s. The border agreements has been accepted and endorsed by the regimes and that there could not be any new matter that his administration has to deal with. “All that is left is to implement the already demarcated and delimited border agreement. So, there are no issues with the agreement: it is binding; the only thing left is to put posts on these borders.”
Hailemariam claims that Ethiopia is committed to regional peace. Why then is his regime illegally occupying internationally delimitated border with Eritrea? Why the doublespeak? The inconsistencies however are not limited to the border issues. Hailemariam’s positions and actions in Somalia and his view of Uganda’s role on the current conflict on SS are contradictory and dangerous for regional stability and progress. When he addressed Ugandan forces in SS, citing that the problem is political, Hailemariam said,
“We believe that all forces that were “invited” by different forces in that country have to withdraw phase by phase.”
The irony, on the same press conference, while addressing Somalia, Hailemariam claiming to have bilateral agreement with the government in Somalia tried to legitimize the presence of Ethiopian forces in Somalia. He said Ethiopia is in Somalia as AMISOM “based on the “request” of the Somali government.”
Ugandan forces are in S. Sudan based on the “invitation” of the legitimate government of S. Sudan. Why then is Hailemariam seeking or talking political solution for the civil war in South Sudan while interfering in Somalia militarily? Why not political solution in Somalia? Assuming that the government in Somalia is independent and free to request assistance freely as a nation, why deny the same right to the government in South Sudan? Hardly anyone believes that Ethiopian forces are welcome by the people of Somalia. AMISOM or not, Ethiopian forces are not welcome. To the contrary Ethiopia’s incursion into Somalia was not received well.
On a recent interview with the VOA, former U.S. Ambassador to Ethiopia David Shinn said that it is a “mistake” for Ethiopian troops to join the AMISOM force in Somalia.
Peace, security, terrorism and Al Shabab are justifications for Hailemariam to return into Somalia. The reality, however, Ethiopia’s incursions into Somalia is impediment to peace and source of great instability.
Ambassador Shinn continued, Ethiopian move could allow al-Shabab to use it as a “rallying cry to recruit new members.”
Moreover, Hailmariam’s positions are contradictory and self-serving as it regards to IGAD’s role on the current conflicts in the region. Hailemariam evoked IGAD and AU to make a case against the presence of Ugandan troops in South Sudan and ignored the role of IGAD in Somalia. Uganda is in South Sudan based on the request of the sitting government of Salva Kiir Miardet, just like Ethiopia is in Somalia based on claims of a request. Why then Hailemariam undermining IGAD’s role in Somalia?
Hailemariam Desalegn’s Compromised Stature     
By all standards Hailemariam Desalegn is on a tenuous position on many levels for many reasons.
Firstly, he is not from the region of the minority clique ruling the country. Many consider Hailemariam as a figurehead. On the 17 Feb, The Telegraph’s reporter David Blair on his report, “Ethiopian Airlines hijacking: Why co-pilot might have taken extreme steps to leave” wrote,
“Two key “push factors” lie behind this outflow: repression and poverty. Ethiopia is a de facto one-party state, dominated by small autocratic elite. Under the previous Prime Minister, Meles Zenawi, elections were shamelessly rigged and the opposition simply closed down. Many Ethiopians believed that Meles favored his own Tigray-Tigrinya ethnic group, who comprise less than seven per cent of the population, for the most powerful and privileged positions in the land.”
Hence, PM Haileriam Desalegn is considered a transitional figurehead until the election of 2015 and likely to be replaced by another member of the TPLF to pursue Zenawi’s agendas.
Secondly, Hailemariam inherited a country with a diminished regional and international influence for many reasons: A) The US has accomplished much of what it intended in Somalia hence the role required from Ethiopia is diminished. B) George Bush’s Somalia war on terror agenda, which the minority regime exploited extensively seems to have shifted slightly as the government in Somalia is recognized by the international community.
Thirdly, the countries in the region have opposing positions and interests on many areas as recent developments in S. Sudan exposed. Additionally,  these countries have demonstrated ability to compete with Ethiopia on many fronts denying Ethiopia the anchor-state-status it enjoyed unchallenged for a while thus minimized Ethiopia’s exclusive role in that regard.
Fourth, International actors such as China and Russia are playing significant roles to influence events and outcomes to favor their geostrategic interests. To be effective, China and Russia need to include all and play a balanced hand with all the nations in the region further diluting Ethiopia’s once dominant role.
Hailemariam’s Diminished Regional Roles 
One of the strongest suits of Meles Zenawi was the fact that he managed to co-opt influence from the regional actors using any means necessary. That level of influence died with Meles for many reasons:
  • The power transition took a long time to materialize. Between the times Meles was rumored sick, his death and the time it took to complete the transition creating vacuum.
  • The transition was manipulated to appease US interests while the real power remained on the hands of few Tigrayans led by the then Information Minister Bereket Simon who is considered the power controlling Hailemariam.
  • The regional actors are focusing on their own interests. One good example of this is the current conflict in S. Sudan and how it will likely affect the dynamics of the relations between South Sudan, Uganda and Ethiopia regarding the Nile. Hailemariam is forced to wager Ethiopia’s interests regarding the Nile in order to pursue US agendas in South Sudan. No consensus on South Sudan could lead to lack of consensus on issues of mutual importance including the Nile. Meles Zenawi was able to garner consensus and support for Ethiopia’s positions on the Nile which is hard for Hailemariam to replicate.
Furthermore, Uganda, Kenya, South Sudan, Rwanda have mutual interests independent from Ethiopia because all these countries depend on port of Mombasa in Kenya for their imports. This gives Kenya leverage and importance that Hailameariam cannot match.
Moreover, initially, with the help of the US, the regime was able to create alliances with countries in the region specifically to encircle and suffocate Eritrea to submission. At this stage, while Hailemariam desperately tries to pretend that Eritrea is isolated; the reality is Eritrea has turned the table. Eritrea has relations with Uganda, Sudan, Kenya, South Sudan and Egypt. At the current stage Hailemariam has no relation with Eritrea, Egypt, opposing positions with Uganda and South Sudan and Kenya has more interest independent from Ethiopia. In effect, Ethiopia is encircled further diminishing Hailmariam’s roles.
  • Shifting US foreign policy. Recent statements by former US diplomats regarding Eritrea stirred frantic reaction. The TPLF went on a full-fledged PR campaign to attack the issues and the personalities demonstrating fear the minority regime has of losing its status that it depends on for its very survival. On a piece about Zenawi’s legacy “Ethiopia: Revelation of Zenawi’s vision for Tigray,” Robele Ababya wrote,
“When asked, in the aftermath of the 2005 election, what legal authority he had to by-pass the Parliament and declare a state of emergency, Zenawi responded by saying that, after all, the donors did not object to the action he took. His response is solid proof, among others, that the monstrous killer was subservient to the interests of the donors at the expense of the vital interests of poor Ethiopia.”
Without US support the regime cannot survive. Hence fighting to maintain the “special-relation” status with the US is a question of survival. That however is beyond the control of the US as more African nations are looking for partnership with China, Russia, India, Brazil and other countries that are more focused on economic issues that Africa desperately need. This diminished US control of African agendas further diminishing Hailemariam’s role in the region that the late Zenawi enjoyed unchallenged.
Hailemariam Desalegn Lame Duck Personified
In the US, a president is generally considered a lame duck at the end of his tenure or when a successor is elected. What that generally means is, during that phase, if the president is not popular his/her influence could not translate into furthering his/her agendas and naturally no coattails. In reality, however, the president’s power is intact to the point that he/she can even wage wars.
In Hailemariam’s case, however, he is a lame duck in the truest sense because in Ethiopia, power is on the hands of the few repressive Tigrayans that are vying for time until the next election. “Ethiopia is a de facto one-party state, dominated by a small autocratic elite” controlling Hailmariam’s actions and public statements.
In addition, Hailemariam has no constituency inside Ethiopia or the Diaspora. Support for Hailemariam is virtually nonexistent.
Conclusion
The situation in Ethiopia is unsustainable. Ethiopia is under extreme internal and external pressures that will ultimately explode abruptly. As demonstrated above, to further the interests of the super powers, the regime suppressed the people and took unnecessary antagonistic positions by becoming a pseudo-hegemon of the region.   
What the press conference demonstrated is that PM Hailemariam Desalegn tried to address concerns of many stakeholders and failed. He tried to address the concerns of the people of Tigray, US interests, Somalia and regional actors. He tried to address Eritrea in a manner that satisfied TPLF and all Ethiopians and failed.
Ethiopia is on a holding pattern bracing for change on the upcoming election. The questions are many. There exists no political party to challenge the TPLF. What does the US want in this transition? Can the TPLF bring a successor from Tigray and continue the “legacy” of Meles? How would the US react to that?
In the absence of clear leadership direction these questions take on a new meaning enlarging the gap between all the publics. That means PM Hailemariam Desalegn will have to await his fate to be decided by the TPLF as the rest of Ethiopia.
Awetnayu@hotmail.com
-VOA Ethiopian AMISOM Membership Scrutinized
-Ethiopia: PM’s Day With the Press Yohannes Anberbir AllAfrica February 15, 2014
-Alemayehu G. Mariam Saving Ethiopia from the Chopping Block
-The Telegraph David Blair, Ethiopian Airlines hijacking: Why co-pilot might have taken extreme steps to leave 17 Feb 2014
-Africa Confidential January edition

How Ethiopia Is Taking A Step Forward and Few Steps Backward


by Jonas Clinton
Ever since I was a 9 year old kid in Calgary, Alberta in 1984, Ethiopia has held something special in my heart.
My connection to Ethiopia began in earnest when I saw disturbing images of destitute and famine victims before my eyes on cold Canadian winter. I cried for days and became depressed. I asked myself how humans can die before our own eyes so fast especially when the problem seems man-made. I quickly convinced my school to fundraise money and my parents donated generously to charity organizations. The Ethiopia that I observed from a distance
Little did I know how Ethiopia would shape my professional life later on. Because of what I saw on TV then, I studied international development in university and worked for years, mostly in Asian countries, with Non-Governmental organizations. However, Ethiopia was my first love. I have wanted to visit Ethiopia for such a long time embrace the unique cultural and historical facts of the country.
The Ethiopians I would meet later in life would always tell me about the proud history of the country being the only non-colonized country in Africa. I was impressed. I loved Ethiopian food, the coffee was amazing and my visit to Toronto almost always included frequent visits to Ethiopian restaurants all over the multicultural city. My non-Ethiopian friends would always complain about my fascination to such a “poor and miserable country”: – they would say.
I would repeat what my Ethiopian friends would tell me and tell them what we see on TV in just propaganda to raise money for charity organizations.
Three weeks ago, I went to visit Ethiopia for a month with my young kids. I remember looking outside my plane as we approached Bole International Airport and observing all green lands all over the country. How can this country starve?
As our flight landed and we exited the plane, we were met Ethiopian returnees from Saudi Arabia. These Ethiopians seemed sad and confused – how could they be miserable and scared about returning “home” from the brutality in the Arab world. Perhaps, they know what I don’t after all it was my first visit to the East African nation.
After a long lineup to get a single visa – we exited Bole. Soon I would learn everything in Ethiopia is linked to bureaucratic mess unless you are privileged to be Chinese or white like me. There were constructions everywhere and it was hard to walk freely as beggars would surround you in no time. And then there are the federal police who seem to follow and observe you where ever you go. I would even see familiar faces following me where ever I go.
It bothered me that I did not have to line up to get to government buildings and even shopping malls. That was strictly for the black faces of Ethiopia the guards would often tell me in their broken English. What happened to being a proud non colonized country?
Washrooms are a luxury placed in shinny buildings for patrons only. There are no public washrooms and the Ethiopian parliament is debating how much to charge for urination in a public arena. According to the government, only 15% of Ethiopians have access to washrooms out of a near 90 million population. How silly is that when the government neglected to build any public washrooms to begin with. Then again – in Ethiopia looking down on the poor is normal. I hope the powerful Ethiopians realize that social safety net for the poor is the hallmark of how one measures the advancement of such a country.
The middle class Ethiopians I would meet would tell me about how the government was perfect and would try to somehow impress me with their expensive jewelry and buildings they have built. They offer me expensive imported drinks such as Jake Daniel’s Blue Label Whisky when ever I visit them in their mansions while I was looking forward to trying local drinks. Ethiopia’s middle class are mostly made up of people with very little education gained from a long distance institution in India and work in the many NGO’s.
When the discussion turns to Ethiopian politics, they would tell me there is no opposition in Ethiopia with the exception of one representative out of 447 in Ethiopia’s House of Commons. For them, the opposition belongs in prison as they are against the state. Imagine putting Justin Trudeau in prison in Canada only because the government does not like what he says about them. I wonder if I could meet the only opposition member but I am warned that the government might not like that and I might pay a high price for it. In a shantytown that is Addis Ababa, anything is possible.
The streets of Addis are literally full of young prostitutes mirroring the poverty that exists in the country. It seems nobody wants to talk about them as well. Is this the Ethiopia that I observed from a distance and that Ethiopians have been telling me about?
I felt sad and confused.
I cut short of my visit and decided to fly out of Addis early by the government owned – Ethiopian Airlines. The Airlines is average by any international standard yet Ethiopians are very proud of its success. The success of the airlines is open to discussion as its numbers and financial reporting in never audited independently.
A day before I left Ethiopia, an Ethiopian airlines plane was diverted by its co-pilot, Hailemedhin Abera Tegegn. The allegation is that he took control of the plane while the main pilot was in the washroom and instead of flying it to its original destination, he flew it to Geneva. Upon arriving in Switzerland, he asked for asylum. Instead, he was arrested and now faces a possible prison of 20 years.
Ethiopia quickly asked for his return claiming he has mental issues. That was retracted as criticism mounted why such a person was flying a plane. His sister attempted to explain however her Facebook account was hijacked by the government and as she opened yet another account to explain her brother’s misgivings, she was imprisoned instead.
According to his aunt based in the United States, Abera, comes from a well to do prosperous middle class family with strict academic discipline and a job he seemed to enjoy. However, he had mysteriously lost a beloved uncle in recent weeks who was politically and eloquently against the government. In Ethiopia – where public demonstration or opposition to the government is seen as treason, he was a surpassed voice of millions not able to speak freely – an almost prisoner citizen.
According to the family – he wanted to show the world the horrible situation in Ethiopia for Ethiopians. Beyond the dotted minor advancement of constructions, mansions and restaurants – Ethiopia’s advancement has very little regards to human rights and security. He felt he was a victim of it all even as he was passed over promotions at work because he was an Amhara and saw his Tigre colleagues prosper.
I saw what he and everyday Ethiopians experience and I wondered why Ethiopians were not speaking out. For Abera – perhaps his alleged action is a desperate attempt to tell the world that something is indeed wrong with Ethiopia’s selective advancement.
Jonas Clinton lives in Calgary, Alberta, Canada.

The Myth of Development and Growth in Ethiopia


by Alem Mamo
“The government talks about poverty reduction, but what they are really trying to do is to get rid of the poor. They destroyed us by taking our forested land, 70% of the population has to disappear, so that 30 % can live on. Under Pol Pot we died quickly but we kept our forests. Under the democratic system it is a slow, protracted death. There will be violence, because we do not want to die.”
A Cambodian villager affected by an Economic Land Concession
“We want to be clear that the government brought us here… to die… right here… we want the world to hear that the government brought the Anuak people here to die. They brought us no food; they gave away our land to the foreigners so we can’t even move back. On all sides the land is given away, so we all die here in one place.”
                                                                                                             An Anuak elder in Abobo Woreda , May 2011
Over the last 40 years Ethiopia and Cambodia travelled similar tragic historical journeys. Mass killings perpetrated by two ruthless Stalinist totalitarian regimes remain a deep historical wound for the majority of the citizens of both countries. Tragically, the pain and suffering inflicted on the collective psyche of the peoples of these two countries haven’t had the proper social, economic and political avenue to heal, this is more so in Ethiopia than Cambodia. While Cambodia continues to make concerted efforts toward national reconciliation and healing, the TPLF/EPRDF minority regime in Addis Ababa followed its predecessor’s brutal crackdown on opposition or anyone suspected of being opposition. Carrying out torture, extrajudicial killings and gross violations of human rights the regime in Addis Ababa remains one of the most repressive governments in the world.
It is against this backdrop of the absence of fundamental human rights and respect to the rule of law that the TPLF/EPRDF regime is engaged in a deafening propaganda campaign of “development” and “economic growth.” Development in its authentic and complete form is not just a matter of a few glittering buildings or some paved roads; development in its broadest and complete form must be demonstrated through political, economic and social aspects of the lives of all citizens. Ethiopia is currently under the rule of former East Germany`s Stasi style security and surveillance police state. The government regularly spies on citizens both inside and outside the country. The social climate in Ethiopia is one of unease and dissatisfaction with the regime.
While the TPLF led regime in Addis Ababa continues in its endless propaganda campaign of “development” and “economic growth” four major undercurrents of ecological, political, economic and demographic tinder are developing.  When combined these four components could not only disprove the government`s false narrative of “development and economic growth,” they may well be catalysts for social upheaval and fundamental change.
Land grabbing, forced eviction, and ecological catastrophe:  Less than a half century ago 40% of Ethiopia was forested. Today only 2.7% remains and according to the UN report, Ethiopia could be completely deforested by 2020—that is 6 years from now.[1] In the simplest of terms what this means is that the ecological im on human and all forms of life will be devastating. If indeed there is anyone in the current TPLF/EPRDF regime concerned about the future of human and all other forms of life, and the very existence of the country, they shouldn’t have sold 1.9 million hectares of forested land to foreign corporations to produce flowers, rice and bio-fuel. These forested lands sold to multinational companies were part of the few remaining tropical forests that play a key role in the health and maintenance of the eco-system. In doing so the TPLF/EPRDF minority rule is working to make sure that by 2020 Ethiopia will be fully deforested and the country’s eco-system turns into a desert. Forced eviction and displacement of farmers from their ancestral land is becoming a routine exercise in Ethiopia. In its recent report the Oakland Institute provided a disturbing trend of forced eviction in southern Ethiopia region. According to Oakland Institute “260,000 local people from 17 ethnic groups who live in the Lower Omo and around Lake Turkana—whose waters will be taken for plantation irrigation—are being evicted from their farmland and restricted from using the natural resources they have been relying on for their livelihoods.”[2] The attack on the natural world and the environment is perhaps one of the most frightening and dangerous by this government.
Concentration of political and economic power in the hands of TPLF/EPRDF inner circle: Ethiopia as a country is effectively a one-party state. The political apparatus is fully controlled by members of TPLF, their allies, and close family members. The domination of the TPLF inner circle is not just in the political arena; it includes all major business ventures in the country. The concentration of most of the wealth and the monopoly of the economic and financial outlets has marginalized the general public from participating in building inclusive and fair economic structures in the country.
Anti-terror law terrorizing law-abiding citizens: The legislation that was designed to “fight terrorism” in Ethiopia is largely becoming a tool for terrorizing law-abiding citizens and to stifle dissent. In the process anyone who criticizes the regime would be incarcerated under the anti-terror law. In the process the regime itself is more violent and more lawless than citizens and organizations it accuses.
Young population: 63% of Ethiopia’s population is under the age of 25[3]. Largely unemployed and excluded from the economic and political discourse, the younger demographic is an important tinder that could ignite major social upheaval in the country. The youth in Ethiopia has a long standing history of being at the forefront of social movements. The current generation is no different from the previous; with proper mentoring and collaboration, the youth in Ethiopia could claim its rightful place in history and rescue itself and the country from a catastrophe.
19TH CENTURY British Prime Minister Benjamin Disraeli (1804-1881) once said “There are three kinds of lies: lies, damned lies, and statistics.” The TPLF-led regime in Addis Ababa has been mastering the art of lies and the art of putting out bogus statistics. Hollow statistics cannot address the fundamental problems facing the country. History tells us that deception and manipulation ultimately will not replace the truth and the facts on the ground. The tinder for social change in Ethiopia is escalating as the ecological, political and economic crises merge together demanding social transformation in the country.
The writer could be reached at alem6711@gmail.com