Thursday, December 26, 2013

ለኢትዮጵያ ሰማያዊ ፓርቲ ምስክርነት

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
ሰማያዊ ፓርቲን እንደፖለቲካ ድርጅት/ፓርቲ ለምን እንደምደግፈው፣
እ.ኤ.አ ዴሴምበር 15/2013 ከዋሽንግተን ዲሲ ወጣ ብላ በምትገኘው አርሊንግተን ከተማ የስብሰባ አዳራሽ በተዘጋጀው የሰማያዊ ፓርቲ የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ ተገኝቼ  ንግግር እስካደረግሁባት ዕለት ድረስ በበርካታ ጥያቄዎች እወጠር ነበር፡፡ አንደኛው ተደጋግሞ የሚጠየቀው ጥያቄ ለበርካታ ዓመታት ገለልተኛ ሆኘ እና ከማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ቡድን ጋር ሳልወግን ከቆየሁ በኋላ በአሁኑ ጊዜ ለሰማያዊ ፓርቲ ለምን ያልተቋረጠ ድጋፍ በመስጠት ላይ እንደምገኝ በሚቀርብ ጥያቄ ላይ የሚያጠነጥን ነው፡፡
በኢትዮቱብ ድረገጽ/ethiotube.com በሰጠሁት ቃለ ምልልስ በግልጽ እንዳስቀመጥኩት ለሰማያዊ ፓርቲ ቀጣይነት ያለው ድጋፍ የምሰጥበት ዋና ምክንያት የኢትዮጵያ ትኩስ ወጣት ኃይል የሀገሩን መጻኢ ዕድል የመወሰን እና በሰላማዊ የትግል ሂደት በመሳተፍ ለውጥ ለማምጣት ዝግጁ ነው የሚል ሙሉ እምነት ያለኝ በመሆኑ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ከኢትዮጵያ ህዝብ ውስጥ ከ35 ዓመት የዕድሜ ክልል በታች የሚገኘው የህብረተሰብ ክፍል 70 በመቶ ይሸፍናል፡፡ እንዲሁም በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ በአብዛኛው የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ሰለባ ሆኖ የሚገኘው ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡ አብዛኛው የወጣት ህብረተሰብ ክፍል የኢትዮጵያ የማጎሪያ እስር ቤቶች የፖለቲካ ጭቆና እና ማስፈራራት፣ ከህግ አግባብ ውጭ በዘፈቀደ በቁጥጥር ስር የመዋል እና እስራት፣ የስቃይ፣ የመብት እረገጣ እና ከህግ አግባብ ውጭ የእስር ቤት አያያዝ ሰለባ ዒላማ ሆኖ ይገኛል፡፡ አብዛኞቹ የኢትዮጵያ ወጣቶች ስር በሰደደ የስራ አጥነት ወጥመድ ተጠፍረው እና ጥራት ያለው የትምህርት ዕድል እና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት መብታቸውን ተነፍገው በሀገራቸው ላይ የበይ ተመልካች ሆነው ይገኛሉ፡፡ እዚህ ላይ የእኔን “አስረጅ” ምሰክርነት ለማስመዝገብ እንዲሁም ለሰማያዊ ፓርቲ ‘ምስክርነት’ ለመስጠት ያህል  በማያወላውል መልኩ የኢትዮጵያ ወጣቶች የቆሸሸውን የጎሳ ፖለቲካ፣ አስፈሪውን የኃይማኖት ጥላቻ  እና በውሸት ድር እና ማግ የተደወረውን የቅጥፈት ተምኔታዊ ፖለቲካ በጣጥሰው በመጣል “ፍቅር የነገሰበት የኢትዮጵያ ማህበረሰብ” የሚባል አንጸባራቂ ከተማ ከተራራው አናት ላይ እንደሚገነቡ ያለኝን የማይታጠፍ እምነት ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡ ይህ የተቀደሰ ተግባር የዛሬው ወጣት ትውልድ ቋሚ ታሪካዊ ዕጣ ፈንታ ነው የሚል ጽኑ እምነት አለኝ፡፡
የእኔ “አስረጅ” ሆኖ መቅረብ የእራሴን ሀሳብ እና አስተያየት ከመግለጽ ባለፈ በምንም ዓይነት መልኩ የሰማያዊ ፓርቲን፣ የአመራሩን ወይም የአባላቱን ያለፈውን፣ የአሁኑን እና የወደፊቱን ድርጅታዊ እና ድርጅታዊ ያልሆነ አቋም አይወክልም፡፡ በሰማያዊ ፓርቲ ላይ ምንም ዓይነት ሚና የለኝም፡፡ ያለኝ ብቸኛ ሚና ቢኖር “የሰማያዊ ፓርቲ ቁጥር 1 አድናቂ” መሆኔን በኩራት መግለጼ ብቻ ነው፡፡ እዚህ ላይ የእኔ ለሰማያዊ ፓርቲ ‘በአስረጅነት’ በጽናት መቆም ቅንድቦችን ከፍ ሊያደርግ ይችላል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ጠንካራ ደጋፊ በመሆኔ ከአንዳንድ ወገኖች ህብረተሰቡን በእድሜ እየለያየ የሚል ትችት ሲሰነዘር ሰምቻለሁ፡፡ እኔ በእድሜ በመከፋፈል መረጃ የመስጠት ጨዋታ ተጫወትኩ እንጅ በስልጣን ላይ ያለው ገዥው አካል እንደሚያደርገው ሁሉ በዘር ወገኔን በመከፋፈል የቁማር ጨዋታ አልተጫወትኩም፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ወጣቱ ኃይል ብይን እንዲሰጥበት በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡ ጆርጅ ኦርዌል እንዳሉት ‘ዓለም አቀፋዊ ማጭበርበር ተንሰራፍቶ በሚገኝበት በዚህ ዘመን ስለእውነት መናገር አብዮታዊ ድርጊት ነው‘፡፡ በአሁኑ ጊዜ የፖለቲካ አጭበርባሪነት፣ የሞራል ዝቅጠት እና አታላይነት ተንሰራፍቶ በሚገኝበት ሁኔታ እኔ ስለሰማያዊ ፓርቲ እየሰጠሁት ያለው ‘አስረጅነት’ እንደ ‘አብዮታዊ ድርጊት’ ይቆጠራል የሚል ዘርፈ ብዙ አመለካከት አለኝ፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ ቁጥር: 1  አድናቂ ለምን ሆንኩ?
በመጀመሪያ ደረጃ ሰማያዊ ፓርቲን የምደግፍበት ምክንያት ከወጣቶች፣ በወጣቶች፣ ለወጣቶች፣ የተቋቋመ የፖለቲካ ፓርቲ ስለሆነ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ የአብዛኛውን የኢትዮጵያን ህብረተሰብ ፍላጎት እና ጥቅም ሊወክል የሚችል ፓርቲ ስለሆነ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ከኢትዮጵያ ህዝብ ከ35 ዓመት የዕድሜ ክልል በታች ያለው የህብረተሰብ ክፍል 70 በመቶውን ይሸፍናል የሚለውን ሀቅ ላሰምርበት እፈልጋለሁ፡፡ (የሚቀርበውን መረጃ ታሳቢ በማድረግ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ አማካይ የህይወት እድሜ ከ49 – 59 ዓመት ነው፡፡)
የኢትዮጵያ የአቦሸማኔው ትውልድ (ወጣቱ ትውልድ) ብዙሀኑን የኢትዮጵያ ህዝብ ለመወከል የሚያስችል የራሱን የፖለቲካ ፓርቲ ማቋቋም ይፈልጋል፡፡ የአቦሸማኔው ትውልድ ለራሱ/ሷ መናገር፣ ለራሱ/ሷ መቆም፣ ለሴቶች፣ ለወንዶች መቆምን ይፈልጋሉ፡፡ የእራሳቸውን እና የአገራቸውን ዕጣ ፈንታ ሊወስኑ የሚችሉት እራሳቸው ወጣቶቹ ብቻ ናቸው፡፡
የጉማሬዎቹ ትውልድ (የእኔ ትውልድ) የፖለቲካ ፓርቲዎች በጉማሬዎቹ፣ ለጉማሬዎቹ የተቀመሩ እና በእነርሱ የአስተሳሰብ ንፍቀ ክበብ ውስጥ የታጠሩ ፍልስፍናዎች ስለሆኑ ከእረፍትየለሾቹ የኢትዮጵያ አቦሸማኔዎች (የወጣቱ ትውልድ) ህልሞች፣ ውስጣዊ ፍላጎቶች፣ ዓላማዎች እና የጋሉ ስሜቶች የስምምነት እምነቶች ንፍቀ ክበብ ውጭ ናቸው፡፡ እኛ የኢትዮጵያ የጉማሬዎች ትውልድ (የእኔ ትውልድ) የአቦሸማኔዎችን ትውልድ (የወጣቱን ትውልድ) ፍልስፍናአና አስተያየት አንረዳውም፡፡ ይህም በመሆኑ ብዙዎቻችን በጎሳ እና በክልል (“ባንቱስታን” ወይም “ክልላዊ”) የፖለቲካ ጭቃ፣ በሚያጣብቅ የጎሰኝነት ዝቃጭ ቆሻሻ፣ እና በታሪካዊ ምክንያተቢስ ጥላቻ  ውስጥ ለበርካታ ዓመታት ተዘፍቀን ስንዋኝ የቆዬን ስለሆነ ለስኬታማነት የማንበቃ የተሽመደመድን የህበረተሰብ ክፍል ነን፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ የአቦሸማኔ ትውልዶች (የወጣቶች ትውልድ) የጥንቱ ወይም የኋላቀር ፋሽን የጎሳ ማንነት ፖለቲካ እስረኛ መሆን አይፈልጉም፣ እንዲሁም ከጥንት ጊዜ ጀምሮ ከእራሳቸው ጋር በጥብቅ ተቆራኝቶ በታሰረ የታሪክ ክስተት መንገድ ላይ ለመራመድ አይፈልጉም፡፡ እንዲሁም ነጻነታቸውን በማወጅ እና የእራሳቸውን ዕጣ ፈንታ ለመምረጥ በመወሰን የእራሳቸው የሆነቸውን ኢትዮጵያ መፍጠር ይፈልጋሉ፡፡
“የኢትዮጵያ የጉማሬ ቡድን” ታማኝ አባል እንዳለመሆኔ መጠን የኢትዮጵያ የአቦሸማኔ ትውልድ ከኢትዮጵያ የጉማሬ ትውልድ በጣም ልዩነት አለው የሚለውን እውነታ ለመቀበል እቸገራለሁ፡፡ ለእኔ እና ለእኔው የጉማሬ ትውልድ የዱላ ቅብብሎሹን ለአቦሸማኔው ትውልድ በማቀበል ከጎን ሆነን የአቦሸማኔውን ትውልድ በትህትና የምናግዝበት የመጨረሻው ጊዜ እየደረሰ መሆኑን ለመቀበል እቸገራለሁ፡፡ ለዚህም ነው እራሴን ከጉማሬ ትውልድ ወደ “አቦ -ጉማሬ” ትውልድ ያሸጋገርኩት፡፡ ይህንን ሽግግር “የአቦ – ጉማሬ ትውልድ መነሳሳት” በሚለው ትችቴ ላይ መዝግቤ ማስቀመጤ የሚታወስ ነው፡፡
በሁለተኛ ደረጃ የወደፊቱ የኢትዮጵያ ወጣት ዕጣ ፈንታ በጥልቅ ያሳስበኛል፡፡ ከጥቂት ዓመታት በፊት ለማስታወስ እንደሞከርኩት ሁሉ “ደስታ የራቀው እና በመጥፎ ሁኔታ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ወጣት በጊዜ ቀመር ተሞልቶ ለመፈንዳት በመጠባበቅ ላይ የሚገኝ የሰው ቦምብ የመሁኑን ሀቅ ያመለክታል፡፡ የወጣቱ ተስፋ መቁረጥ፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ደስታ እየራቀው መሄድ፣ በቅዠት ህይወት ውስጥ መኖር እና ለብዙ ጊዜ በሚቆይ የኢኮኖሚ ቀውስ በመደቆስ ጥንካሬን ማጣት፣ የኢኮኖሚ ዕድሎችን እና ተጠቃሚነትን ያለማግኘት እና የፖለቲካ ጭቆና በገፍ ተንሰራፍቶ መገኘት ሊፋቅ የማይችል አስተማማኝ መረጃ ነው፡፡ ወጣቱ ለነጻነት ያለው ጥልቅ ፍላጎት እና የለውጥ ፈላጊነት ስሜት በእራሱ ማረጋገጫ ነው፡፡ እዚህ ላይ ሊነሳ የሚችለው ብቸኛ ጥያቄ የሀገሪቱ ወጣቶች ለውጥን ሊያመጡ የሚችሉት እየጨመረ በመጣው ወይም በሌላ በሰላማዊ የለውጥ አማራጮች…የሚለው ነው፡፡” ሰማያዊ ፓርቲ ተስፋ ያጣውን የወጣት ኃይል ወደ ሰላማዊ ሽግግር በማምጣት በኢትዮጵያ ውስጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል የሚል እምነት አለኝ፡፡
ሦስተኛ በወጣት ኃይል አድራጊ እና ፈጣሪነት ላይ በሙሉ ልቤ እተማመናለሁ፡፡ የወጣት ሀሳብ እና ጥልቅ የለውጥ ፈላጊነት ስሜት ልብን፣ አዕምሮን እና ሀገርን የመለወጥ ኃይል አለው፡፡ የወጣት ኃይል በዓለም ላይ ከሚገኙ ጠብመንጃዎች፣ ታንኮች እና የጦር አውሮፕላኖች በላይ የበለጠ ኃይል አለው፡፡ የአሜሪካ የሲቪል መብቶች እንቅስቃሴ የተካሄደው በወጣቶች ኃይል በተከፈለ የጉልበት መስዕዋትነት አማካይነት ነው፡፡ አብዛኞቹ በአመራር ቦታ ላይ የነበሩት እና የመብት ተሟጋቾች ወጣቶቹ የህብረተሰብ ክፍሎች ነበሩ፡፡ ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ በቢርሚንግሀም አላባማ የተካሄደውን የሲቪል መብቶች ሰላማዊ እንቅስቃሴ ሲመሩ የ26 ዓመት ወጣት ነበሩ፡፡ በዚያን ጊዜ ጆን ሌዊስ የ23 ዓመት ወጣት የነበሩ ሲሆን 24 ጊዚያት ታስረዋል፣ እንዲሁም ድርጊቱን ሊያስታውሱት በማይችሉት መልኩ በብዙ አጋጣሚዎች ሰውነታቸው ድቅቅ እስከሚል ድረስ ተደብድበዋል፡፡ እ.ኤ.አ በሜይ 6/1963 በበርሚንግሃም ከ2000 በላይ የሚሆኑ አፍሪካ አሜሪካውያን የሁለተኛ፣ የመለስተኛ ሁለተኛ እና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ተማሪዎች የዘር መድልኦን በመቃወም ሰልፍ በመውጣታቸው ብቻ ለአሰቃቂው እስር ተዳርገዋል፡፡
ወጣት አሜሪካውያን በቬትናም ላይ በእብሪት በመነሳሳት የተካሄደውን ጦርነት እንዲቆም አድርገዋል፡፡ በካሊፎርኒያ የዩኒቨርስቲ የተጀመረው የመናገር ነጻነት እንቅስቃሴ በአሜሪካ የመናገር ነጻነትን እና የዩኒቨርስቲ አካዳሚ ነጻነትን አጎናጽፏል፡፡ ያለወጣቱ ድምጽ መስጠት ባራክ አቦማ ለፕሬዚዳንትነት መመረጥ አይችሉም ነበር፡፡ ኮሚኒስታዊ ገዥዎችን እና በቅርቡም በሰሜን አፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ አገሮች ለመለወጥ አስቸጋሪ ናቸው ተብለው ይታሰቡ የነበሩትን ርህራሄየለሽ አምባገነኖች በሰላማዊ ትግል አንኮታኩቶ በመጣሉ እረገድ ወጣቱ ኃይል ወሳኝ የሆነ ሚና ተጫውቷል፡፡
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ወንበር ላይ ተፈናጥጠው የሚገኙት ገዥዎች የንጉሳዊውን አገዛዝ እና አምባገነናዊውን የወታደራዊ መንግስት በትጥቅ ትግል ለማንበርከክ ሲፋለሙ የነበሩ ወጣት “አብዮተኞች” ነበሩ፡፡ በእርጅና የእድሜ ጊዚያቸው ግን ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ከኢትዮጵያ ምድር ለማስወገድ ሲፋለሙት የነበረውን ጭራቅ ሆነው ተቀምጠዋል፡፡ ከዚህ አንጻር በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ህብረተሰብ ለመመስረት ለበርካታ ዘመናት መስዕዋትነትን በመክፈል የእራሳቸውን ድርሻ በመወጣት ላይ ባሉት የኢትዮጵያ ወጣቶች ኃይል ላይ ሙሉ እምነት አለኝ፡፡ እ.ኤ.አ በ2005 አሁን በስልጣን ላይ ያለው የኢትዮጵያ ገዥ አካል ታጣቂዎች እንደ አበደ ውሻ በአዲስ አበባ መንገዶች ላይ በመክለፍለፍ በመቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶችን በጥይት ጨፍጭፈዋል ገድለዋል፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩትን ደግሞ ለእስራት ዳርገዋል፡፡ (በዚያን ጊዜ በሰው ልጅ ህይወት ላይ በጣም አስደንጋጭ እና አስፈሪ የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ወንጀል በማየቴ በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ተሟጋችነት አንደቀላቀል ተገድጃለሁ፡፡) በአሁኑ ጊዜም እንኳ የኢትዮጵያ ወጣቶች ለዴሞክራሲ፣ ለህግ ልዕልና፣ ለነጻነት እና ለሰብአዊ መብት ጥበቃ ሲባል የደም፣ የላብ እና የእንባ መስዕዋትነት በመክፈል ላይ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያ ምርጡ እና ብሩህ አዕምሮ ያለው ወጣት እየተቀጣ፣ ፍርደገምድል ፍርድ እየተበየነበት፣ እየታሰረ፣ እና ጸጥ እረጭ ብሎ እንዲገዛ እየተደረገ ነው፡፡ ከእነዚህ የወጣት ዝርዝር የመጀመሪያው እረድፍ ላይ የሚገኙት ብርቱካን ሚደቅሳ፣ እስክንድር ነጋ፣ አንዷለም አራጌ፣ ርዕዮት ዓለሙ፣ በቀለ ገርባ፣ አቡበካር አህመድ፣ ውብሸት ታዬ፣ ኦልባና ሌሊሳ፣ አህመዲን ጀቤል፣ አህመድ ሙስጣፋ፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ በቅርቡ ከህይወት የተለየው የኔሰው ገብሬ እና ሌሎች ለቁጥር የሚያታክቱ ትንታግ የኢትዮጵያ ወጣቶች ናቸው፡፡
በመጨረሻ ሆኖም ግን አስተዋጽኦው ቀላል ካልሆነው ከሰማያዊ ፓርቲ ፕሮግራም ጋር ሙሉ በሙሉ እስማማለሁ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በደንብ አስቦበት እና የሀገሪቱን ዘርፈ ብዙ ችግሮች ለመቅረፍ የሚያስችል ተግባራዊ ፕሮግራም ነድፎ የሚንቀሳቀስ ፓርቲ ነው፡፡ ከእኔ ልዩ አተያይ እና ስጋት አንጻር በፍትሀዊ አስተዳደር፣ በሰብአዊ መብቶች እና በህግ የበላይነት አተገባበር ላይ ትኩረት በማድረግ የፓርቲውን ፕሮግራም ስገመግመው በጠንካራ መሰረት ላይ የተዋቀረ ልዩ ፓርቲ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ፓርቲው ሙሉ በሙሉ ነጻ የሆነ እንዲሁም ከፖለቲካ ተጽዕኖ እና ጣልቃገብነት ፍጹም ነጻ የሆነ እና ብቃት ያለው የፍትህ ስርዓት በሀገሪቱ እንዲመሰረት ድጋፍ ያደርጋል፡፡ ዳኞች ሲያጠፉ መከሰስ ያለባቸው መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በሙያቸው በቋሚነት ጡረታ እስከሚወጡበት ጊዜ ድረስ ተቀጥረው እንዲሰሩ ያደርጋል፡፡ ፓርቲው ህገመንግስታዊ ፍርድ ቤት ከነሙሉ ስልጣኑ ጋር እንዲቋቋም ድጋፍ ያደርጋል፡፡ ኢትዮጵያ ፈርማ ባጸደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ውሎች እና ስምምነቶች ለመገዛት እና ለተግባራዊነታቸውም ዕውን መሆን ፓርቲው ጠንክሮ እንደሚሰራ ቃል ገብቷል፡፡ የግለሰብ መብቶችን ጥበቃ የመናገር እና የእምነት ነጻነቶችን ጨምሮ ተግባራዊ እንደሚያደርግ ፓርቲው ቃል ገብቷል፡፡ መንግስት እና ኃይማኖት በግልጽ መለያየት እንዳለባቸው ፓርቲው በጽኑ ያምናል፡፡ ፓርቲው ማንኛውንም በብዙሀን መገናኛ ዘዴዎች ላይ የሚደረግን ቅድመ ምርመራ አጥብቆ ይቃወማል፣ እንዲሁም ከህግ አግባብ ውጭ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ማህበራት እንዳይዘጉ ያደርጋል፡፡ የሀገሪቱ የጦር እና የደህንነት ኃይል ታማኝነቱ ለሀገሪቱ ህገመንግስት መሆን እንዳለበት እና በምንም ዓይነት መልኩ ለፖለቲካ ፓርቲ፣ ለጎሳ ቡድን፣ ለክልል ወይም ለሌላ አካል ታማኝ መሆን እንደሌለበት ፓርቲው በፕሮግራሙ ላይ አጽንኦ በመስጠት አስፍሮታል፡፡ የፓርቲው የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ፣ የማህበራዊ እና የባህል ጉዳዮችም እንደዚሁ በተመሳሳይ መልኩ ትኩረትን በጣም የሚስቡ ናቸው፡፡
ሰማያዊ ፓርቲን  እንደ  ንቅናቄ እና የኢትዮጵያ የአቦሸማኔዎች (ወጣቶች) ትውልድን እውነተኛ ድምጽ ለምን እንደምደግፍ፣
እንደ እራሴ ሀሳብ ሰማያዊ ፓርቲ እንደማንኛውም ተወዳድሮ ስልጣን በመያዝ ወደ ስልጣን ቢሮ ከሚገባ  የፖለቲካ ድርጅት የበለጠ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እንደፖለቲካ ድርጅት እራሱን ቢያዘጋጅ እና በተለመደው መልክ ምርጫ ቢያሸንፍ እና የፓርላማ ወንበር ቢይዝ ምንም አዲስ የማገኘው ነገር የለም፡፡ ከ80 በላይ “የተመዘገቡ ፓርቲዎች” ባሉባት ሀገር (በጣም አብዛኞቹ ለይስሙላ የተቋቋሙ የጎሳ የፖለቲካ ፓርቲዎች) እና ገዥው “ፓርቲ” በ99.6 በመቶ በሚያሸንፍበት ሁኔታ ከግማሽ ነጥብ በመቶ ያነሰ ድምጽ ለማግኘት እንደሰማያዊ ፓርቲ ሁሉ ሌላ ፓርቲ ተመዝግቦ ለዚህች በጣም በጣም ትንሽ ለሆነችው ድምጽ ለመወዳደር የመሞከሩን አስፈላጊነት ትርጉምየለሽ ያደርገዋል፡፡ ለዚህም ነው ሰማያዊ ፓርቲን በኢትዮጵያ ከወጣቶች፣ ለወጣቶች፣ በወጣቶች የተቋቋመ የወጣቶች ንቅናቄ ነው የሚል እምነት ያለኝ፡፡
“የሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄን” የኢትዮጵያ ወጣቶች ለእራሳቸው እና ለወደፊቱ ትውልድ የሚተላለፍ ህልማቸውን እና ሀሳቦቻቸውን የሚተገብር ድርጅታዊ ተቋም አድርጌ እወስወደዋለሁ፡፡ እንደ ንቅናቄ ሰማያዊ ፓርቲ በብዙ የአቅም ደረጃዎች ላይ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያን ወጣቶች ስለብዙው የሀገራቸው ታሪክ፣ ልማዶች እና ባህሎች እንዲያውቁ የሚያደርግ “የትምህርት” ተቋም ነው፡፡ የኢትዮጵያ ወጣቶች የማትከፋፈል የአንዲት ኢትዮጵያ፣ ኃያል ወራሪውን የአውሮፓ ኃይል አሸንፋ እና አሳፍራ የመለሰች የኩሩ አርበኞች ዘር የትውልድ ሀረግ መሆናቸውን ያስተምራል፡፡ እንደ አሁኑ ሳይሆን በአንድ ወቅት ኢትዮጵያ በዓለም እና በአፍሪካ ለሚኖሩ ጥቁር ህዝቦች የኩራት ፈርጥ ነበረች፡፡ የአሁኑ የሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ የቀደመውን ኩራታችንን እንደገና መልሶ ለኢትዮጵያውያን ህዝቦች የማጎናጸፍ ዓላማን ሰንቆ ተነስቷል፡፡
“የሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄን” ዋና ዋና ዕሴቶች እጋራለሁ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ገዥዎችን እና ኢፍትሀዊነትን በሰላማዊ የትግል ስልት መንገዶች የማስወገድ እምነት አለው፡፡ በዓለም ላይ በየትኛውም ቦታ ገዥዎችን እና ኢፍትሀዊነትን በሰላማዊ የትግል ስልቶች በመጠቀም ለማስወገድ እሰብካለሁ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በኢትዮጵያ ወጣቶች የሽግግር ኃይል ላይ እምነት አለው፡፡ ባለፉት ሰባት ዓመታት በኢትዮጵያ “እና በአፍሪካ” ላይ ወጣቶች የጻፍኳቸውን የሰኞ ዕለታዊ ትችቶች በሙሉ መልክ በማስያዝ በጥራዝ ቢዘጋጁ የኢትዮጵያ ወጣቶችን የሽግግር ኃይል በተጨባጭ የሚያመላክት ማስረጃ ይሆናልሉ፡፡ የእኔ መፈክርአሁንም በፊትም ወደፊትም ፣ “የኢትዮጵያ ወጣቶች ተባበሩ፣ በፍጹም እጅ እንዳትሰጡ፣ ኃይል ለኢትዮጵያ ወጣቶች!” ነው፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ አንድ ግብ ብቻ አለው፣ “ፍቅር የነገሰበትን የኢትዮጵያ ማህበረሰብ” መፍጠር፣ ልክ ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ በረዥሙ የትግል ጉዟቸው በአሜሪካ የሰብአዊ እና የሲቪል መብቶችን በማለም “ፍቅር የነገሰበት ማህበረሰብን” ለመመስረት እንዳደረጉት ተጋድሎ ሁሉ፡፡ ዶ/ር ኪንግ እንዲህ ብለው አስተማሩ፣ “የሰላማዊ ትግል ማህበራዊ ለውጥ መጨረሻው ዕርቅ ነው፣ መጨረሻው ኃጢያትን ተናዝዞ ንስሀ መግባት ነው፣ መጨረሻው ፍቅር የነገሰበትን ማህበረሰብ መመስረት ነው፣ እንግዲህ ይህ ዓይነቱ አስተሳሰብ እና ፍቅር ነው በባላንጣነት የሚተያዩትን ወገኖች ወደ ጓደኝነት የሚያመጣው፡፡” “ፍቅር የነገሰበት የኢትዮጵያ ማህበረሰብ“ ከክልላዊነት (ባንቱስታን) አመድነት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚወጣ እምነቴ የጸና ነው፡፡
“ፍቅር የነገሰበት የኢትዮጵያ ማህበረሰብ” የሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ መሰረቱ አንድነት፣ ሰላም እና ተስፋ ነው፡፡ “ፍቅር የነገሰበት የኢትዮጵያ ማህበረሰብ” ሰው በመሆኑ ብቻ አንድ ይሆናል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ከከፋፋይ የጎሰኝነት እና ከአፍቅሮ የጎሰኝነት ስሜት ነጻ ይሆናል፡፡ ይህ ዓይነቱ ማህበረሰብ እኩልነት፣ ፍትሀዊነት እና ተጠያቂነት ያለው ህብረተሰብ ለመመስረት ጥረት ያደርጋል፡፡ “ፍቅር የነገሰበት የኢትዮጵያ ማህበረሰብ“ ከእራሱ እና ከጎረቤቱ ጋር ሰላም ፈጥሮ የሚኖር ህብረተሰብ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ከጎሳ አለመቻቻል እና ጥላቻ ነጻ የሆነ እንዲሁም ከፍርሃት፣ ጥልቅ ጥላቻ እና ከገዥዎች እና ከጨቋኞች ነጻ የሆነ ማህበረሰብ ይፈጥራል የሚል እምነት አለኝ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ደኃ እና ሀብታም፣ ወጣት እና ሽማግሌ፣ ወንድ እና ሴት፣ ክርስቲያን እና ሙስሊም… ለማለም ነጻ፣ ለማሰብ ነጻ፣ ለመናገር፣ ለመስማት እና ለመጻፍ ነጻ፣ ከጣልቃገብነት ነጻ ሆኖ ለማምለክ፣ ለመፍጠር ነጻ፣ ለመስራት ነጻ እና ነጻ ለመሆን ነጻ የሆነ ዓላማ ይዞ ነው የተነሳው፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ ሰላምን በአግባቡ በመጠቀም ጥላቻን፣ የጥላቻ መንፈስን፣ ለመጣላት መቸኮልን፣ ወደ ጓደኝነት፣ መተሳሰብ እና መከባበር በማሻጋገር ለኢትዮጵያ ህዝብ ሰላምን ያመጣል የሚል እምነት አለኝ፡፡ ንቅናቄው ከመራራ ትችት በውይይት፣ ከመቃረን በስምምነት፣ ከጥላቻ በፍቅር፣ እና ጭካኔን፣ ወንጀለኝነትን እና ታጋሽየለሽነትን ለማሸነፍ የሰው ልጅን ክብር ከፍ የሚያደርጉትን መርሆዎች እንደሚከተል እምነቴ የጸና ነው፡፡ “ፍቅር የነገሰበት የኢትዮጵያ ማህበረሰብ“ “የተስፋ እና የህልሞች መሬት” ነው፡፡ ይህ ማህበረሰብ ወጣቶች ለእኩል ዕድሎች፣ ለእኩል መብት እና ፍትህ እንዲያስቡ የሚያደርግ ነው፡፡ ይህ ማህበረሰብ የኢትዮጵያ ወጣቶች ነጻ ሆነው ተስፋዎቻቸውን እና ህልሞቻቸውን በጋራ መካፈል እንዲችሉ የሚያበቃ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ወጣቶች የማይገታ ተስፋ አንዳላቸው ጽኑ እምነት አለኝ፡፡
ለሰማያዊ ፓርቲ ምን ማድረግ እንዳለብን እንጠይቅ፣
ሁሉም ኢትዮጵዊ በተለይም የእኔ የጉማሬው ትውልድ ከሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ ጎን እንድንቆም  አበረታታለሁ፣ እማጸናለሁም፡፡ አውቃለሁ፣ ብዙዎቻችሁ ቀደም ሲል ድጋፋችሁን ለመስጠት በሞከራችሁበት ጊዜ በተፈጠረው ያልተሳካ የትግል ውጤት ምክንያት ተገቢነት ያላቸው ጥያቄዎች፣ ብዥታዎች፣ እና ጥርጣሬዎች ሊኖሯቹህ እንደሚችሉ እገነዘባለሁ፡፡ “እነዚህ ወጣት እና የአመራር ልምድ የሌላቸው ሰዎች ትክክለኛውን ነገር የሚሰሩ ለመሆናቸው ምን ማስተማመኛ አለን?“ በማለት ተጠይቂያሁ፡፡ እኔም እንዲህ የሚል መልስ ሰጠሁ፣ “ልምድ ያለን እና እምነት የሚጣልብን የጉማሬው ትውልድ አመራሮች የሆንነው ከዚህ ቀደም እንዴት ሰራን?“ አፍሪካ በማያቋርጥ አምባገነናዊ የአገዛዝ መዳፍ ስር ወድቃ ስለምትገኝ የወጣቱን የህብረተሰብ ትኩረት የሚስቡ በርካታ ነገሮች እየተፈጠሩ ነው፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ አመራሮች፣ አባላት እና ደጋፊዎች ስብዕናዎቻቸው ከምን ከምን ነገሮች እንደተዋቀሩ አሳይተውናል፡፡ የተዋቀሩባቸው የመሰረት ድንጋዮች በዝርዝር ሲታዩ የሚከተሉትን ያካትታል፡ ድፍረት፣ የሞራል ጽናት፣ ስነስርዓት፣ ብስለት፣ ጀግንነት፣ ክብር፣ የመንፈስ ጽናት፣ ፈጣሪነት፣ ትህትና፣ ሀሳብ አፍላቂነት እና እራስን ለመስዋዕትነት ማዘጋጀት ናቸው፡፡ ስብዕናዎቻቸውን በማክበር ላለመንበርከክ ሲሉ በቁጥጥር ስር ውለዋል፣ ታስረዋል፣ እንዲሁም ተደብድበዋል፡፡ ሰላማዊ ትግሎቻቸውን አላቋረጡም፡፡ እኛን በማሳመን ሙሉ ድጋፋችንን ከማግኘታቸው በፊት ሌላ ምን ተጨማሪ መስዕዋትነት መክፈል ይኖርባቸዋል? ወጣቶች እና አዲስ ነገር ለማምጣት ጥልቅ ፍላጎት ያላቸው ናቸው፣ በሰላማዊ ትግል ለውጥ ለማምጣት ተገቢው ልምድ ያላቸው ሲሆን ይህንኑ ልምዳቸውን እስከመጨረሻው ይቀጥሉበታል፡፡
አንዳንድ ሰዎች ሰማያዊ ፓርቲ ለገዥው አካል ወይም ለሌላ ድብቅ ዓላማ ላላቸው ኃይሎች ተቀጣሪዎች ላለመሆናቸው ምን ማረጋገጫ አለ በማለት ይጠይቃሉ፡፡ ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ የምለው ነገር ቢኖር የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላት እና ደጋፊዎች የገዥው አካል ታማኝ ሎሌዎች ናቸው ብለን የምናስብ ከሆነ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም፣ ፕሮፌሰር ያዕቆብ ኃይለማርያም እና ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያምም ሊጠቀሱ የሚችሉ ታማኝ ሎሌዎች ናቸው ማለት ነው፡፡ ገዥው አካል ብልህ ከሆነ ሰማያዊ ፓርቲ ስለየህግ የበላይነት እና ስለዴሞክራሲያዊ አስተዳደር ያሉትን ፕሮግራሞች በመገናኛ ብዙሀን ለማስተላለፍ እንዲችል መፍቀድ ይኖርበታል፣ ይህን ካደረገ እኔ ለዚህ ደጋፊ ነኝ፡፡ በአሁኑ ጊዜ ገዥው አካል ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች (በሚስጥር እስር ቤቶች የሚገኙትን ጨምሮ) የሚለቅ ከሆነ፣ ጨቋኝ ህጎችን የሚሰርዝ ከሆነ፣ የሰብአዊ መብት ድፍጠጣዎችን እና ምርጫ ማጭበርበርን የሚያቋም ከሆነ ከመንገድ በመውጣት የመጀመሪያ በመሆን እነሱን በማሞገስ የምዘምር እሆናለሁ፡፡ ጉዳዩ በስልጣን ላይ ስላሉት ሰዎች አይደለም፣ ሆኖም ግን ጉዳዩ በስልጣን ላይ ስላሉት ጭራቃዊ ድርጊት ስለሚፈጽሙት ሰዎች እንጅ፡፡
ባለፉት አስርት ወይም ከዚያ በላይ ዓመታት ተመስርተው በመንቀሳቀስ ላይ የነበሩት እና በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙት የፖለቲካ ድርጅቶች ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ ስኬታማ ሳይሆኑ እንደቀሩ አንዳንድ ሰዎች ይነግሩኛል፡፡ እንዲህ በማለትም ይጠይቁኛል፣ “ሰማያዊ ፓርቲም ስኬታማ ሳይሆን የሚወድቅ ላለመሆኑ ምን ዋስትና አለህ?“ ሰማያዊ ፓርቲ ላለመውደቁ ምንም ዓይነት ዋስትናዎች የሉም፡፡ ስኬታማ ሳይሆን የሚወድቅ ከሆነ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች እና አባላት ጽናት እና እራስን ለስነስርዓት ያለማስገዛት፣ የዓላማ ጽናት እና እራስን መስዕዋት ለማድረግ ያለመቻል ጉድለት ሊሆን አይችልም፡፡ በዋናነት ለውድቀቱ ምክንያት ሊሆን የሚችለው ድጋፍ ያለማግኘት፣ ቅን መንፈስ ያለመኖር፣ በእራስ የመተማመን ጉድለት፣ የለጋሽነት እጥረት እና በአገር ውስጥ ካለው ኢትዮጵያውያን/ት ወገኖች እና ከዲያስፖራው ማህበረሰብ የማቴሪያል እና የሞራል ድጋፍ ለማግኘት ያለመቻል ነው፡፡ ፓርቲው ስኬታማ ባይሆን እና ለውድቀት ቢዳረግ በእብሪትነት ተነሳስተን፣ የሌባ ጣታችንን ወደ ፓርቲው በመቀሰር፣ “ተናግሬ አልነበረም!“ ስንል ሦስቱ ጣቶቻችን ደግሞ ቀስ ብለው ወደ እኛ እያመለከቱ መሆናቸውን መዘንጋት የለብንም፡፡ ኔልሰን ማንዴላ እንዲህ ሲሉ ተማጽነዋል፣ “እኔን በማስመዘግባቸው ስኬቶች አትገምግሙኝ፣ይልቁንም ምን ያህል ጊዜ እንደወደቅሁ እና ከውድቀቶች ተመልሸ እንደተነሳሁ እንጅ” ብለዋል፡፡ ከዚህ አንጻር ሰማያዊ ፓርቲ ወደፊት ምን ያህል ጊዜ አዳልጦት ይወድቃል ብለን ከመገምገም ይልቅ ፓርቲው በእኛ እገዛ እና ድጋፍ ከውድቀቱ እንደገና ለመነሳት ምን ያህል ጊዜ ጥረት ያደርጋል የሚለውን ነው መገምገም የሚኖርብን፡፡
ባለፉት በርካታ ጊዚያት እንደታየው የሚያዋጡት የገንዘብ ድጋፍ አላግባብ ሊባክን ይችላል የሚል ስጋታቸውን አንዳንድ ሰዎች ገልጸውልኛል፡፡ ጠንካራ የሆኑ የተጠያቂነት እና ግልጸኝነት ዋስትናዎችን ማግኘት ይፈልጋሉ፡፡ እንዲህ ብለውም ይጠይቁኛል፣ “ባለፉት ጊዚያት ሌሎች እንዳደረጉት ሁሉ ሰማያዊ ፓርቲም በእርሱ ላይ ያለንን እምነት ላለመሸርሸሩ በምን ሁኔታ ማረጋገጥ እንችላለን?”
በሰሜን አሜሪካ ያለው የሰማያዊ ፓርቲ የድጋፍ ስብስብ በጣም ጠንካራ እና በስነስርዓት የታነጸ የኢትዮጵያ ወጣት ኃይል ስለሆነ ከዚህ ስብስብ ጋር መተዋወቄ እና አብሬም መስራቴ ታላቅ ክብር እና ደስታ ይሰጠኛል፡፡ እነዚህ ወጣት ኢትዮጵያውያን/ት የኢትዮጵያን ወጣቶች ትግል ለመደገፍ ከኪሳቸው በርካታ ገንዘብ በማውጣት በስራ ላይ እንዲውል በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ የሙያ ስብጥራቸውን ስንመለከት ወጣት ፕሮፌሽናሎች፣ በንግድ የሙያ ዘርፍ የተሰማሩ ወንዶች እና ሴቶች እንዲሁም የኢትዮጵያን የጎሳ፣ የጾታ እና የባህል ህብረ ብሄር የሚወክሉ ናቸው፡፡ የተያቂነትን እና ግልጸኝነትን ዋጋ በሚገባ የተገነዘቡ ናቸው፡፡ እርስ በእርሳቸው በመተማመን እና ለእሴቶቻቸው ተገዥ በመሆን ድጋፋቸውን የሚሰጡ ናቸው፡፡ ለወጣቶቹ ዕድሎችን በመስጠት መሞከር እና ለምሰጠው የድጋፍ ገንዘብ ችግር የለብኝም፣ ምክንያቱም ወጣቶቹ የዚህ አይነት ዉርደት ላይ መውደቅ አንደማይሹ ተገንዝበአለሁ፡፡ መርህን በሚያከብሩት የኢትዮጵያ ወጣቶች እና ህዝቦች ታላቅ እምነት አለኝ፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች ትክክለኛውን ነገር ይሰራሉ የሚል እምነት የእኔ ዋስትና ነው፡፡
እ.ኤ.አ ዴሴምበር 15/2013  በኣርሊንግቶን ከተማ አዳራሽ ለመጀመሪያ ጊዜ በተጠራው የሰማያዊ ፓርቲ ስብሰባ ላይ በመገኘት ባደረግሁት ንግግር የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ይልቃል ጌትነት እርዳታ ለመሰብሰብ እና ለኑስ አምስት ሳንቲም ልመና ወደ አሜሪካ አልመጣም በማለት ለተሰበሰበው ታዳሚ ተናግሬ ነበር፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ከእኛ በሰሜን አሜሪካ ከምንኖር ኢትዮጵያውያን/ት እርዳታ ወይም የገንዘብ ልገሳ አይፈልግም፡፡ ይልቁንም ይልቃል ወደ አሜሪካ የመጣው ገዥው አካል በሰማያዊ ፓርቲ ላይ እያደረሰ ያለውን አስቸጋሪ ሁኔታ፣ የህግ ስርዓት ሂደቱን፣ በአባላቱ ላይ የሚደርሱባቸውን ችግሮች፣ ጨካኝ አምባገነናዊ ስርዓት ባለበት ሁኔታ ፓርቲው ዓላማዎቹን ለማሳካት እንዴት እየሰራ እንዳለ እና የኢትዮጵያ ወጣቶች ነጻ እና ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ትግል ላይ ያሏቸውን ህልሞች እና ተስፋዎች ለእኛ ለወገኖቹ ለማካፈል ነው፡፡
በአሜሪካ ከተሞች ለሰማያዊ ፓርቲ ስብሰባዎች በተያዙ ፕሮግራሞች ሁሉ በመገኘት በኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ ለውጥ እንዲመጣ ለሚታገሉት ባለራዕይ ወጣቶች ለይልቃል፣ ለሰማያዊ ፓርቲ አባላት እና ለንቅናቄው ድጋፍ ሰጭ ጀግኖች ወጣቶች አቀባበል ማድረግ እንዳለብን ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡ በከተማው የስብሰባ አዳራሽ የሚካሄዱትን ስብሰባዎች ወጣት መሪዎች እንደእነ ይልቃል፣ እስክንድር፣ አንዷለም፣ ርዕዮት እና ሌሎች ብዙዎቹ በግል ያደረጓቸውን የጀግንነት ስራዎች በማወደስ ብቻ የምናልፈው ሳይሆን በአዳራሹ ማክበር ያለብን ሌሎችም ወጣት ጀግኖች በአደባባይ በመንገዶች በመውጣት ተቃውሟቸውን እንዲህ እያሉ ላሰሙት ጭምር ነው፣ “አንለያይም! አንለያይም!“ (እንደተባበርን እንኖራለን!) ወይም ኢትዮጵያ፣ አገራችን! ኢትዮጵያ፣ አገራችን! (ኢትዮጵያ፣ የእኛ አገር!)፡፡ (አንለያይም! አገራችን፣ ኢትዮጵያ! በማለት ወጣቶቹ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ሲጮኹ ስሰማ ሁልጊዜ ይነሽጠኛል፡፡)
የሰማያዊ ፓርቲ መሪ ይልቃል እዚህ በመካከላችን መገኘቱ ለእኔ እ.ኤ.አ በ2005 በተደረገው ምርጫ የተጭበረበረውን ድምጽ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተው በአምባገነኑ መሪ ትዕዛዝ በታጣቂዎች በግፍ ያለቁት ወጣቶች እንዳልሞቱ የሚያደርግ ኩራትን በመፍጠር እለቱን እንድናስታውሰው ያደርገናል፡፡ ይህ ዕለት የህግ የበላይነት ምንም ይሁን ምን መቀጠል እንዳለበት እና ለነጻ እና ለፍትሀዊ ምርጫ ዕውን መሆን በሰላማዊ ትግል ሲፋለሙ ለነበሩት እና በግፍ ለተገደሉት ወጣቶች መታሰቢያ ይሆን ዘንድ የይልቃል በመካከላችን መገኘት ሕያው ምስክር ነው፡፡
ለሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ ምን ማድረግ እንችላለን? የተሸለ ጥያቄ ሊሆን የሚችለው ለወጣት ጀግኖቻችን፣ ሲፋለሙ ህይወታቸውን ላጡት፣ በእስር ቤት በመማቀቅ ላይ ለሚገኙት፣ የግርፋት ስቃይ እየተፈጸመባቸው ላሉት፣ በየዕለቱ ማስፈራራት ለሚፈጸምባቸው፣ ስቃይ እና ውርደት ለሚፈጸምባቸው  ምስጋናችንን፣ ክብር መስጠታችንን እና አድናቆታችንን እንዴት ነው መግለጽ የምንችለው? የሚል ይሆናል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ ማግኘት የሚችለውን ማንኛውንም ድጋፍ ማግኘት ይፈልጋል፡፡ የሞራል ድጋፋችንን ይፈልጋሉ፡፡ የእኛን ማበረታታት ይፈልጋሉ፣ እኛ በእነርሱ ላይ እምነት ያለን መሆኑን ማወቅ ይፈልጋሉ፡፡ ከሁሉም በላይ ወጣቶችን በሙሉ ለመድረስ እንዲችሉ፣ ለትምህርት እና ለግንዛቤ መፍጠሪያ ፕሮግራሞች ማስፈጸሚያ ሊውሉ የሚችሉ ከእኛ የማቴሪያል ድጋፍ ይፈልጋሉ፡፡ ድርጅታዊ ህልውናቸውን ለማጠናከር እና በመላ አገሪቱ ቀጣይነት ባለው መልኩ መንቀሳቀስ እንዲችሉ የእኛን የማቴሪያል ድጋፍ ይፈልጋሉ፡፡ ጠንካራ የህግ መከላከያ ገንዘብ ለማግኘት የእኛን ድጋፍ ይፈልጋሉ፡፡ በአፍሪካ አህጉር አላግባብ በበለጸጉ፣ ሙስናን በሚያራምዱ እና ምህረትየለሽ አምባገነኖች ላይ ትግል ለማድረግ የማቴሪያል ድጋፍ ይፈልጋሉ፡፡
ለሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ የምናደርገው የገንዘብ ድጋፍ በሰላማዊ ትግል ለፍትህ፣ ለእኩልነት፣ ለዴሞክራሲ እና ለሰብአዊ መብቶች መጠበቅ የሚያደርጉትን በቅርብ በመደገፍ ምስጋናቸንን በማቅረብ ከጎናቸው መሆናችንን ለመግለጽ ነው፡፡ ለሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ ያለን ስጦታ ሰላሟ በእራሷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለማየት ሀብትን ማፍሰስ ነው፡፡ እንሰጣለን፣ እንለግሳለን፣ በዚህም መሰረት ቀጣዩ የኢትዮጵያ ትውልድ በእኛ ስህተት እና ድንቁርና በተፈጠረው ሁኔታ ሳይቸገር በአዲሲቱ ኢትዮጵያ በሰላም ይኖራል፡፡ የእኛን ወጣት ትውልድ መደገፍ የእያንዳንዳችን እና እንደሀገርም የማህበረሰባችን ኃላፊነት ነው፡፡ እኛ ልጆቻችንን፣ ሁሉንም በኢትዮጵያ ያሉ ወጣቶችን ካልረዳን… ማን እንዲረዳ ይፈለጋል?
ሰማያዊ ፓርቲ ለእኛ ምን እንደሚያደርግልን እንጠይቅ፣
እ.ኤ.አ በኦገስት 2012 በአንድ ትችቴ ላይ “የአቦሸማኔው ትውልድ፣ የጉማሬው ትውልድ” በሚል ርዕስ እንዲህ ስል ጠየቅሁ፣ “ኢትዮጵያን ሊጠብቅ ሊያድን የሚችል ማን ነው?“ በሰላማዊ መንገድ በኢትዮጵያ ለውጥ ለማምጣት መከተል ያለብን መንገድ አገራዊ ውይይት ማድረግ እንደሆነ የኢትዮጵን ወጣቶች ተማጽኛለሁ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አቤቱታዬን ለበርካታ ጊዚያት በተደጋጋሚ ሳቀርብ ቆይቻለሁ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄን በመጀመሪያ በተጠናከረ መልኩ በእራሳቸው በፓርቲው አባላት ላይ በቀጣይም በመላው የኢትዮጵያ ወጣት ማህበረሰብ ላይ የዕርቅ ውይይት ማድረግ እንደሚያስፈልግ ጥሪ አቅርቤ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የዕርቅ ውይይት በኢትዮጵያ የወጣቱ ህብረተሰብ ውይይት መጀመር ቀጥሎ የሚፈጸም ይሆናል የሚል እምነት አለኝ፡፡
የኢትዮጵያ የአቦሸማኔ ትውልድ እራሳቸውን ማጠናከር አለባቸው፣ የእራሳቸውን የፖለቲካ እና የማህበራዊ ቦታ መፍጠር አለባቸው፡፡ አገራቸው ከአምባገነንነት ወደ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በሰላማዊ መንገድ ሽግግር ማድረግ እንድትችል የእራሳቸውን አጀንዳ በመቅረጽ ወጣቶቹ ዘርፈ ብዙ ውይይቶችን መጀመር አለባቸው፡፡ የቋንቋ፣ የኃይማኖት፣ የጎሳ፣ የጾታ፣ የክልል እና ወዘተ ገደብ ሳይኖር ወጣቶች የእራሳቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ የዘመቻ እቅድ ማዘጋጀት እና በወጣቱ ማህበረሰብ ዘንድ ንግግሮችን ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡ ውይይቶቻቸው ግልጽ በሆኑ መርሆዎች፣ በእውነት፣ በዴሞክራሲያዊ ተግባሮች እና በነጻነት እና በሰብአዊ መብቶች መከበር ላይ የተመሰረቱ መሆን አለባቸው፡፡ ከፍርሃት እና ከጭፍን ጥላቻ ነጻ ሆነው መወያየት አለባቸው፡፡ ሆኖም ግን በመከባበር እና በሰለጠነ መንገድ መከናወን ይኖርበታል፡፡ ከሁሉም በላይ የአቦሸማኔው ትውልድ የውይይት ሂደቱን “የእራሱ” ማድረግ አለበት፡፡ የአቦሸማኔው ትውልድ በሚሰበሰብበት ጊዜ የጉማሬው ትውልድም ይገኛል፣ ነገር ግን በዝምታ  ማዳመጥ ነው ያለባቸው:: ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል በቀላሉ ለማታለል የሚችሉ መሰሪ የጉማሬው ትውልድ አበጋዞች ስለሚኖሩ ምንጊዜም ቢሆን የአቦሸማኔው ትውልድ ነቅቶ ባይነ ቁራኛ ሊጠብቃቸው ይገባል፡፡ በአረብ የለውጥ አመጾች/Arab Spring እንደታየው ሁሉ ወጣቶች በወጥመድ ተይዘው የታዩባቸው ሁኔታዎች ስለነበሩ የኢትዮጵያ ወጣቶችም በወጥመዶች እንዳይጠለፉ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው፡፡ በመጨረሻም በማታለል የተካኑት የጉማሬው ትውልድ አባላት ወጣቶችን ከጨዋታ ውጭ እንዲሆኑ፣ እንዲጭበረበሩ፣ እንዲደለሉ ያደርጓቸዋል፡፡ መጠንቀቅ ተገቢ ነው::
የዕርቅ ወይይቶች በድንገት እና ተራ በሆነ መልኩ በወጣት የመብት ተሟጋቾች መካከል መጀመር እንዳለባቸው አምናለሁ፡፡ ለምሳሌ እንደዚህ ያሉ ውይይቶች በሚግባቡ እና ተመሳሳይነት አስተሳሰብ ባላቸው የሰብአዊ መብት ተሟጋች ወጣቶች መካከል በመንደር ወይም በጎረቤት ደረጃ መካሄድ ይችላሉ፡፡ ወጣት የሰብአዊ መብት ተሟጋች ወጣቶች አቅማቸውን፣ ያላቸውን እምቅ ኃይል፣ ዕድሎችን እና ችግሮችን ለይተው በማውጣት ዕቅድ ነድፈው ትናንሽ ህብረተሰብ አቀፍ የዕርቅ ውይይቶችን ማካሄድ ይችላሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት ያሉትን ድርጅቶች፣ ተቋሞች፣ ማህበራትን እና መድረኮችን በመጠቀም ወጣት የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች የዕርቅ ውይይቶችን በማካሄድ የወጣቶችን ግንዛቤ ማሳደግ  ይችላሉ፡፡
የዕርቅ ወይይት መነጋገርን ብቻ አይደለም የሚያካትተው ነገር ግን እርስ በእርስ በንቃት መደማመጥን ጭምር እንጅ፡፡ ወጣቶች ከኢትዮጵያ ብሄረሰቦች እርስ በእርስ በመማማር የእራሳቸውን ብዙሀንነት ማጠናከር ይችላሉ፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ የአቦሸማኔ ትውልድ ከጉማሬው ትውልድ ስህተቶች እና ከሌሎች አገሮች ወጣቶች ልምዶችም ለመማር ይችላሉ፡፡ የኢትዮጵያ አቦሸመኔ ትውልድ የሚያደርጓቸው የዕርቅ ውይይቶች በመርህ ላይ የተመሰረቱ እንዲሆኑ አጥብቄ እማጸናለሁ፡፡ ወጣቶች ደስተኛ ባልሆኑባቸው ነገሮች ላይ መቃወም መቻል አለባቸው፡፡ በነገሮች ላይ አለመስማማት ማለት የዕድሜ ልክ ጠላት መሆን ማለት አይደለም፡፡ የሰለጠነ ውይይት ማድረግ ለጉማሬው ትውልድ ከባድ ቢሆንም ለአቦሸማኔው ትውልድ ግን በጣም አስፈላጊ ነገር ነው፡፡
ምነው ዝምታ?
“ዓለም አቀፍ ማጭበርበር በተንሰራፋባት ምድር ላይ“ ዝምታ ከቃላት እና ከስዕል የበለጠ ይናገራል፡፡ ማርቲን ሉተር ኪንግ እንዲህ አሉ፣ “በመጨረሻ የምናስታውሰው የጠላቶቻችንን ቃላት አይደለም፣ ነገር ግን የጓደኞቻችንን ዝምታ እንጅ“፡፡ ይህንን ትችት ካጠናቀቅሁ በኋላ “ስለጓደኞቻችን” “ዝምታ” መናገር አለብኝ፣ ምክንያቱም አንዳንድ ጊዜ ዝምታ ከመናገር የበለጠ የመግለጽ ችሎታ አለው፡፡ የኢትዮጵያ ወጣቶች ፓርቲ መሪ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ በመጡበት ጊዜ እና እስከ አሁን ድረስ ለበርካታ ዓመታት ታይቶ በማይታወቅ መልኩ እጅግ ብዙ ኢትዮጵያውያን ታዳሚዎች በተገኙበት ስብሰባ ላይ የወጣቶቹ መሪ ንግግር በሚያሰሙበት ጊዜ ትኩረትን በሚስብ መልኩ የአሜሪካ ድምጽ ወኪል ጋዜጠኛ ሳይገኝ ቀርቷል፡፡ የአሜሪካ ድምጽ ድርጊቱን ለመዘገብ አንድም ጋዜጠኛ ሳይልክ ቀርቷል፡፡ የአሜሪካ ድምጽ ዜናውን ለመዘገብ ለምን እንዳልተገኘ የማውቀው ነገር የለም፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ስብሰባ ግን ከተለያዩ የኢትዮጵያ ስፖርቶች፣ ባህላዊ፣ አካዳሚያዊ እና የማህበረሰብ ስብሰባዎች እንዲሁም የመጽሀፍት ርክክብ ፊርማ ስነስርዓት ሲኖር የአሜሪካ ድምጽ በሳምንቱ መጀመራያ እና በሳምንቱ ማጠቃለያ በዋሽንግተን ዙሪያ አካባቢ ሰፊ ሽፋን ሰጥቶ ከሚዘግበው የሚያንስ አለመሆኑን በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ፡፡ ምናልባትም ሰማያዊ ፓርቲ እና የኢትዮጵያ ወጣቶች ለአሜሪካ ድምጽ ምንም ያልሆኑ ቀላል ነገሮች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ የአሜሪካ ድምጽ ለወጣቶቹ ግድ ላይኖረው ይችላል፣ የኢትዮጵያ ወጣቶችም ለአሜሪካ ድምጽ ጉዳያቸው አይደለም፡፡
የአሜሪካ ድምጽ እንዲገነዘበው የምፈልገው ነገር ግን በሟቹ በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዝናዊ “ኢትዮጵያ  ላይ ዘር ማጥፋት” ፕሮፓጋንዳ አካሂደዋል የሚል ክስ በይፋ ባስታወቀበት ጊዜና ሌላም ጊዜ ወንጭፋቸውን ሲያነጣጥሩባቸው እና ቀስቶቻቸውን ሲቀስሩባቸው በነበረበት ወቅት ከእነርሱ ጎን ቆሜ ነበር፡፡ በዚያ ውንጀላ ጊዜ የአሜሪካ ድምጽ በጽናት ለመርህ የቆሙ መሆናቸውን፣ ለሙያው ክብር ሰጥተው ይዘግቡ እንደነበር፣ ያለአድልኦ እንደሚሰሩ ጊዜን አክብረው ደግመው እና ደጋግመው እንደሚዘግቡ ሽንጤን ገትሬ ተከራክሪያለሁ፡፡ የአሜሪካ ድምጽ በሰማያዊ ፓርቲ ጉባኤ ላይ በመገኘት እንደ ድሮው ሁሉ በጽናት ለመርህ ቆመው፣ ለሙያው ክብር ሰጥተው እና ያለአድልኦ የጉባኤውን ሂደት እንደሚዘግቡ እጠብቅ ነበር፡፡ ምናልባትም ኢትዮጵያውያን በአሁኑ ጊዜ የአሜሪካ ድምጽ የሚለውን ስያሜ የዝምታ ድምጽ ተብሎ መጠራት ጀመረ ወይ ብለው እየጠየቁ ይሆናል፡፡ የዝምታ ድምጹን ለመስማት እንቀጥላለን፣ ሆኖም ግን በዝምታ አይደለም የምንሰማው፡፡
ከዚህ በኋላ ዝምታ መኖር የለበትም፣ ድምጻችንን ከፍ አድርገን እንጩህ እና ለሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ ድጋፋችንን እናሳይ፣ ዝምታን ከዚህ በኋላ እናቁም፡፡ ለሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ ድጋፋችንን በይፋ እናውጅ፡፡ ቀጥ ብለን እንቁም እና በእነርሱ እንኩራ፡፡ ለሚያካሂዱት ሰላማዊ እና ግጭት አልባ የስርዓት ለውጥ ትግል አድናቆታችንን በመግለጽ ድጋፋችንን እንስጥ፡፡ ወደ ነጻነት የሚወስደው መንገድ የቱንም ያህል ረዥም ጉዞ ቢፈጅ ከእነርሱ ጋር መሆናችንን እናረጋግጥላቸው፡፡ ወጣቶቹ በመጨረሻም ድልአድራጊዎች ይሆናሉ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ አባላትን እንደምንወዳቸው በተግባር እናረጋግጥላቸው!
የኢትዮጵያ ወጣቶች ተባበሩ፣ በፍጹም እጅ እንዳትሰጡ፡፡ ኃይል ለኢትዮጵያውያን/ት ወጣቶች!
ታህሳስ 15 ቀን 2006 ዓ.ም

“ሞት እንዳለ ባውቅም፤ መሞት ግን አልፈልግም!” ብላ ነበር ሚካያ በሃይሉ

ምጻዊት ሚካያ በሃይሉ ከትላንት በስትያ ታህሳስ 16 ቀን ህይወቷ አልፎ፤ የቀብር ስነ ስርአቷ ተፈጽሟል። መልካም ስራዋ ግን ከኛ ጋር አብሮ ይቆያል። እኛም ሚካያን ለማስታወስ ያስችለን ዘንድ፤ ወደ ኋላ ተመልሰን የቀድሞ ፋይላችንን ማገላበጥ ጀመርን። ከሶስት አመት በፊት፤ በሚያዝያ ወር 2002 ዓ.ም. ከሚካያ ጋር አንድ ቃለ ምልልስ ተደርጎ ነበር። ይህንን ቃለ ምልልስ ከአዲስ አበባ ተቀብለን በዚሁ ድረ ገጻችን ኢ.ኤም.ኤፍ ላይ ለህትመት አብቅተነው ነበር። ቃለ ምልልሱን ያደረገችው ከጋዜጠኛ አቤል አለማየሁ ጋር ሲሆን፤ ከሶስት አመታት በፊት ለህትመት ያበቃነውን ጽሁፍ በድጋሚ አቅርበነዋል።
ቃለ ምልልሱን በፒ.ዲ.ኤፍ ያንብቡ። ለማንበብም እዚህ ላይ ይጫኑ። ለማንበብም እዚህ ላይ ይጫኑ።

Mikaya Behailu
Mikaya Behailu

ዓረና-መድረክ በትግራይ – ከሽሬ ህዝብ ጋር ሊወያይ ነው

የዓረና መድረክ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ እንዳሳወቀው፤ ከሽሬ ህዝብ ጋር በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ለመመካከር ለእሁድ ታህሳስ 20, 2006 ዓም በሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ህዝባዊ ስብሰባ መጥራቱን ገልጿል። የዓረና አመራር አባላት በሽሬ እንዳስላሴ ከተማና አከባቢው ቅስቀሳ ጀምረዋል። ስብሰባው ከጠዋቱ ሦስት የሚጀምር ሲሆን በከተማ ልማት አዳራሽ ይደረጋል።
የህዝብ ግንኙነት ሃላፊው እንደገለጸው፤ የሽሬ ህዝብ ፅኑ ሲሆን በትጥቅ ትግሉ ዋነኛ ተካፋይ ነበር። በህወሓት ትግል ወቅት ከፍተኛ መስዋእት ከከፈሉ የትግራይ አከባቢዎች በቀዳምነት የሚጠቀስ ሲሆን በልማታዊ ተጠቃሚነት ግን የመጨረሻ ደረጃ ከሚይዙ አከባቢዎች ይሰለፋል።
ሽሬዎች ህወሓትን ተንከባክበው አሳደጓት። ህወሓት ስልጣን ከያዘች በኋላ ግን ተመልሳ ሽሬዎችን ጎዳች። ህወሓት ለሽሬ ከተማ የውኃ አገልግሎት ለማቅረብ ሃያ ሦስት ዓመት ፈጀበት። አሁንም ችግሩ አልተፈታም።
መቼም የሽሬን ሰው ማስፈራራት አይቻልም። የህወሓት ካድሬዎች እንደለመዱት ህዝቡ በስብሰባ እንዳይሳተፍ ለመከልከል ምን ያደርጉ ይሆን? አብረን እናያለን።
“እሁድ ጠዋት በሽሬ ከተማ እንገናኝ።” በማለት መልእክቱን አስተላልፏል – የዓረና መድረክ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ፣ አቶ አብርሃ ደስታ።

Fear And Loathing In Ethiopia: Groups, Individuals Cite Government Abuse In New Opposition Party Report (WS



Members of this northeast African nation’s most prominent opposition party say they weren’t doing anything wrong one day in late September when police officers came along to stop, question and detain them.
Several members of the group had gathered in Kazanches, a central neighborhood in Ethiopia’s capital city of Addis Ababa, to hand out flyers and promote a Sept. 29 demonstration. Having already secured governmental permission for their upcoming protest, they expected no interference.
“I don’t know why, and I don’t know who ordered them, but some police officers came and told us to stop distributing the brochures,” opposition activist Daniel Tefera told IBTimes. “I said, ‘This is our constitutional right, and you have no right to stop this.’ But two policemen called another five policemen and without any reason, they took us to the police station. We were arrested for four hours.”
Tefera is the communications officer for the Unity for Democracy and Justice, or UDJ. The party, which is part of Ethiopia’s largest opposition coalition, Medrek, is one of several that accuse the government of stifling political dissent. UDJ recently became the first to lay out the details of the ruling party’s alleged abuses in a 39-page formal report that is full of stories like Tefera’s.
“Since it has taken power, the current government of Ethiopia has been harassing its people in different locations and times,” the report claims. “Usually those people whose human rights are abused are members of opposition political parties and their advocates.” The document goes on to give accounts of more than 150 alleged human rights abuses committed against party members and other civilians since 2010. Most involve arbitrary detention, but some point to beatings, torture, religious persecution and even civilian deaths as a result of relocation efforts.
The scores of victims mentioned include Getu Mekicha, a party officer in Gojjam, who in February of this year was robbed of about 150 birr ($8) and kicked severely by a local official, breaking his hand; Gezahagn Mekonen, a party member who was “snatched forcefully” from his Oromia residence in October 2012, rendering his entire family homeless; and Abebe Akalu, a public relations worker for UDJ, who was arrested in October this year. The report claims that while in custody, Abebe was forced to consume alcohol, frightened with a pistol, beaten and threatened that “unless he stops his peaceful political struggle, he will be blamed as a terrorist who is trying to overthrow the government and at risk of life imprisonment.”
In some cases, the alleged abuses have resulted in social and economic ostracism. Party member Beshir Basaye was distributing opposition literature in Oromia when he was arrested in March of 2012, according to the report, and detained for more than four months. Upon his successful appeal and subsequent release, he tried to resume his work in wholesale coffee trade. But the report claims that “the local cadres are making a campaign to the local coffee producers not to supply coffee to him. In doing so, the officials are causing great problems in the livelihood and existence of the [victim].”
The document, written in Ethiopia’s official language, Amharic, was first unveiled at a UDJ press conference on Oct. 31 but was not finalized and published online until a few days later. It was hand-delivered to the prime minister’s office on Dec. 2, but party chairman Negasso Gidada wasn’t sure the report would get much of a reception there. “When they see it comes from UDJ, they might throw it in the rubbish bin!” he told IBTimes. “I don’t think they will react.” Negasso served as president of Ethiopia from 1995 to 2001 but fell out with the ruling coalition months before his term ended. He formally joined UDJ in 2009 in order, he says, to bring about a more transparent, democratic system of governance and to help unify the country.
As it turned out, UDJ’s report did get a reception at the prime minister’s office this month, albeit a cool one. “We’re a very responsible government, so we have to look into the allegations made by UDJ,” said government spokesman Getachew Reda in a phone interview. “The reading of the report suggests that it’s more innuendos and unsubstantiated claims. We have to get all the details before we respond to every specific allegation, but these are the same claims that have been regurgitated by opposition groups for years.”
Political opposition groups have a complicated history in Ethiopia, which boasts one of Africa’s fastest-growing economies and its second-largest population. The ruling coalition, the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front, or EPRDF, first coalesced as a rebel group fighting against the socialist Derg administration. It came to power in 1991 and hasn’t lost control of the Ethiopian political scene since. A controversial election rocked the country in 2005, when early results predicted massive gains for the Coalition for Unity and Democracy, then the most prominent opposition group. After the much-delayed final results delivered a majority to the EPRDF, riots ensued in Addis Ababa, a CUD stronghold. Tens of thousands were arrested, and more than 200 people lost their lives.
Since then, the ruling party hasn’t faced any serious political challengers. The 2010 elections were largely peaceful, and UDJ now occupies only one seat in the national parliament.
After years of civil war and a devastating famine, developmental progress under EPRDF has been plainly evident – especially in Addis Ababa, a bustling city that boasts low crime rates, ongoing infrastructural projects and the African Union headquarters. National economic growth has averaged 10.6 percent annually over the past 10 years, though it slowed to 9.7 percent in the fiscal year ending this July. Outside of urban areas, that growth isn’t always apparent; more than one-fourth of the population lives in poverty, and about 85 percent of Ethiopians work in agriculture, much of it subsistence. The ruling party aims to promote broad-based growth by investing heavily in infrastructure and commercial agriculture projects, and an uncompetitive political environment makes it easier to pursue those initiatives. But opposition leaders argue that although a state-driven economy may work for Ethiopia, a state-driven democracy is unsustainable.
National security concerns also constrain Ethiopia’s political arena. The government passed a sweeping anti-terrorism law in 2009, and critics – including international organizations like Human Rights Watch and Amnesty International – have condemned the measure for enabling crackdowns on opposition parties and members of the media. HRW reports that at least 11 journalists have been sentenced under the law since 2011, and at least three are now in prison. Negasso charges that the EPRDF has used the anti-terrorism law to target political activists, noting that several of the victims described in the UDJ report are now behind bars indefinitely.
The report says that in Sept. 2010, the year after the law was passed, party members Andualem Aragie and Natinael Mekonen were arrested on charges relating to terrorism. Both were detained, and UDJ accuses security forces of subjecting the men to “beating and torture, detaining them in dark room for a long period of time [and] preventing them from getting sufficient medical treatment.”
The suspects were eventually freed, but some cases are still ongoing. In February of this year, for instance, party member Alemu Tafesse was arrested on suspicion of involvement in a terrorist plot on Kemisie, a town in South Wollo where human rights violations are frequent, according to UDJ. The report notes that although Alemu remains behind bars a full 10 months after his arrest, his case has never been presented in court.
“We are against terrorism, so we say our country may have an anti-terrorist law – just not the kind of law that is now existing,” said Negasso. “We want it to be discarded and be replaced by another anti-terrorist law, and the victims of the 2009 anti-terrorist law who were imprisoned – party members and journalists – must be released immediately.”
UDJ’s report comes at an interesting time. The next national elections are in 2015, and opposition groups have been increasingly active lately. This year, a major demonstration was held in Addis Ababa for the first time since 2005. Thousands of demonstrators participated in a march across the capital city in an event organized by Semayawi, or the Blue Party, which is not a member of the Medrek coalition. The party tried to hold another demonstration on Sept.1, but their request to organize was denied and Semayawi officials accused the government of arresting about 100 party members and confiscating equipment. UDJ’s more successful demonstration – the one Daniel was arrested for promoting – came later that month. Semayawi organized another protest in November, this one at the Saudi Arabian embassy to condemn the Gulf country’s ongoing deportation of tens of thousands of illegal Ethiopian workers. But it was shut down by police before it began, leading to the arrests of several party members because the gathering had not been authorized by the government. Medrek officials were gearing up for yet another demonstration earlier this month, but they backed down when the government would not permit them to march on their planned route alongside the parliamentary building.
Now that the UDJ report has been made public, Negasso hopes it will bring even more attention to the complaints of opposition activists. He says the document has been sent to regional officials, the national ombudsman, the Ethiopian Human Rights Committee, Human Rights Watch and Amnesty International.
Government spokesman Getachew says the report won’t be ignored by government officials. “What we have to do is correspond with our people on the ground. We can’t rule out the possibility of some off-the-grid functionary acting in a manner that runs counter to the constitution,” he said, adding that the government may pursue investigations into the allegations within the coming weeks.
But after years of pushing for change with little to show for it, most opposition members remain skeptical. “It is always the same,” said Daniel. “I don’t expect any change from the government.”

Time to Bring Eritrea in From the Cold

By Hank Cohen,  AllAfrica 
Prime Minister Meles Zenawi and President Isaias Afwerki signing a peace agreement in Algieria 2000.
The late Meles Zenawi and Isaias Afwerki of Eritrea signing the Algiers Agreement, a document maily the work of Meles Zenawi to nail Ethiopia as a landlocked country for ever.  
Editor's Note - In 1991, when the Derg fell, US peace mediator Herman Cohen reportedly favored that Eritrea keep Massawa while Port of Assab remain with the much larger neighbor, Ethiopia. The enemy to Cohen's proposal was the late Meles Zenawi, an Eritrean mercenary from Adwa. He is largely credited with turning TPLF rebels into enemy soldiers that would fight against their own country. When war broke out in 1998, which was largely the making of Mr. Zenawi's "appeasement policy" toward his country, Eritrea, the Tigrians couldn't find the gut to remove the enemy who had misruled Ethiopia for nearly eight years. TPLF officials said they didn't want to show "division" to the enemy (in this case, Eritrea) and sought "unity" that kept Meles in power.
Actually, they were scared to remove Meles from power, eventhough they were aware that he would no doubt help Eritrea win the war over Ethiopia; eventhough they were aware that the entire Ethiopia people would erupt with joy and celebration that finally the enemy within is caught and brought down to justice.
Calls from Tigrians in North America (who were members of a now-defunct TigraiNet forum] for the removal of Meles Zenawi fell on deaf ears. Meles kept a low profile and helped win over Badme (a battle) as a confidence-building measure before he gets time and strike back without mercy. He waited for another more year, and aborted a victory-laden final offensive (killed the war) that was sending Eritrean soldiers in disarray over the border to the Sudan.
The BBC or Reuters asked Cohen what would be the next step of the 'triumphant Ethiopians.' Cohen said the Ethiopians will right the wrong, and reclaim the all-important Port of Assab, a sharp remark which deprived Meles a good night's sleep.
Right the next morning, Mr Meles Zenawi called for a press conference in Addis, and without quoting Cohen, dismissed Cohen's claims as baseless. "Ethiopia will never take an inch of an Eritrean territory [let alone Assab Port]," he asserted.
After Meles sabotaged a clear Ethiopian military victory, TPLF officials half-heartedly tried to accuse their boss of "treason." With one strike, Meles turned them to dust, and emerged an undisputed strongman. In August 2012, Meles was taken care of by a divine power, but to this day, failed-state Ethiopia remains in the hands of his disciples, masked mercenaries who deceptively call themselves 'Woyane.'
Though Meles has died, the TPLF officials [not the Eritreans crowding the TPLF poliburo], are skeptical that Meles has really died, because no one is daring to write the true history how a generation of Tigrians were reduced to foot soldiers, and fought a war that made their country landlocked.
Below is a piece by Herman Cohen over the Ethiopia-Eritrea stand-off. Write us what you feel. Thanks.


After being part of Ethiopia for forty years, the people of Eritrea held a referendum in April 1993 and decided to establish an independent state.
The referendum took place in the aftermath of a thirty-year insurgency against two successive Ethiopian regimes waged by the Eritrean Peoples Liberation Front (EPLF).
At the same time, an allied insurgent group, the Tigrean Peoples Liberation Front (TPLF), took over power in the Ethiopian capital, Addis Ababa, after the military collapse of the Soviet-supported regime headed by President Mengistu Haile Mariam.
Between 1993 and 1998, the two "brother" governments of Eritrea and Ethiopia, headed by the EPLF and TPLF, enjoyed excellent relations.
They maintained a common economic system that allowed landlocked Ethiopia full access to the Eritrean Red Sea ports of Asab and Masawa, including control of their own handling facilities for the transit of cargo.
The relationship started to cool in 1997 when the Eritreans created their own currency, the Nakfa. They did this without arranging to establish a system of daily settlements for cross border trade between their currency and the Ethiopian Birrh. This could have been done through a facility provided by the International Monetary Fund.
Without such a facility in place, the Ethiopian Government announced that all cross border trade had to be settled in US Dollars. This resulted in a financial setback for Eritrea because of its limited access to hard currencies.
In 1998, the Eritrean Government complained that Ethiopian government representatives, including police, were beginning to encroach on Eritrean territory near the border town of Badme in southwest Eritrea. According to Eritrean sources, four of their police officers who went to Badme to investigate turned up dead.
Again, the Eritreans said that they had no choice but to retaliate with military force against the alleged Ethiopian encroachments and murder of their policemen.
The Ethiopian Government denied all of the Eritrean allegations about encroachments and the killing of Eritrean policemen, claiming that the Eritrean military attack was totally unjustified.
Instead of negotiations, the Eritrean action triggered a massive Ethiopian armed response, unleashing a major bilateral war that lasted two years, and that caused approximately 100,000 dead and wounded on both sides.
Under Algerian Government mediation, a cease-fire was accomplished in 2000. In view of the border as the ostensible main issue in contention, the Algerians established the Ethiopia-Eritrea Border Commission (EEBC) to arbitrate the exact boundary line. While the EEBC was doing its work, the long border remained heavily armed on both sides.
The results of the EEBC arbitration upheld Eritrea's main claims on the border delineation. The Ethiopian Government made a public statement agreeing to the arbitration result, but insisted that it would not proceed to delineate the final border settlement until they could have bilateral discussions with Eritrea.
The Government of Eritrea declared that it was open to discussions without any preconditions, but insisted that Ethiopia first had to delineate the border pursuant to the arbitration decision. This total stalemate in the bilateral relationship has continued until the present, with both governments holding to their inflexible positions.
Because of the stalemate, the border has remained heavily armed on both sides. This situation has caused particular hardship to Eritrea. Because of the country's small population, young men conscripted into the armed forces to patrol the long border have had to serve for indefinite periods without knowing when they would be demobilized and returned to their families.
As a result, over the past decade thousands of young Eritrean have 'illegally' left their country to seek asylum in the other countries, including Ethiopia, Egypt, Israel, the Emirates and southern Europe.
In addition to the expensive armed camps on both sides of the border, the situation of 'no peace - no war' has resulted in a total stoppage of cross border trade, and the loss to Ethiopia of Eritrea's convenient nearby ports for Ethiopia's exports and imports.
Ethiopia's only access to the ocean since the war began has been via the 900 mile antiquated railway from Addis Abeba to the port of the neighboring country of Djibouti at the entrance to the Indian Ocean from the Red Sea. In addition to the long distance between Djibouti and Addis Abeba, port fees in Djibouti are excessively high.
To make matters worse, both Ethiopia and Eritrea have become ensnarled in the chaos of Somalia since that government collapsed in 1991.
The rise of the Islamist group Al Shabab, with abundant assistance from al-Qaeda in the Arabian Peninsula caused Ethiopia to send troops to Somalia at various points from 2006 to the present day.
Between 2006 and 2010, the security crisis in Somalia has caused relations between Eritrea and the United States to deteriorate badly. In 2008, the George W. Bush Administration declared Eritrea to be a "state sponsor of terrorism", thereby triggering US trade, investment, and travel sanctions against Eritrea and its leaders.
The reason was the identification of Somali Islamist extremists attending a Somali political dialogue meeting in Eritrea. Indeed, this caused the US Government to become so enraged that the American Assistant Secretary of State for Africa expressed to desire to reopen the EEBC arbitration decision in order to favor the Ethiopian border claims. This request was not adopted.
The Obama administration accused the Eritrean Government of allowing the transit of arms to Al-Shabab - the reason for this alleged support being that Eritrea wanted to help an enemy of Ethiopia, thereby putting pressure on its neighbour to implement the arbitration decision.
In 2009, Senior Etritrean officials met in Rome with the American Permanent Representative to the UN, Susan Rice, and the US Assistant Secretary of State for Africa, Ambassador Johnny Carson.
The American delegation was apparently not satisfied with the Eritrean rebuttal of the allegations about their allowing the transit of arms to Shabab.
There were also accusations of Eritrean support to insurgents opposing the Ethiopian regime from within. As a result, Ambassador Susan Rice introduced a resolution in the UN Security Council calling for sanctions against Eritrea.
The resolution, UNSC 1907, was enacted in a watered down version of the original harsh US draft, but nevertheless caused Eritrea to become something of an international pariah. This situation continues.
However, as far as external support for Shabaab is concerned, all available intelligence indicates that Eritrea has not had any contact since 2009.
Earlier intelligence reports, denied by Eritrea as fabricated, indicated Eritrean facilitating the transfer of funds to Shabaab - nothing of that sort has been reported since 2009 by any source. Those of us who know Eritrea well understand that the Eritrean leadership fears Islamic militancy as much as any other country in the Horn of Africa region.
In recent months, positive signals have been coming from both countries. Eritrean President Isaias Afewerke has been quoted as saying that Eritrea cannot fulfill its destiny without Ethiopia.
The Prime Minister of Ethiopia, Hailemariam Desalegn, has said that he is willing to go to Eritrea to engage in dialogue. In short, the wartime tensions of 1998-2000 no longer have a logical basis for continuing to exist. Normalization of Ethiopian-Eritrean relations promises a win-win future for both nations.
In view of the absence of any intelligence, real or fabricated, linking Eritrea with Shabaab for over four years, the UN Security Council should terminate sanctions imposed in 2009 by UNSC resolution 1907.
Since European Union governments have maintained normal relations with Eritrea since the country's independence, one of the European members of the UN Security Council should propose a resolution to end the sanctions. The US should agree to abstain rather than veto such a resolution.
To break the stalemate between Eritrea and Ethiopia over the implementation of the EEBC boundary decision, there needs to be a mutually face-saving solution. I propose that Ethiopia offer to accept a symbolic initial takeover by Eritrea of territory awarded by the EEBC, followed by the same day opening of dialogue with a totally open agenda.
This dialogue could have the benefit of a neutral mediator, or not, depending on the wishes of the two governments. Here again, one of the neutral Europeans should have the ability to inspire confidence in both sides.
A normalization of relations, following the end of UN sanctions against Eritrea, would have immediate benefits for both countries.
A resumption of Ethiopian use of Eritrean ports would provide economic benefits to both countries with trade resuming in both directions. Both sides would also be able to demobilise the border with important cost savings.
Both countries, of course, continue to have important human rights issues. Normalization of bilateral relations would make it easier for the US and the international community to encourage political and governance reforms.
Finally, the normalization of relations between the United States and Eritrea would open the door to military-to-military cooperation of the type that would enlist Eritrea in the war against Islamic terrorism in the Horn coming from across the Red Sea.
Yes, the time has come to bring Eritrea in from the cold.
Herman J. 'Hank' Cohen is Former Assistant Secretary of State for Africa.
 

Et tu, ESAT?

by Yilma Bekele
‘Et, tu Brute?’ is what the Roman Emperor Julius Caesar was heard to have said when he saw his dear friend Marcus Brutus in league with his assassins. In English he was saying ‘you too, Brutus?’ It is said by historians that Caesar was fond of Brutus and treated him as he would a son. His betrayal must have been very painful.Mengistu Hailemariam Former Ethiopian President said “Ethiopians must free their country”
This last week I was forced to utter Et tu three times in one weak. Like Caesar was blindsided by the turnabout behavior of his friend I was completely rendered speech less by the action of those I considered dear and close. As an Ethiopian I definitely consider myself beyond surprise when it comes to news and actions of my homeland and people. What country would ever consider of robbing abused returning immigrants? In fact I have managed to develop such a thick skin that most things just bounce off barely leaving a scratch. It is not for being uncaring but a simple defense mechanism to survive. I am an Ethiopian and I suffer in silence.
The last month has been very difficult for us Ethiopians like it or not. To witness the cold blooded and ugly behavior of the Saudi Government against our people was a painful experience. Our heart goes to the victims. The shameful act of the so called Ethiopian government was a lesson on what happens when warlords, village idiots and their enablers take over a country. The Woyane mafias were more concerned about offending the Arab billionaires more than the suffering of their citizens.
To make matters worse the pride of all humans in general and Africans in particular Nelson Mandela Died. The world was a sad place. Not many Mandela’s come around this way often. Talk about Mandela completely dominated the news. The international media was looking under every nook and cranny to find anything to do with the great leader. No story was deemed irrelevant if it has anything to do with Madiba. The love for Mandela was universal.
I was sucking on Mandela lore when I came across ESAT’s presentation. They stopped me on my tracks. That is when like Caesar I said Et tu ESAT? (antem esat?) How could you mix water and oil my friend. Isn’t that what they were attempting to do? Asking an ordinary criminal, a murderer to give testimonial about a liberation fighter, a humanist, a leader by the ballot box is bizarre and insults the memory of our Madiba not to mention our poor tossed around Ethiopian existence.
The interviewer referred to criminal Mengistu Hailemariam as the former president of Ethiopia. That is totally not true. The individual was the former dictator of Ethiopia. As far as history tells us we Ethiopians have never freely elected a leader. We had hereditary kings until Emperor Haile Selassie and a successive of dictators since then. What we got today being dictator number two and half. No matter how ever much painful it was I listened to the monologue.
As I suspected it was the usual hot air with no deep analysis but your garden variety personal views presented as verifiable facts. It was déjà vu time if you remember during the hay days of the Derg era where the ‘leader’ was an expert on every subject. This was chapter two where the dictator became a historian and political scientist and gave us a lesson on the liberation movements, the international situation and the colonial era. He is entitled to his opinion but not his facts but dictators are allergic to facts thus they weave their own theory out of thin air which with the help of the gun they force all to see it their way. He must be starved for attention because one question is all he needed to run away with his rehearsed play of course with himself as the star.
To add insult to injury the criminal was asked for advice regarding the current situation of our precious homeland. This is where I got sick. I felt insulted. I shrank until I disappeared. It is like asking the arsonist about the building he just torched. May the Gods have mercy on our soul?
Thus I took my time and talked to a lot of Ethiopians on the subject of Mengistu. Some were offended like I was, a few dismissed it as a nonevent and there were a few that actually liked it. Mengistu Hailemariam dominated our people and country for a long time. His reign is remembered to be a very traumatic time for our people. He was accidentally thrust into being a leader, a position that he was not prepared or had the aptitude for. There is no need to spell out the many horrifying and cruel acts carried out by his gang which no Ethiopian escaped from.
Today we are harvesting what Mengistu sowed. Millions of relatives of his victims are still with us. There are those that lost a family member, a loved one, a neighbor, a friend whose memory is still fresh and constant reminder of those difficult days. Mengistu is our collective nightmare.
I heard him mention the Emperor and thought how cold blooded he must be talking about the person he murdered presiding as judge, jury and executioner. How callous one has to be. But we knew that. They say he is brave and decisive but he left his army behind and run away. That is the dictionary definition of a coward. He said he hasn’t killed a fly but when he was the leader blood flowed like river in the streets of Ethiopia. That is an example of a person on denial. Some claim he was patriotic, loved his country but a generation of educated were sacrificed, high ranking military officers faced the firing squad, and thousands started the exodus which hasn’t abated yet. That is what happens when you have a mad person in charge.
This is the individual that ESAT and some other obscure outfits are trying to invite to our living rooms as honorable guests that would contribute positively to the conversation. What valuable lesson could we learn from an individual that has not even come to terms with the crimes he perpetuated and has not even bothered to ask for forgiveness to the people and nation he hurt and bring closure to those that have lost their loved ones? What exactly did he tell us that we don’t know?
He said Mandela did not come to Ethiopia because he did not like Woyane’s ethnic policy. Wow is all I could say. He was brought out of the deep freeze to tell us what we already know? All this excitement to show that Madiba was not fond of the likes of the nameless warlord? I had no idea that we needed Madiba to tell us how awful Woyanes are. I am sorry ESAT that is yesterday’s news. The Ethiopian people have gone beyond that and if it was not for the network of terror cells Woyane has established on every street they would have dealt with the mafia outfit a long time ago.
What else, I am afraid nothing. Not that there could be anything more and no earthly reason to expect to be anything of value. So what is the idea of getting this has been individual to come out and disturb our peace, derail our freedom train and confuse the many young Ethiopians that have not yet made an intelligent determination on what has happened the last forty years.
May be I misunderstood. It is possible I am barking up the wrong tree. I always thought of ESAT as different. You know like a weapon of Democracy and freedom. The voice of the voiceless is what I tell people. ‘Ethiopia’s eyes and ears’ Is what is said of ESAT. Organ mal function is what my brain screamed. What happened here, and where is the disconnect? What trajectory are we heading? Are we going to be the voice of the least common denominator?
Some would try to argue about freedom of speech. Little knowledge is always dangerous. I am afraid that principle is not applicable here. I would not advocate silencing the fascist thug but at the same time I wouldn’t hand him my microphone to disperse his toxic, irrelevant and idiotic idea using my hard earned media. We welcomed ESAT to raise the level of conversation to a higher level. Diaspora Ethiopians that are by no choice of their own displaced from their mother land contribute to ESAT so it could help us inform each other, echo the cry of our people, organize to fight injustice and teach each other to love, respect and help create the future democratic Ethiopia.
Inviting the likes of yesterday abusers is not the way to go. Felling the hurt brought about by Mengistu and Meles is the first order of business. If we don’t feel each others pain we are likely to inflict pain on others. If barbaric acts by usurpers and warlords is not condemned and etched in our brain to avoid in the future aren’t we condemned to repeat history?
I was feeling sad and dejected when I came across more of the same waiting for me around the corner. It is no other than the Honorable Ato Bulcha Demeksa that made me rush to the pharmacy in search of valium or any drug that would numb my frayed nerve. In an interview on German Radio our elder father was peddling hate filled discourse on the relationship between different ethnic groups in our country. He even went to the extent of describing it as a colonial situation. A very interesting analysis when you consider our elder statesman was Minister during the time of the Emperor and a member of Parliament during Woyane rule.
You would think that age has a mellowing effect and being an elder, an experienced statesman, and a leader would make you choose your words carefully and foresee the consequences of loose speech. With all due respect I am forced to conclude the honorable gentleman made a major mistake. He gave fuel to some erratic, ego driven jihadists the perfect argument to peddle their nihilistic argument for fifteen minutes of fame.
The final straw that was trying to buckle my back was the interview with Tamrat Layne an idiot that always requires a crutch to stand up straight. Yesterday he was a Marxist that supposedly fought to get rid of military rule and build dictatorship of the proletariat. In fact he was so gung ho about it he went to the bush and raised a gun to build his new society. Upon wining he was crowned Prime Minister and sent out to disparage his own ethnic group and incite war against unarmed peasants. Needless to say when his usefulness was exhausted he made to confess to financial crimes and thrown in the dungeon.
This criminal whose hand is soiled by the blood of our family members is now living among us as a Christian preacher. Hi current crutch is no other than the holy Bible and I am afraid he is deeply immersed until the next phase of his transformation. Who knows tomorrow he might pick crack cocaine to lean on to support his weak underdeveloped brain. But no matter he was interviewed as a newsmaker to tell us on how to conduct our struggle against his former friends. It is not him I am worried about but my poor country and people that are jumping from one criminal to another to lead us on the road of failure.
Et tu ESAT, Et tu Bulcha is what is keeping me awake at night. May be I need new friends that would not play with my fragile ego and show a little bit of respect and empathy. As for Tamrat I await for his next interview and hopefully he would show up as a Drag Queen complete with makeup and that I promise would put my world right side up.

የጥራት እና ደረጃ መዳቢ ባለስልጣን መ/ቤት እና ህ.ወ.ሀ.ት

ነጻነት ይበልጣል (ከጀርመን)
ዛሬ ላስነብባችሁ ያሰብኩት  ቀደም ሲል የጥራት እና ደረጃዎች መዳቢ ባለስልጣን መስሪያ ቤት ተብሎ ይጠራ ስለነበረው  አሁን ለአራት ተከፋፍሎ እንዲጠፋ ስለተደረገ ተቋም ነው፡፡ መስሪያቤቱ ምርት እና አገልግሎችን  በመቆጣጠር የሸማቹን ደህንነት እና ጤንነነት ማስጠበቅ ፤ የገቢና ወጪ ምርቶችን  ጥራት በመከታተል ጉልህ ድርሻ እንዲያበረክት ታስቦ የተቋቋመ ነው፡፡መስሪያቤቱን ለረጅም ዓመታት በበላይነት ይመሩ የነበሩት አቶ መሳይ ግርማ ሲባሉ በውስጡ የፍተሻ እና ካሊብሬሽን አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የሰርተፊኬሽ አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የኢንስፔክሽን አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የደረጃዎች ዝግጅት ዳይሬክትሬት፣ የስልጠናአገልግሎት  ዳይሬክትሬት እና የፋይናንስ ዳይሬክትሬት እና ሌሎች የአገልግጎች ዘርፎች ነበሩት፡፡አቶ መሳይ መስሪያቤቱን ከ16 ዓመት በላይ አስተዳድረዋል፡፡ድንገት ባልተጠበቀ ሰዓት ከአቶ መሳይ እውቅና ውጭ 3 ሰዎች  አቶ ተክኤ ብርሀኔ ከመቀሌ፣አቶ ደቻሳ ጉሩሙ ከጅማ እና አቶ ዳንኤል ዘነበ ከሀረርጌ ተመልምለው  ወደ መስሪያቤቱ ተመደቡ፡፡ሰዎች ሳይፈለጉ መመደባቸው ብቻ ሳይሆን በወቅቱ እንዲከፈላቸው የተፃፈላቸው የደመወዝ መጠንም በመስሪያቤቱ የደመወዝ ስኬል የሌለ፤ ካላቸው የትምህርት እና የስራ ልምድ ጋር ምንም አይነት ዝምድና ስለሌለው አቶ መሳይ መክፈል አልችልም በማለት አንገራገሩ፡፡እነሱ መች የዋዛ ቢሆኑ እና እስከ ጠቅላይ ጽ/ቤት የተዘረጋ ሰንሰለት ስለነበራቸው በስልክ ተደውሎላቸው ሳይወዱ በግድ መክፈል ጀመሩ፡፡ እነዚህ ሰዎች በ2002 ዓ.ም ለሚካሄደው  ምርጫ ቅድመ ዝግጅት እንዲረዳ ከየክልሉ ተፈልገው የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ሀዋርያ ሁነው ወደ ፌዴራል መንግስት የመጡ ናቸው፡፡ተክኤ በስፓርት ፣ደቻሳ በሂሳብ እና ዳንኤል በማኔጅሜንት ተመርቀዋል፡፡ ሲመጡ የሚያርፉበት የኪራይቤቶች የሚያስተዳድረው ሰፋፊ ግቢ የተዘጋጀላቸው ሲሆን ዳንኤል ከአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጽ/ቤት አጠገብ፤ተክኤ እና ደቻሳ ደግሞ 22 አካባቢ ባለ ሰፋፊ ግቢ እንዲኖሩ ተመቻችቶላቸዋል፡፡ ዋናው  የቅርብ ጊዜ አላማቸውም በ2002 ለሚደረገው ምርጫ የመንግስት ሰራተኛውን ከኢህአዴግ ጎን ማሰለፍ እና ቀጣይ አመራሮችን ማዘጋጀት ነው፡፡ በዚህም መሰረት ባሉበት ቀበሌ በምርጫ ጣቢያ ሀላፊነት ተመድበው ይሰራሉ፡፡በተጨማሪም መንግስት በቢ.ፒ.አር.(business process reengineering) ብሎ ወደፊት ሊዘረጋ ላቀደው የሰራተኞች ማፈኛ መንገድ የራሱን  ታማኝ  የስለላ ሰዎች ወደ መሲሪያቤቱ ያስገባል፡፡ የአዲሶቹን ተመዳቢዎች አመጣጥ ተከተሎ በመስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የፍረሃት  ድባብ ተፈጠረ፡፡እነሱ ሰራተኞችን ወደሚጭነው ሰርቪስ ሲገቡ አንድም ሰው ትንፍሽ አይልም፡፡የአውቶቡሱ ሰው ሁሉ በጸጥታ ይዋጣል፡፡ጆሮ ጆሮ እያሉ ያንሾካሽካሉ፡፡በእረፍት ሰሀት እነሱ በተቀመጡበት አካባቢ አብሮ ተቀምጦ ሻይ ቡና የሚል የለም፡፡ሲመደቡ የኮሙኒኬሽን ሰራተኞች ተብለው ሲሆን ከመስሪያቤቱ እውቅና ውጭ ከነአቶበረከት ሰምኦን ጋር በየሳምንቱ ስብሰባ እና የመረጃ ልውውጥ ያደርጋሉ፡፡ከሳይንስና ቶክኖሎጂ ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲን ሳዶ ጋር ከፈለጉ በአካል መኪና አዝዘው ካልፈለጉ በስልክ በቀጥታ መገናኘት ይችላሉ፡፡አቶ መሳይ እና ሌሎች የመስሪያቤቱ ከፍተኛ አመራሮች የማያውቁት መረጃ ከነሱ ጋ ይገኛል፡፡በዚህ የአንድ አመት ቆያታቸው በመስሪቤቱ ደጋፊዎችን ማፍራት አልቻሉም፡፡
በ2003ዓ.ም የቢ.ፒ.አር ጥናት ሲጀመር አዲስ የመጡት ካድሬዎች  የጥናት ቡድን መሪ እየተባሉ ተመደቡ፡፡ ቢ.ፒ.አር ለመስራት ቀርቶ ስለመስሪቤቱ አሰራር በቂ እውቀት የሌላቸው ሰዎች መስሪያቤቱን አፍርሶ እንደ አዲስ የማደራጀት ስራ በእነዚህ ሰዎች ስር ወደቀ፡፡በዚህም ተቀራራቢ ስራዎችን በጋራ ማደራጀት በሚል ሰበብ ከብሄራዊ የጨረር መከላከያ አንዱን መምሪያ በማፍረስ፤የክሊነር ፐሮደክሽን መስሪያቤትን ሙሉ በሙሉ፤የሳይንስ መሳሪያዎች መስሪያቤትን ሙሉ በሙሉ አፈራርሰው አነዚህን መስሪያቤቶች ከደረጃ መዳቢ ባለስልጣን መስሪያቤት ጋር በማዋሀድ አራት የተለያዩ መስሪያቤቶችን ለመፍጠር ጥናቱ ተጀመረ፡፡ አዲስ የተጠኑት መስሪያቤቶች 1.Meterology institute, 2.Accreditation biro, 3 .Standards agency 4. Conformity assessment enterprise ይባላሉ፡፡ እነዚህ መስሪያቤቶች በተጠኑበት ወቅት ለጥናት ቡድኑ በየሳምንቱ በጣም ውድ በሆኑ ሆቴሎች የእራት ግብዣ  እየተዘጋጀ ለ6 ወር ያክል ተደከመበት፡፡ወደ መጨረሻው ምእራፍ ሲቃረብ  የጥናት ቡድኑ ሙሉ በሙሉ ናዝሬት ውስጥ ከ10 ቀን በላይ ሆቴል ውስጥ ተቀምጠው እንዲሰሩ ተደረገ፡፡በመጨረሻም የጥናቱን መጠናቀቅ አስመልክቶ  በአቶ ጁነዲን ሳዶ አማካነት አርባምንጭ ለሶስት ቀናት ድል ያለ ግብዣ ተደረገ፡፡ከአርባምንጭ መልስ ሁሉም በሳይንስ እና ቴክኔሎጂ ሚ/ር ስር የሚገኙ ሰራተኛ  ለገሀር በሚገኘው የመንገድ እና  ትራንስፖርት መሰብሰቢያ አዳራሽ ጠቅላላ ስብሰባ ተካሄደ፡፡በስብሰባው የየጥንት ቡድኑ ሀላፊዎች የጥናታቸውን ውጤት ይፋ አደረጉ፡፡የሀገራችን ችግሮች ተዳሰሱ፡፡ለችግሮች መፍትሄ ይሆናሉ የተባሉ አማራጮች ከየአቅጣጫው ጎረፉ፡፡አብዛኞች ወጣቶች ተስፋ ያደረጉትን በየመስሪያቤቱ ያለውን ብልሹ አሰራር እንዴት ማስወገድ እንደሚቻል አስተያየታቸውን ሰጡ፡፡በዚህ ውይይት ከተነሱት ውስጥ እስካሁን የማሰታውሳቸው አቶ ገብረጊዳን ገብረመስቀል በቅጽል ስሙ(GG) “በየመስሪያቤቱ ያለውን የተማረ የሰው ሀይል  እጥረት ለመቅረፍ መንግስት በውጪ የሚኖሩት ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ገብተው እንዲሰሩ ቢደረግ መልካም ነው፡፡ለምሳሌ እንደ ኢንጅነር ቅጣው እጅጉ አይነት ሰዎች ነበሩዋት ሌሎችም እንዲህ አይነቶች ይኖራሉ ብሎ ተናገረ፡፡”በእረፍት የንግድ ሚኒስትሩ የአቶ ታደሰ ሐይሌ ባለቤት ወ/ሮ አልማዝ ካህሳይ ይህን የተናገረውን ልጅ ጠራቸው እና ስሙን ጠይቃ “አንተማ የእኛው ነህ እየውልህ ኢ/ር ቅጣው በመንግስታችን ላይ ሊሰራ አቅዶት የነበረውን ስለማታውቅ ነው እንዲህ ያልከው፡፡በቶሎ ቀጨው እንጂ ቢቆይ በጣም አደገኛ ነበር፡፡እንዲህ አይነቱን ሰው ስሙን መጥራት የለብህም” አለችው፡፡ይቅርታ ወ/ሮ አልማዝ እኔ እሱን አላውቅም ነበር ሲል መለሰላት፡፡ሌላው ከጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት የመጣ  አቶ ጸጋዬ የሚባል አንድ ተናጋሪ በንግግራቸው መሀል ጣል ያደረጉዋት ቀልድ መሰል መልክት ሁሌም ትከነክነኛለች፡፡አቶ ጸጋዬ “አማርኛ እጅዋን አገኘች በግል ትምህርት ቤት ውስጥ አማርኛ መናገር እና ድንጋይ መወርወር ያስቀጣል ተብሎ በጉልህ ተጽፎ አንድ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ አንብቤያለሁ” ብለው አረፉ፡፡ሌላው ጠያቂ አብዲ ዱጋ ይባላል፡፡አብዲ ጥያቄውን ያቀረበው ለሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ነው፡፡ጥያቄው “ኦሮሚያ ክልል ውስጥ አየተካሄደ ያለው የአበባ እርሻ ልማት የአካባቢውን አፈር እና ውሃ እየበከለው ነው፡፡በዚህም የተነሳ እንስሳት ይሞታሉ ሰዎች ይታመማሉ፡፡የሰራተኞችም ህይወት አደጋ  ውስጥ ነው  የሚከፈላቸውም ገንዘብ እዚህ ግባ የሚባል አደለም፡፡እንዲያውም  ባለ ሀብቶች ከሌሎች ሀገሮች ሲባረሩ ነው ወደዚህ ሀገር የመጡት ይባላል እና ይህን እንዴት ያዩታል? ሲል ጠየቀ፡፡አብዲን የገጠመው ከፍተኛ ውግዘት ነው፡፡ለውግዘቱ መነሻም በወቅቱ የአበባ እርሻ ልማት ሲጀመር አቶ ጁነዲን የኦሮሚያ ርእሰመስተዳድር ስለነበሩ እሳቸውን እንደተቃወመ ተቆጠረ፡፡አብዲም ያጠናው ባዮሎጂ ስለነበር ሙያዊ ትንታኔ መስጠቱን ቀጠለ፡፡ክርክሩ እየከረረ ሲሄድ ጓደኞቹ ዝም እንዲል አደረጉት፡፡ስልጠናው ለ5 ቀናት በፍረሃት እንደተዋጠ ተጠናቀቀ፡፡ከዚህ ሰብሰባ መልስ በቀጥታ ሁሉም መስሪያቤት ወደ ሰው ኃይል ምደባ እንዲገባ መመሪያ ተላላፈ፡፡
ስብሰባው አርብ ተጠናቆ ሰኞ ጠዋት አቶ መሳይ ከመስሪያቤቱ በፍቃዳቸው እንዲለቁ  ትእዛዝ እንደተሰጣቸው  ለሚቀርቡዋቸው ሰዎች  ሲናገሩ የኮሚኒኬሽን ሰራተኞቹ እነ ተክኤ ደግሞ  ምደባውን እንዳያስተጉዋጉል በማሰብ አስቀድሞ መባረሩን በየቢሮው እየዞሩ ያውጃሉ፡ይህን ተከትሎ መስሪያቤቱ ሰው የሞተ ያክል በኡኡታ በልቅሶ ታመሰ፡፡አብዛኖች መልካም ተግባሩን ለሰራተኛ አዛኝነቱን እያሰቡ አባታቸውን በሞት የተነጠቁ ያክል ከልብ አዘኑ፡፡በዚሁ እለት የንግድ ሚኒስትሩ የአቶ ታደሰ ሀይሌ ባለቤት ወ/ሮ አልማዝ ካህሣዬ መስሪያቤቱን እንዲያስተዳድሩ ተሾሙ ፡፡የተለያዬ ዳይሬክተሮችን ሹመት ሰጡ፡፡በዚህ ወቅት ቀደም ሲል ወያኔን እንደሚቃወሙ የሚታወቁት እና ከአቶ መሳይ ጋር ቀረቤታ አላቸው የተባሉ ነባር ዳይሬክተሮች ተነስተው በምትካቸው የኢህአዲግ አባላትን መመደብ ተጀመረ፡፡ ምደባውም የሚካሄደው እያንዳንዱ ሰራተኛ እየተገመገመባለው ችሎታ ነው ይባል እንጅ ነገር ግን አስገራሚው እና ያን ያክል የተደከመበት ጥናት የግምገማውን 75% የሚይዘው  ከስራው ጋር ምንም ግንኙነት የሌለው አመለካካት የሚባል ነገር ነው፡፡ሰራተኞች በወቅቱ ያነሱት የነበረው ጥያቄ አመለካከት በምን ሊለካ ይችላል የእኔን አመለካካት ምን እንደሆነ ማን ያውቀዋል የሚል ነበር፡፡ ግምገማውን የሚሞሉት ቀደም ብየ የጠቀስኳቸው እነ ተክኤ፣ደቻሳ እና ዳናኤል ናቸው፡፡እነዚህ ሰዎች እንደመሰላቸው የግምገማ ነጥቡን መስጠታቸው ሳያንስ ምደባውን በዋናነት የሚመሩት እነሱ ናቸው፡፡ወደ ደረጃ መዳቢ መስሪያቤት የመጡትን የሌላ አዳዲስ  መስሪያቤት ሰራተኞች መልካቸውን ሳይቀር የማያውቁዋቸውን ሰዎች ግምገማ በድፍረት ይሞሉ ነበር፡፡በመሀል በተቃዋሚነት ያልተፈረጁትን እና አባል መሆን የሚፈልጉ ካሉ በምደባ እና በእድገት አያባበሉ ወደ ድርጅቱ የማግባባት ስራ ተከናወነ፡እኔ ስራየን እንጂ የፓርቲ አባል መሆን ፍላጎት የለኝም ያሉት ደግሞ ቀደም ሲል በተለያዩ የውጭ ሀገራት ሳይቀር ከፍተኛ ስልጠናዎችን ተከታትለው ስራቸውን በብቃት ሲወጡ የነበሩ በርካታ ባለሙያዎች አብዮታዊ ዲሞክራሲን ባለመቀበላቸው ብቻ  ዘራቸው እየታየ ከስራቸው ከተባረሩት መካከል ከዚህ  በታች የተዘረዘሩት ለማሳያ ያክል የቀረቡ ሲሆኑ አንድም የትግራይ ብሄር  ተወላጅ አለመባረሩን አንባቢያን ሊገነዘቡት ይገባል፡፡ሌላው እና አስገራሚው ነገር በወቅቱ  የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን እያገለለ እየተካሄደ ያለው ምደባ ያሳሰባቸው የኢህዴድ አባላት ጥያቄያቸውን ለሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ቢያቀርቡም ወ/ሮ አላማዝ ካህሳይ እያንዳንዱን ኦሮሞ እቢሮአቸው ጠርተው አርፈው እንዲቀመጡ አለዚያ እንደሚባረሩ በዛቻ ገልጸውላቸዋል፡፡በወቅቱም ከፍተኛ ተቃውሞ ያሰማው አቶ ሙሉጌታ መኮነን ያለስራ ለአንድ ዓመት ደመወዝ ብቻ እየተከፈለው ሊሰራ በማይችል ዘርፍ የቡድን መሪ ሁኖ ሲመደብ በስሩ ግን ምንም ሰው አልነበረም፡፡
ተ.ቁ           ስም    የነበራቸው ሀላፊነት
ብሄር
1አቶ መሳይ ግርማየጥራት እና ደረጃ መ/ቤት ዋና ዳይሬክተር
ኦሮሞ
2አቶ ጋሻው ወርቅነህየጥራት እና ደረጃ መ/ቤት ምክትል ዳይሬክተር
አማራ
3አቶ ተፈራ ማሞየኤሌክትሪክል ላብራቶር  ሃላፊ
ኦሮሞ
4አቶ ሀይሉየመሳሪያ ጥገኛ አገልግሎት ሃላፊ
ኦሮሞ
5አቶ ደሬሳ ፉፋየሰርተፊኬሽን አገልግሎት ዳይሬክተር
ኦሮሞ
6አቶ መስፍንየስልጠና አገልግሎት ዳይሬክተር
አማራ
7አቶ አዱኛው መስፍንየጥራት ማኔጅሜንት አሰልጣኝ
አማራ
8አቶ እንዳየኢንፎርሜሽን አገልግሎት ሀላፊ
አማራ
9አቶ አመሃ በቀለየጥራት ማኔጅሜነት አሰልጣኝ
አማራ
10አቶ ሂርጳየጥራት ማኔጅሜነት አሰልጣኝ
ኦሮሞ
11አቶ መረሳየሰርትፊኬሽን ኤክስፐርት
ኦሮሞ
12አቶ ቴወድሮስ ዘካሪያስየፍተሻ ላብራቶር ኤክስፐርት
አማራ
13አቶ  ልኡልየባህርዳር ቅርንጫፍ  ሀላፊ
አማራ
14 የሰርትፊኬሽን ሲስተም ኦዲተር የነበሩት
ኦሮሞ
15 የድሬደዋ ቅርንጫፍ ሀላፊ የነበሩትአማራ
16 የናዝሬት ቅርንጫፍ ሀላፊ የነበሩትኦሮሞ
17 የሀዋሳ  ቅርንጫፍ ሀላፊ የነበሩትደቡብ
ታማኝ የህወአት አባላት  በባትሪ  ከሌላ ቦታ ተፈልገው ያለ ልምድ  እና ችሌታቸው  በከፍተኛ አመራርነት ሲመደቡ የተለሳለሰ አቋም ያላቸውን እና የአባልነት ጥያቄ ሲቀርብላቸው ጥያቄውን የተቀበሉ ነባር የመስሪያቤቱ ሰራተኞች የፍርፍሪው  ተቋዳሽ ሁነዋል፡፡በዚህ ምደባ እስከቡድን መሪ ያለው ሀላፊነት ያለ ፓርቲ አባልነት ወይም ያለ ትግራይ ተወላጅነት በምንም መልኩ ለተራው ሰራተኛ አይሰጥም፡፡
ተ.ቁ ስም  ቀደም የነበራቸው ሀላፊነትአሁን የተሰጣቸው ሀላፊነትብሄር
1ወ/ሮ አልማዝ ካህሳየየኢንስፔክሽን አገልግሎት ዳይሬክተርየደረዳዎች ዋና ዳይሬክተርትግሬ
2አቶ ወንዶሰን ፍስሃየካሊብሬሽን አገልግሎት ሀላፊ የሜትሮሎጂ ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተርትግሬ
3አቶ አርአያመከላከያ ኢንጅነሪንግየአክረዲቴሽን ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተርትግሬ
4አቶ ጋሻው ተስፋዬየፍተሻ ላብራቶር ኤክስፐርትየተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርትግሬ
 አቶ ገብሬኝግድ እና ኢንዱስትሪ ኤክስፐርትበደረጃዎች ኢጀንሲ ዳይሬክተርትግሬ
6አቶ ብርሀኑ ተካ ረዳየፋይንነስ አስተዳደር ዳይሬክተርየተስማሚነት ምዘና ድርጅት የፋይናንስ ዳይሬክተርጉራጌ
7ወ/ሮ ገነት ገ/መድህንየፍተሻ እና ካሊብሬሽን  አገልግሎት ዳይሬክተርየአክረዲቴሽን ጽ/ቤት ዳይሬክተርትግሬ
8ወ/ሮ ብርሀን ብሂልየአዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጸሀፊየተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሰው ሀብት እስተዳደር ሀላፊትግሬ
9አቶ ብርሀኑ ተካየሰርቪስ ሹፌርየተስማሚነት ምዘና ድርጅት የተራንስፖርት መምሪያ ሀላፊትግሬ
10አቶ ተክኤ ብርሀኔየኮሙኒክሽን ሰራተኛየተስማሚነት ምዘና ድርጅት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተርትግሬ
11አቶ ዳዊት የሰርቪስ ሹፌርየሜትሮሎጂ ኢንስቲቲዩት የትራንትፖርትመምሪያ ሀላፊትግሬ
12አቶ ጸጋዬኢንስፔክተርየአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ሀላፊትግሬ
13አቶ ዘነበኢንስፔክተርየገበያ ጥናት ሀላፊትግሬ
ቀደም ሲል እንደማናኛውም ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳሉ የመንግስት መስሪያቤቶች የሚታዩ ችግሮች ቢኖሩም የተወሰደው እርምጃ ግን የወቅቱን የትግሬዎች የንግድ እንቅስቃሴ ያላንዳች ተቆጣጣሪ እንደፈለጉት ለማሽከርከር ታስቦ አንደሆነ ይታወቃል፡፡ለዚህም መነሻ የሚሆነው በተለያዩ ጊዜያት በቆርቆሮ፣ በብረታብረት፣ በማዳበሪያ፣ በሳሙና፣በከብሪት፣ በሲሚንቶ ፣ በዘይት፤ በጨርቃ ጨርቅ ፣ በባትሪ ድንጋይ፣በኤሌክትሪክ ገመዶች የመሳሰሉት ምርቶች ላይ ተደጋጋሚ ችግር ተከስቶ በበላይ አካል የስልክ ትእዛዝ ደረጃቸውን ያልጠበቁ ምርቶች ለህብረተሰቡ እንዲሰራጩ ተደርጉዋል፡፡ ለአብነት ያክል የአቢሲኒያ ሲሚንቶ ፋብሪካ በጥራት ጉድለት ምክንያት እንዳያመርት አገዳ መስሪያቤቱ ሲያስተላልፍ በወቅቱ የከተማ ሚኒስትር የነበሩት ዶ/ር ካሱ ኢላላ  ፍተሻውን ያከናወኑ ባለሙያዎችን በግላቸው ቢሮ ድረስ በማስጠራት ትክክል አደላችሁም፤ልማታችንን እያደናቀፋችሁ ነው፤ ኢንቬስተሮች ወደ ሀገራችን እየመጡ እንዳይሰሩ መሰናክል እየፈጠራችሁ ስለሆነ አቁሙ ሲባሉ የመስሪያቤቱ ሀላፊዎች እገዳውን ባስቸኩዋይ አንዲያነሱ ቀጭን ትእዛዝ አስተላለፈዋል፡፡ መስሪያቤቱም እንዲፈርስ የተደረገው ባለሞያዎችም የተፈናቀሉት ሆን ተብሎ ያለ አግባብ  መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲረዳው ያስፈልጋል፡፡

ሰላም ለአቶ አበራ የማነዓብ

ታደለ መኩሪያ
Ethiopian political prisoner Abera Yemaneab
አበራ የማነአብ
አቶ አበራ የማነዓብን ለመጀመሪያ ጊዜ ያየሁት በበጋው እ ኤ አ በ1990 ዓ ም ካናዳ ቶሮንቶ ከተማ ነበር። ስለ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ኃይሎች ቅንጅት (ኢዲኃ ቅ)  ዓለማውን አስመልክቶ ለቶሮንቶ ኗሪ ኢትዮጵያውያን ማሕበረሰብ  ማብራሪያ እንዲሰጥ ተጋብዞ  በመጣበት ወቅት ነበር። ከጉዞው ወደ ሰብሰባው አዳራሽ በቀጥታ የመጣ ይመስላል፤ ፀጉሩ አልተበጠረም፤ በትከሻው ላይ ያላወረደው ሸክም እንዳለ ያመለክታል፤ ከጉልጓሎ ወይም ከአጨዳ የመጣ ታታሪ ገበሬ አስመስሎታል፤  በግርድፉ እንደምንገምተው በከፍተኛ የትምህርት እውቀት ተገርቶ የወጣ አይመስልም፤ ወይም የከፍተኛ የቢሮክራሲው ማሕበረሰብ ክፍል አይመስልም። ከስብሰባው አካባቢ ከሀገር የወጣው በሱማሌያ በኩል ነው የሚል ጭምጭምታ ሰለሰማሁ እኔም በዚያ አቅጣጫ የወጣሁ ስለነበር ሰለዚያ አካባቢ ሁኔታ ራሴ በግል ያሳተምኳትን  መጽሐፌን አበረከትኩለት፤ ከዚያ በኋላግን አላየሁትም።
በኢትዮጵያውያን አቆጣጠር 1986 ዓ ም ለዲሞክራሲ አማራጭ ኃይሎች ሰብሰባ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ አዲስ አበባ ሄዶ ቦሌ አይሮፕላን ማረፊያ ተይዞ ወህኒ መውረዱን ሰማሁ። በ1997 ዓ ም ለጥቂት ቀናት ተለቆ ተመልሶ መታሰሩንም  በድሕረ ገጾች አነበብኩ። የተፈታበትን ቀን ዕርግጠኛ  ባለውቅም ሕዳር መጨረሻ 2006 ዓ ም በኢትዮጵያ ሳታላት ትቪ (ኢሳት) ሲሳይ አጌና ቃለ መጠይቅ ሲያደርግለት ሳይ በጣም ተደሰትኩ። ቶሮንቶ ባየሁት ወቅት እንደኔው ጊዜው የፈጠረው የፖለቲካ አቀንቃኝ መስሎኝ ነበር። ለሁለት ጊዜ በተከታተልኩት ቃለ መጠየቆች አቶ አበራ የማነዓብ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ አገፋው ሰው መሆኑን ተረዳሁኝ። በሕይወት መኖሩ የሚያስደስት ነው፤ ከርሱ ልምዶች ብዙ የምንማረው ነገር እንደለ እገምታለሁ። አቶ አበራ የማነዓብ ለመጠይቆቹ መልስ ሲሰጥ ከተጣደ የቡና ጀበና እንፋሎት የመሰለ ሐቅ ገንፍሎ ሲወጣ ፤ የኢሳቱ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና እባክህ ንገረን የሚል የጉጉት ስሜት በፊቱ ላይ ይነበብ ነበር።
ከአቶ አበራ የማነዓብ ለማወቅ የምፈልጋቸው በዙ ነገሮች አሉ። ይህን ሰል ሌሎቻችሁን  አይመለከትም  ማለቴ አይደለም። ሁላችንም በጋራ ያጣነውና በስደትም በሀገር ውስጥም እንዲመጣ የምንታገልለትን ‘ፍትህ’ የሚለውን ቃል በመልሱ ውስጥ ጠቅሶታል። ከሃያ ዓመት እስራት በኋላ ከ1956 ዓ ም የጀመረውን የፍትህ ፍለጋ ዛሬም በ2006 ዓ ም  አላገኘውም። በዚህ ሳምንት ያረፍት የፍትህ ታጋዩ ታላቁ ሰው ኔልሰን ማንዴላ ኢትዮጵያ ውስጥ ለረጅሙ ትግላቸው ዝግጅት ያደረጉበት ዘመን መሆኑ ነው፤ አበራ የማነዓብም የፍትህ ጥያቄውን የጀመረው። የሚገርመው የኝህን የታላቅ ሰው ሞት ከውጭ ሰምቼ ኢሳትን ከፍቼ ሰበር ዜናውን አዳምጬ  ወደአለፉት ቀናት ፕሮግራሞች አለፍኩኝ። ሲሳይ አጌና  አቶ አበራ የማነዓብን መጠየቅ ሲያደርግለት ከሚያሳየው ላይ አነጣጠርኩኝ።ይህንን ጽሑፍ እንዳቀርብ ያነሣሣኝ ያ ገጠመኝ ነው።
አቶ አበራ የማነዓብ በ1969 ዓ ም እርሱና የቀሩት የመላው ኢትዮጵያ ሶሻሊስት ንቅናቄ በአራት አቅጣጫ ወደ ሕዕቡ መግባታቸውን ገልጾልናል። ወደ ምስራቅ ኢትዮጵያ የሄዱትን በአካልም በዝና የማውቃቸው ነበሩ፤ እነርሱም፤ መገርሳ በሪ በባሌ ያደገ የ ክፍለሃገር ምክትል አስተዳዳሪ የነበረው፣ ዶክተር ባሩ ቱምሳ፣ አቦማ ምትኩ፣ዲማ ነገዎ፣ኡላና የሐረር አካዳሚ ምሩቅ፣ ገላሳ ዲቦና ሌንጮ ለታ የማስታውሳቸው ናቸው። በምዕራብ ኢትዮጵያ በሲዳሞ ክፍለሃገር በኩል መግባታቸውን በ1970 ዓም በሱማሊያ ሬዲዮ ጣቢያ በአማርኛው ፕሮግራም የእሸቱ አራርሶ መጠየቅ ከሰማሁ በኋላ ነበር።እሸቱ አራርሶ በ1969 ዓ ም በሲዳሞ ክፍለሃገር  የሕዝብ ድርጅት አላፊ ነበር። እንግዲህ በደቡብ፣ በደቡብ ምዕራብና ምስራቅ ያሉ ወጣቶች ወደሱማሌያ መሰደድ የጀመሩት  ከ1967 ዓ ም  ስልሳዎቹ ጅንራሎችና ሚኒስትሮች በደርግ  ከተረሸኑ በኋላ ነበር።
ወደ ዋናው ርዕሴ  ልመለስና አቶ አበራ የማነዓብ የሲዳማ አውራጃ አስተዳዳሪ ሳለ፤ መገርሳ በሪ  ደግሞ የባሌ ክፍለ ሃገር ምክትል አስተዳዳሪ ነበር። ኃይለማሪያ ሌንጮ ተቀዳሚ አስተዳዳሪ ነበር። በ1969 ዓ ም መሆኑ ነው ሻለቃ ተፈራ ወልደተሳይ ተቀይሮ ባሌ ሲመጣ፤  ከአቶ አበራ የማነዓብ  እንደሆነው ከመገርሳም ጋር አልተስማሙ ለቆ አዲስ አበባ ገባ። ይህ እንግዲህ 1969 ዓ ም መጀመሪያው ላይ መሆኑ ነው፤ መኢሶን ሕዕቡ የገባው ነሐሴ 1969 ላይ ነበር። ይህንን 1969 ዓ ም ደጋግሜ የምጠቅሰው ሻለቃ ኃይለማሪያም ሌንጮና ሻለቃ ተፈራ ወልደ ተንሳይ የሲዳሞና የባሌውን ክፍለሃገር ሕዝብ በተለይ ወጣቱን አስበርግገው ከሱማሌያ ጉያ  እንደከተቱት ለማሳየት ነው። ምንጊዜም የሃገራችንን ሕዝብ ከሃገሩ እንዲኩበልል የሚያደርጉት መሪ ነን ባዮቹ መሣሪያ የታጠቁት ክፍሎች መሆናቸውን መረዳት አለብን። ባሌ ከደሎ መና ዋቆ ጉቶም  ቀደም ብለው  ሀገር ለቀው ወደሱማሌያ ተሰደዋል፤ እርሳቸውን ይዘው እንግዲህ  የሱማሊያ መንግሥት የሱማሌ አቦ የሚለው ድርጅት አቋቋሞ እርስ በርስ ሊያጫርሰን የተሰማራው። አንዳንድ በቦታው ያልነበሩ በሕዝቡ ውስጥ ምን ይካሄድ እንደነበር የማያውቁ በሰሚ ሰሚ ዋቆ ጉቶን የኦሮሞ ነፃነት ግንባር መሪ አድርገው ያቀርቧቸዋል።ስለዋቆ ጉቶ ጊዜው ሲፈቅድ ከ1956 ዓ ም እስክ 1970 ዓ ም ያለውን እንዲት ማንኛው ኢትዮጵያዊ አሁን ድረስ የሚጠይቀውን ‘የፍትህ’ ጥያቄ በተለይ ለደሎ ሕዝብ ይጠይቁ እንደነበር በሌላ ጽሑፌ እመለስበታለሁ።  የባሌና የሲዳሞ  ክፍለሃገር ወጣቶች በሱማሊያ አቦ ሰም ታጥቀው በገጠር መሸጉ። በሲዳሞ በኩል ባላውቅም በባሌ በኩል ወደ መደብ ትግል አንለውጠዋለን ብለው የተቀላቀሏቸወን  የኢሕአፓ አባላት በሰላይ ስም  ፈርጀው ገለዋቸዋል።  በሐረርም እንደዚያው በታወቁት የክፍለሃገሩ ኗሪ ሼክ ኢብራሂም ቢሊሳ በሐርጌሳ በኩል በሱማሌ አቦና በኢሰላሚያ ኦሮሚያ  ስም ታጥቀው በምስራቁ ክፍል መሽገው ነበር።የመኢ ሶ ን መሪዎች በሲዳሞ ሕዕቡ ሲገቡ ኦሮሞኛ ተናገሪው ሕዝብ በሱማሌ  አቦ ቁጥጥር ሥር ነበር፤ ሱማሌ አቦ ነን የሚሉትም አብዛኞቹ ኦሮሞ ተናጋሪዎች ሲሆኑ መሪዎቹ ኦሮሞኛ ጉራኛና ሱማሌኛ  የሚናገሩ ግን ሱማሌያ ውስጥ ለብዙ ዓመታት የኖሩ ቆለኞቹ ነበሩ። በኦሮሞና በአማራ መካከል ልዩነት አያደርጉም። የደርግ መንግሥት አባሪ አድርገው ይመለከቷቸዋል። ስለዚህ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አልነበረም። በሐረር በኩል የገቡት የመኢሶን አባላት የኦሮሞ ተወላጆች ቢሆኑ  ኢስላሚያ ኦሮሚያና ሱማሌያ አቦ በአንደነት የሚቀሳቀሱበት ስለነበር በኦሮሞ ነፃነት ግንባር ስም መሣሪያ ይዘው አንዲት ጥይት  የተኮሰ አልነበረም፤ በመኢሶን፣ በኢሕአፓ እንደዚያው። ሰለዚህ አቶ አበራ የማነዓብ   በወቅቱ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በሐረር በባሌ በሲደሞ መኖር ያለመኖሩን በዙ ተጨባጭ ሐቆችን ሊያስጨብጠን ይችላል። ስለ እነ መገርሳ በሪ አማሟትም በሕይወት የሚኖሩት አንዲት ነገር ትንፍሽ ሲሉ አይሰማም። በመሬት ላይ የሌሉ ነገሮች እንደነበሩ ተደርገው እየተነገሩ ሕዝቡ ወደ ትልቁ ጠላቱ  ሀገር ከፋፋዩ ወያኔ  እንዳያተኩርና ለፍትህ የሚደረገውን ትግል እንዳይገፋ መሰናክል ሆኖበታል። የሱማሌያ አቦ ታጣቂዎች ወያኔ ሀገሪቱን ተቆጣጥሮ የሽግግር መንግሥት ሲመሰርት ራሰቸው ቀይረው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ነን ሲሉ የኦሮሞ መሑራን ከወያኔ ሽግግር መንግሥት የተካፈሉት  ደግሞ ጦራችን ነው ብለው እርፍ አሉት። ይህን  ሁኔታ በሌላው ጸሑፌ እመለስበታለሁ።
ለዛሬው እኔና  አቶ አበራ የማነዓብ የምንጋራቸው ጉዳዮች ላይ አተኩራለሁ።አቶ አበራ የማነዓብ የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች መማክርት ዋና ጸሐፊ በነበረበት 1956 ዓ ም የስደስተኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ።ስለዚህ ስለእርሱ ስገልጽ የእርሱ ወደርተኛ ሆኜ ለመቅረብ እንዳልሆነ አንባቢዎቼ እንዲረዱልኝ እሻለሁ።  እርሱ የሚከተለው የፖለቲካ ድርጅት አባል አይደለሁም። ይልቁንም ‘እርሱ ካልተፈታ አልፈታም’ ካለቺው፤ እርሱም ‘የእኔ እህት ካላት’ ክፍል ነኝ። የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) አባል የሆነችውን ገነትን ነበር ‘የእኔ እህት’ ያላት። በመኢሶንና በኢሕአፓ ስም ጎራ ለይተን ቂምና ጥላቻን በተግባርም በቃልም ስንገልጸው ለኖርነው ያ አቀራረብ የጥላቻን  ግባ ከመሬቱን ያከናወነ ይመስለኛል።
እኔም በኢሕአፓ አባልነት ከአዲስ አባባ ዩኒቨርሲቲ ተይዤ ከታሰርኩበት እስር ቤት   1971 ዓ ም የካቲት አምልጬ የተወለድኩበት ክፍለሃገር ባሌ ደሎ መና የዋቆ ጉቱ ሀገር ገባሁ። የሱማሌያ አቦ ታጣቂዎች ከተቆጣጠሩት አካባቢ ከርሜ በ1972 ዓ ም  ዶሎ የሱማሌ ክፍል ዳዋ ወንዝ ላይ ሰፈርን፤ ከአምስት መቶ በላይ ወጣቶች ነበሩ። በምዕራብ በኩል ከሲዳማ ክፍለሃገር የመጡ አቶ አበራ የማነዓብ የጠቀሳቸው አቶ ወልደማኑኤልና ልጆቻቸው እሸቱ አራርሱ እኔ የማውቃቸው  አቶ ይልማ ና አቶ ቁምጣ የሚባል ከክብረመንግሥት አካባቢ ኦሮመኛ ተናጋሪ ነበሩ፤ በመሐል የምንገኘው ደግሞ ከባሌ የመጣናው ስንሆን መሪያችን የዋቆ ጉቶ ምክትል የሆነው አልይ ዑመር ነበር። ዛሬ በስደት ለነደን ይገኛል። በምስራቅ በኩል ከኦጋዴን የመጡ የሠፈሩበት ነበር። አቶ አበራ የማነዓብ ወደቆሮሌ የተወሰደው ከቤተሰብ ጋር ስለነበር ይመስለኛል። አቶ አበራ የማነዓብ ብዙ ግንዛቤ ይኖረዋል ብዬ የማስበው በሲዳማ ነፃ አውጪ ስም ሆነ በ ሱማሌ አቦና በሱማሌ ገልቤድ ወይም ምዕራብ ሱማሌያ ብለው ይቀሳቀሱ የነበሩት ተዋጊዎች ደርግ በፈጠረው የጅምላ  ግድያ ምክንያት የውጪ ጠላቶች የፈጠሯቸው እንጂ  ሀገርን ለማስገንጠል ወይም ለመገንጠል የሚቀሳቀሱ አልነበሩም። ወጣቱም ወደእነዚህ ንቅናቄዎች ሲቀላቀል የወጪዎችን ደባ ለማክሸፍ ነበር። ጥላሁን ግዛው 1961 ዓ ም የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲት ተማሪዎች መማክርት ፕሬዘዳንት ወቅት እሸቱ አራርሶ ዋና ጸሐፊ ነበር። ዶክተር እሸቱ ጮሌ በ1956 ዓ ም የቀደማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቪርሲቲ ፕሬዘዳንት  ሲሆን  አበራ የማነዓብ  ዋና ጸሐፊ ነበር። ስለዚህ  ሕዝቡ ውስጥ የገቡት ሀገራቸውን ለማስገንጠል ነው ብሎ የሚያስብ የለም። በሲዳሞ መስመር እነ ሻለቃ ሰርኔሣ ‘እኔ ኮሩ ኢትዮጵያዊ ኦሮሞ እንጂ ሱማሌ አቦ አይደለሁም በማለቱ በሱማሊያ እስር ቤት ተገሏል፤ እሸቱ አራርሱ  የኢሕአፓ አባል መሆኔን እያወቀ  ከሱማሌው ሴንተራሌ እስር ቤት ለማስፈታት   መጣሩ ከሥር ከተፈታሁ በኋላ ሰምቻለሁ። ሱማሌያ ለቅቄ ከወጣሁ በኋላ በሱማሌያ እስር ቤት አንደ ሻለቃ ሰርኔሣ መገደሉን ተነግሮኛል። ስለዚህ በምስራቅ በኩል ወደሕዝቡ የገቡት የመኢሶን ሆኑ የኢሕአፓ አባላት ሀገር ለመገነጠል ወይም ለማስገንጠል ያለመሆኑን   ከኔ በላይ አቶ አበራ የማነዓብ ሊያውቅ ስለሚችል ከቃለ መጠይቅ ያለፈ በመጽሐፍ መልክ ሊያስተላልፈው የሚችለው ብዙ የማናውቀው ሐቅ ይኖረዋል ብዬ አምናለሁ። በዚህ አጋጣሚ ቤተሰቡ ከርሱ ጋር በሀገርም በባዕድ ሀገርም የደረሰባቸውን እንግልት በቆራጥነት መውጣታቸውን ሣላደንቅ አላልፍም።

ለርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አባላትና ወዳጆች፤ እንዲሁም በመላው UKየምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ሁሉ

ቀን፡ 23/12/2013
በስደት ላይ በሚገኘው ኢትዮጵያዊ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ ጥረት፤ ድካምና ተጋድሎ አማካኝነት ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በዘረጋው የጎሳ ፖለቲካ ተጽዕኖ ሥር ሳትወድቅ በአስተዳደር ራሷን ችላ በመመራት ለከፍተኛ የዕድገት ደረጃ የበቃችው አንጋፋዋ የለንደን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ወቅት ለወያኔ ባደሩ ጥቂት ባንዳ ካህናትና ተከታዮቻቸው አማካኝነት ገንዘብና ጉልበታቸውን አስተባብረው፤ ጥረውና ግረው የሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ባለቤት ካደረጓት አባላቷ ተነጥቃ የወያኔ አገዛዝ ሹመኞችና ደጋፊዎች ንብረት እንድትሆን የሚካሄደው ጥረት ቀጥሎ ይገኛል።Reese Adbarat Saint Mary of Debre Tsion Ethiopian Orthodox Church
ቀደም ሲል እነዚሁ ከሃዲ ካህናትና ተከታዮቻቸው ወያኔ ከጎሳው መርጦ ከሾማቸው ከአቡነ እንጦስና ከነ መጋቢ ተወልደ ጋር ግንባር በመፍጠር በ12 October 2013 ሁለት ጳጳሳትን ከኢትዮጵያ በማስመጣት ቤተ ክርስቲያኗን በወያኔ አገዛዝ ሹመኞችና ደጋፊዎች ቁጥጥር ሥር ለማዋል ሙከራ ያደረጉ ሲሆን ይህ ሙከራቸው ግን ስደተኛው ኢትዮጵያዊ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝቤ ላይ የምትፈጽሙት ግፍ፤ በደልና ፍትሕ አልባነት አልበቃ ብሏችሁ በዚህ ነጻነትና ፍትሕ በሰፈነበት ሃገር ደግሞ ተመሳሳይ ድርጊት እፈጽማለሁ ብላችሁ አታስቡ በማለት ሰላማዊና ሕጋዊ ተቃውሞ በማድረግ ሙከራቸውን ሊያከሽፈው ችሏል።
ከዛም በመቀጠል የከሃዲዎቹ መሪ የሆኑት አባ ግርማ ከበደ አዲስ አበባ ድረስ በመሔድ ከወያኔ አገዛዝ ባለሥልጣኖችና የደህንነት ሰዎች ጋር በመምከር ለንደን በሚገኘው የወያኔ ኤምባሲና ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሃ.ት) ጽሕፈት ቤት እየተረዱ የጀመሩትን ተግባር እንዲያጠናቀቁ መመሪያ ተቀብለው ተመለሱ።
አባ ግርማ ከበደም ለወያኔ አገዛዝ ያላቸውን ታማኝነት ለማረጋገጥ ሲሉ ዜና ቤተ ክርስቲያን ለተሰኘው መጽሄት ለንደን ላይ የሚያስቸግሩኝ ግንቦት ሰባትና ቅንጅት ናቸው የሚል ክስ በማቅረብ ከነዚህ ሁለት ድርጅቶች ጋር ለሚያደርጉት ትግል ወያኔ ከጎናቸው እንዲቆምላቸው መጠየቃቸውን መጽሄቱ በእትሙ ላይ ካሰፈረው ለመረዳት ተችሏል።
በዚህ ድጋፍና መበረታታት በመታገዝ በአሁኑ ወቅት ደግሞ እነዚህ ባንዳ ካህናትና ተከታዮቻቸው የሃገሪቱን ሕግም ሆነ የቻሪቲን ሕግና መመሪያ አንቀበልም በማለት በኤምባሲ ተወካዮችና ለንደን ከደረሱ ካለፈው 7 ጀምሮ ማርያም ቤተ ክርስቲያንን ደጃፏን ረግጠው በማያውቁት አቡነ እንጦስ አማካኝነት በ29/12/2013 ቤተ ክርስቲያኗን ከፍተው ለማስረከብ መዘጋጀታቸውን ይፋ ማስታወቂያ በማሰራጨት ላይ ይገኛሉ።
ከዚሁ ጋርም በኤምባሲና በወያኔ ጽ/ቤት አስተባባሪነት በለንደን ያሉና ከለንደን ውጪ ያሉ የሌላ ቤተ ክርስቲያን አባላት ተጓጉዘው መጥተው ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በብዛት በመገኘት ቤተ ክርስቲያኗን በወያኔ አገዛዝ ሹመኞችና በኤምባሲ ተወካዮች ቁጥጥር ሥር ለማዋል ኃይልና ጉልበት እንዲሆኗቸው ለማድረግ እየሰሩ መሆኑን አቡነ እንጦስ በሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለጸሎት ለተሰበሰበው ሕዝብ ይፋ ቅስቀሳ አድርገዋል።
ይህንን በሚያደርጉበት ጊዜ ግን ለአካባቢው ፖሊስ የተሰጠው ምክንያት የጸሎትና የአምልኮት መብታችንን ይከበርልን ዘንድ ቤተ ክርስቲያኑን ስንከፍት አስፈላጊው ትብብር ይደረግልን የሚል በመሆኑ ፖሊስ ያሉትን አምኖ ተቀብሎ ትብብር ሊያደርግላቸው እንደሚችል ይገመታል።
በለንደንና በመላው UK የምትገኙ ውድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮችና የማርያም ወዳጆች ሁሉ፡
መብትና ነጻነት ያለትግል፤ ድካምና መስዋዕትነት አይገኝምና ዛሬ የእምነትና የነጻነት ምልክታችን የሆነችውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስደተኛው ኢትዮጵያዊ ሃብትና ጉልበቱን አስተባብሮ የንብረት ባለቤት ባደረጋት ማግስት የወያኔ ሹመኞች የውስጥ ባንዳዎችን በመሣሪያነት ተጠቅመው የሃይማኖቱን ማዕከል፤ ሃብትና ንብረቱን ነጠቁት ማለት ነገ በስደቱ ዓለም ነጻ የኮሚኒቲ ማዕከል፤ የፖለቲካ ተቋም፤ መኖር ቀርቶ በቤተሰብ ደረጃም ሆነ በግል ሰብ ሳይቀር በነጻነት ሃገር መብትና ነጻነትን አሳልፎ ለመስጠት ትለቁ በር ከፋች ስለሆነ ሁሉም የማርያም ወዳጅና ነጻነት ወዳድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ በ29/12/2013 ከ0800 ሰዓት ጀምሮ በርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በመገኘት ቤተ ክርስቲያኑን እንዲከላከልና በስደት ሃገር የተጎናጸፈውን መብትና ነጻነቱን እንዲያስከብር በእመቤታችን በቅድስት ማርያም ስም ጥሪአችንን እናቀርባለን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
http://londondebretsion.org/ ተከታተሉን
ourchurchdebretsion@gmail.com ኢ-ሚየል መረጃ ማግኘት ይችላሉ።

ኢኮኖሚያችን ሲያድግ የህዝቡ ኑሮ ለምን አሽቆለቆለ?

ማስተዋል ደሳለው
ላለፉት 8 እና ዘጠኝ ዓመታት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሁለት አሃዝ አያደገ ነው ሲባል እንሰማለን፤  የእድገት ፍጥነቱ  ላይ የሚነሱ በርካታ ጥያቄውች  ቢኖሩም መንግስት  የመንገድ ግንባታ ፣ የኃይል ማመንጫ ግንባታወችን እና መሰል ነገሮችን  በመጥቀስ እድገት እንዳለ አስረግጦ ይከራከራል::  በሌላ በኩል የኢኮኖሚ እድገቱ ተመዘገበ በሚባልባቸው ዓመታት በዋጋ ንረት የህዝቡ ኑሮ ከጊዜ ወደጊዜ እያሽቆለቆለ  እንደሆነ በግልፅ የሚታይ ነገር ነው:: ታዲያ  የኢኮኖሚ እድገት አለ በተባለባቸው ዓመታት የህዝቡ ኑሮ ለምን አሽቆለቆለ? ይህን ጥያቄ ከ 7 ዓመት በፊት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ  ተጠይቀው የሰጡት መልስ የዋጋ ንረቱን የኢኮኖሚ እድገቱ እራሱ የፈጠረው ጉዳይ ነው ነገር ግን ቀስ በቀስ እድገቱ ሲቀጥል ራሱ እድገቱ ችግሩን ይፈታዋል ብለው ነበር፤ ነገር ግን ከሰባት ዓመት በዃላም እንኩአን ሊሻሻል  የህዝቡ የኑሮ ሁኔታ ከቀን ወደቀን እየባሰበት ሂዷል::  ችግሩ የተለያዩ  ምንጮች ቢኖሩትም በዋናነት በ 2 ከፍሎ ማየት ይቻላል::
፩. የኢኮኖሚ እድገቱ ምንጭ
፪. የሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር
የኢኮኖሚ እድገት ማለት በአጭሩ ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ተጨማሪ ሀብት መፍጠር ማለት ነው::  በመጀምሪያ ላለፉት 8  እና ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ ዉስጥ  የተፈጠሩት ተጨማሪ ሀብቶች ምንድን ናቸው ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል ፤  በአብዛኛዉ ሀገሪቱ ዉስጥ የተፈጠሩት ሀብቶች ከመንገድ ፣ ከሕንፃ እና ከ ከኃይል ማመንጫ ከግንባታ ጋር የተያያዙ ናቸው:: በመቀጠልም የዚህ ሀብት የገንዝብ ምንጭ ምንድን ነው ብሎ ማየት ያስፈልጋል፤ የገንዘቡ ምንጭ በዋናነት ከብድር እና እርዳታ የተገኘ ሀብት ነው ፣ በተለይም በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ 1998 ዓም ጀምሮ በሶማሊያ በመጀመሪያ የእስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረት በመቀጠልም የአልሻባብ እንቅስቃሴ መጠናከር ለኢትዮጵያ ትልቅ ሲሳይ ይዞ ነው የመጣው:: በሶማሊያ ያለዉን ሁኔታ  ለመቆጣጠር ምዕራባዉያኑ የሚያደርጉትን ጥረት በመደገፍ  በዋና አጋርነት የተሰለፈችዉ ኢትዮጵያ ላለፉት ስምንት ዓመታት በየዓመቱ በቢልየን ዶላር የሚቆጠር ገንዘብ በእርዳታ መልክ ከምዕራብ ሃገራት እንድታገኝ አድርጓታል:: ይህም ማለት ሀገሪቱ ዉስጥ የጎላ  የኢኮኖሚያዊ መዋቅር ፣ የአሰራር ስርዓት  እና የቴክኖሎጅ ለውጥ ሳይኖር ከፍተኛ ገንዘብ ወደኢኮኖሚው ፈሰስ እንዲሆን አድርጓል:: በሌላ አገላለፅ  የቆየው የሀገሪቱ  ኢኮኖሚ የጎላ የምርት ጭማሪ ሳይኖረው ከዉጭ የተገኘ ብድር እና እርዳታ ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ተጨመረ እና የኢኮኖሚዉ መጠን አደገ ማለት ነው::  ስለዚህ የህዝቡን የኑሮ ሁኔታ እና የሀገሪቱን ተወዳዳሪነት ሊያሻሽል የሚችል የግብርና እና የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ የጎላ  ለዉጥ ሳይታይ ለመሠረት ልማት ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ፈሰስ የተደረገው ገንዝብ የገንዘብ አቅርቦትን (Money Supply) በመጨመር እና  የአገልግሎት ዘርፉ ( Service sector) ከሌሎቹ የኢኮኖሚ ዘርፎች ተነጥሎ እንዲለጠጥ እንዲሁም ዋጋ እንዲንር በማድረግ አብዛኛዉን ሕዝብ ለችግር አጋለጠ ::
ከብድር እና እርዳታ የተገኘው ገንዘብ መሰረተ ልማት ላይ ሲዉል ከላይ የተገለፀው ችግር ቢኖርበትም በአንፃሩ የመሰረተ ልማት መስፋፋት የማምረቻ ወጭ ( cost of production) እንዲቀንስ በማድረግ የሚያስገኘው ጥቅም አለ ፤ በተጨማሪም ገንዘብ ገንዘብን ይፈጥራል “ money creats money” በሚለው የኢኮኖምክስ  መርህ መሰረት ኢኮኖሚዉ ዉስጥ የተረጨው ገንዘብ በአብዛኛዉ አገልግሎት ዘርፉ ላይ የፈጠረው ተጨማሪ ሀብት አለ:: ነገር ግን ይህ የተፈጠረ ተጨማሪ ሀብት በጠንካራ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር ስላልተመራ ወደጥቂት ሰወች እጅ እንዲገባ ሁኗል::  ሃብቱ እጃቸው የገባ ሰወችም የኢኮኖሚዉን መዋቅር ሊለዉጡ የሚችሉ እንደኢንዱስትሪ አይነት ዘርፎች ላይ ከመሰማራት ይልቅ ከሙሰኛ ባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለዉን የከተማ ቦታ በኢንቨስትመንት እና በሊዝ ስም በመዉሰድ ህንፃ በመገንባት እየተለጠጠ ላለው የአገልግሎት ዘርፍ በማከራየት በአቁአራጭ ከፍተኛ ገቢ ለመሰብሰብ ተጠቀሙበት::
በሌላ በኩል የሀገሪቱ የመሬት አስተዳደር ስርዓት በሙስና የተጨማለቀ እና ወጥ ስላሆነና አዳዲስ ብቅ ለሚሉ ባለሀብቶች መሬት ማግኘት ከባድ ስለሆነ ሀገሪቱ አሁን ባለችበት ተጨባጭ ሁኔታ ወሳኝ ሀብት (strategic resource) የሆነዉን የከተማ ቦታ ቀድመው የያዙ ባለሀብቶች የገቢያ ዉድድሩን ሚዛናዊ እንዳይሆን በማድረግ አዲስ የሚፈጠሩ ተወዳዳሪያቸውን በቀላሉ ከገቢያ ያስወጣሉ:: በተጨማሪም እንደነዚህ አይነቶቹ  ባለሀብቶች በአብዛኛው የፖለቲካዉ እና የግዥዉ ፓርቲ ጥገኛ ስለሆኑ የሚጠበቅባቸዉን ያክል  ግብር እና ታክስ አይከፍሉም:: ሥራቸዉን ስለሚያውቁም በሀገሪቱ በረጅም ጊዜ ሊከሰት ይችላል ብለው የሚፈሩትን ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ስለሚሰጉ የሚያገኙትን ትርፍ ወደዉጭ ያሽሻሉ ፤ በጎን ሙሰኛ ባለስልጣናትም የሚዘርፉትን ገንዘብ ከሀገር ያሸሻሉ:: ከዚህ ላይ ፋይናንሽያል ትራንስፓረንሲ ኳሊሽን  ያወጣዉንና ኢትዮጵያ በህገወጥ የገንዘብ ፍሰት (illicit financial flow) በፈረንጆቹ ከ 2000 እስከ 2009 ያጣችዉን 11. 7 ቢልየን ዶላር ልብ ይሏል::
ለማጠቃለል የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ጤናማ ሁኖ እንዲያድግ ከተፈለገ ከላይ የተጠቀሱት  የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ መዋቅር ድክመቶች መስተካከል የሚገባቸዉ ሲሆን ፤ በዉጭ ብድር እና እርዳታ ላይ መንጠልጠሉን ቀንሶ ከሀገር ቤት በፍትሃዊነት ከሚሰበሰብ ግብር ሊሆን ይገባል:: ከዉጭ የሚገኘዉን ሀብትም  በብዛት መሰረተ ልማት ላይ ብቻ ማዋሉ የሚያስከትለዉን ችግር ጥልቅ ጥናት በማካሄድ  መመርመር እና  ገንዘቡ ከመሰረተ ልማቱ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪው እና የእርሻዉን ዘርፍ መዋቅር ወደተሻለ ደረጃ እንዲደርስ ለማስቻልም መሰራት አለበት:: ከሁሉም በላይ ግን የኢኮኖሚ ነቀርሳ የሆነዉን ሙስና ለማስወገድ ከአንድ ፓርቲ የበላይነት ወደ መድብለ ፓርቲ ስርዓት መሸጋገር እንዲሁም ተጠያቂነትን ሊያጠናክሩ የሚችሉ እንደገለልተኛ ፍርድ ቤቶች ፣ የግል መገናኛ ብዙሃን  የመሳሰሉትን ተቋማት መፍጠር ያስፈልጋል:: ይህ ካልሆነ ግን ሀገሪቱ ሽህ ጊዜ ብታድግ የኢኮኖሚውን ፍሬ ጥቂቶች እየበሉ የአብዛኛዉ ሕዝብ  ኑሮ ማሽቆልቆሉ ይቀጥላል::