Thursday, October 17, 2013

ለሕዝባዊ ተቃውሞ የወያኔ ፈቃድ የማይጠየቅበት ቀን እንዲመጣ እንታገላለን!!!

  


መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም. አንድነት ለዲሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ከሌሎች በርካታ ፓርቲዎች ጋር በመተባበር የጠራው ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል። ይህ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ከዝግጅቱ እስከ ፍፃሚው ብቻ ሳይሆን ከፍፃሚው በኋላም በድርጊቶች የታጀበ ነበር።
ወያኔ ለሰልፉ እውቅና ሰጥቶ እያለ “መቀስቀስ አይቻልም፤ ፓስተር መለጠፍ አይቻልም፤ በዚህ ማለፍ፣ በዚያ መዞር አይቻልም” እያለ የፓርቲው መሪዎችን፣ አባላትንና ደጋፊዎችን ሲያስር፣ ሲፈታ፣ ሲያዋክብ ሰንብቷል። ይህም ሆኖ ግን የፓርቲ መሪዎች፣ አባላትና ደጋፊዎች ወከባውን ተቋቁመው ሰላማዊ ሰልፉን መጀመር ቻሉ።
ወያኔ ሰልፈኛው ወደ መስቀል አደባባይ እንዳይደርስ የለመደውን ጉልበት ተጠቀመ። ከተለያዩ አቅጣጫዎች ይተሙ የነበሩ ሰላማዊ ሰልፈኞች እንዳይገናኙ በፓሊሶች ታገቱ። ኢትዮጵያ ውስጥ አፈና የደረሰበት ደረጃ ጎልቶ ታየ። ሰልፈኛው ሊደርስ ያሰበው ቦታ – መስቀል አደባባይ – መድረስ ሳይችል ቀረ። የሰልፉ አስተባባሪዎች የነበሩበት ብዛቱ በመቶ ሺህ የተገመተ ስብስብ ሊደርስ በቻለበት ቦታ የመዝጊያ ሥነሥርዓት ፈጽሞ ተበተነ።
የወያኔ ጆሮ ጠቢዎች ከሰልፊ በፊት፣ በሰልፉ ጊዜ እና ከሰልፉ በኋላ ግንባር ቀደም የሰልፉ ተዋንያንን የማደን፣ የማዋከብ፣ የማሠር፣ የመደብደብ “ሥራ” በዝቶባቸው ሰንብቷል። ባሠሩና ባዋከቡ መጠን ግን የሕዝብ ምሬት እየበረታ መጥቷል።
ወያኔ ሰልፉን ለመቆጣጠር እጅግ ብዙ የሆነ የፓሊስ፣ የጦርና የሰላይ ሠራዊት ለማሠማራት ተገዷል። ይህ ራሱ አንድ ድል ነው።
ከዚህ ሰልፍ የተገኘው ጥቅም ግን ይህ ብቻ አይለም። ወያኔ በሕዝብ ልብ ውስጥ ዘራሁት ያለው ፍርሀት በኖ የሚጠፋ መሆኑ፤ እድል በተፈጠረ ጊዜ ሁሉ ወጣቶች በፈጠራ ሥራዎቻቸው ተመልካችን ማስደመም የሚችሉ መሆኑን፤ የተለያዩ ሀይማኖቶች ተከታዮችን ለማጋጨት ወያኔ የሸረበው ድር የተበጣጠሰበት መሆኑ ሰልፉ አሳይቷል።
በሌላ በኩል ደግሞ ወያኔ በወታደር እና በሰላዮች ብርታት ላይ የቆመ ሥርዓት መሆኑን አሳይቷል። ወያኔ በጠመንጃና በስለላ ላይ ያለው ሞኖፓሊ ካልተሰበረ ሕዝባዊ ተቃውሞዎችንም እሱ ከሚፈልጋቸው ክበብ እንዳይመጡ ማፈን የሚችል መሆኑ አሳይቷል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህንን የወያኔ ወታደራዊና የስለላ ሞኖፖሊ መስበር የሥራው አንድ አካል አድርጎ ይመለከታል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በሕጋዊና ሰላማዊ መንገድ አምባገነኑን ወያኔ በመገዳደር ላይ ያሉትን ወገኖች ትግል ያደንቃል። እንዳንዳንዳችን የየበኩላችን ጥረት ካደረግን የኢትዮጵያን የመከራ ጊዜ በእጅጉ እንደምናሳጥር ያምናል።
ግንቦት 7 ሕዝብ ተቃውሞ ለማቅረብ የወያኔን ባለሥልጣኖች ፈቃድ መጠየቅ የሚያበቃበት ጊዜ እንዲመጣ ተግቶ ይሠራል። ለዚህ ዓላማም ተባብረን እንድንቆምም ጥሪ ያደርጋል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

አያ ጅቦ ሳታመካኝ ብላኝ !!!

  


ኃይለማሪያም ደሳለኝ በአንድ ወቅት ዉሸትን የማያዉቅ ጠንካራ ክርሰቲያን ነዉ ተብሎ ሲነገርለት ሰምተን ነበር፤ ታድያ ይህ ሰዉ መለስን ሲተካ ብዙዎች በጥርስ የለሽ አንበሳነቱ ቢስማሙም ዉሸት እንደ ንጉስ በነገሰባት ኢትዮጵያ ዉስጥ ዉሸት የማያዉቅ መሪ መጣ መባሉ ብዙዎቻችንን ነጻነት የተገኘ ያክል አስደስቶን ነበር። ሆኖም ከወያኔ ጋር የዋለ ሰዉ እራሱን ሆኖ መክረም አይችልምና ኃይለማሪያምም ባስቀመጡት ቦታ የማይገኝ የሌላ መንደር ሰዉ ሆኖ ተገኘ። በዚህም የዜጎችን ተሰፋ አመከነ፤ ደስታቸውንም ወደ ኃዘንና ትካዜ ለወጠው።
ባለፈዉ ሳምንት መጨረሻ ላይ በመገናኛ ብዙኋን ፊት ያየዉን አላየሁም፤ የሰማዉን አልሰማሁም፤ ያልሆነዉን ሆነ የሆነዉን ደግሞ አልሆነም እያለ ሽምጥጥ አደርጎ የካደዉ ኃይለማሪያም ደሳለኝ፤ በእርግጥም ጎበዝ የመለስ ዜናዊ ተማሪ መሆኑን በተግባር አስመስክሯል። ኃይለማሪያም ባለፈዉ ዓርብ አንድ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር። ይህ ግለሰብ በዚህ ጋዜጣዊ መግለጫዉ ኢትዮጵያን ያክል ትልቅ አገር ከሚመራ ሰዉ ቀርቶ ከአንድ ተራ የቢሮ ተላላኪ እንኳን የማይጠበቅ መልስ ሲመልስ ተስተዉሏል።
ኃይለማሪያም በጋዜጣዊ መግለጫዉ ወቅት ከቀረቡለት ብዙ ዲሪቶ ጥያቄዎች ውስጥ አንዱ አገር ቤት ውስጥ እየተደረገ ያለው ሠላማዊ ሰልፍ ጉዳይ ነበር። ኃይለማሪያም አገር ቤት የሚደረጉ የተቃውሞ ሰልፎች “በራሳቸው የሚደረጉ ሳይሆኑ ከኋላ ባሉ ሌሎች ኃይሎች መሪነት የሚደረጉ” ናቸው ሲል ተናግሯል። ኃይለማሪያም ጌቶቹ ፊቱን በጨርቅ አስረዉት የኢትዮጵያ ህዝብ ችግር፤ መከራና ስደት አልታይ ብሎት ነዉ አንጂ ወያኔን የመሰለ ነብሰ ገዳይ ባለበት አገር ዉስጥ የህዝብን ብሶት የሚያስጋቡ ጥያቄዎች በየቀኑ ይመነጫሉ አንጂ ከዉጭ አገርማ አይመጡም። በሌላ በኩል ደግሞ ይሄዉ ኢትዮጵያ በቅርቡ ያፈራቸዉ ዋሾ ሰዉ የእስልምና እምነት ተከታዮች የሚያደርጉት ሠላማዊ እንቅስቃሴ የአሸባሪዎች እጅ ያለበትና፤አማኞቹ ሃይማኖታቸውን የወደዱ መስሏቸው ሳያውቁ የገቡበት ስለሆነ እንዲታረሙ እንመክራቸዋለንም” ብሏል። እዚህ ላይ በግልጽ እንደምናየዉ ኃይለማሪያም ደሳለኝ እመራዋለሁ የሚለዉን ህዝብ ጥቅምና ፍላጎት ፈጽሞ ሊረዳ አልቸለም፤ ስለዚህ ምክር የሚያስፈልገዉ መብትና ነጻነት ምን እንደሆኑ ገብቶት የሚታገለዉ የአትዮጵያ ህዝብ ሳይሆን ኃይለማሪያም እራሱ ነዉ።
እኛ ግንቦት ሰባቶች ወያኔን የመሰለ ጨካኝ እና ምንም አይነት አገራዊ ኃላፊነት የማይሰማውን ዘራፊና ዘረኛ ቡድን በሠላማዊ መንገድ የሚጋፈጡ ወገኖቻችንን እናደንቃለን። እነዚህ ወገኖቻችን ኃይለማሪያም ደሳለኝ እንደሚለው የማንንም አጀንዳ የተሸከሙ ሳይሆኑ የራሳቸው የሆነ አጀንዳ ያላቸውና ኃይለማሪያም በዉክልና ለሚያስረግጣቸዉ ወገኖቻችዉ መብትና ነጻነት የሚታገሉ ጅግኖች ናቸዉ። አጀንዳቸውም የተደበቀ ወይም ከጀርባውም ሌላ ነገር ያለው አጀንዳ አይደለም።አጀንዳቸው ግልጽ እና የታወቀ የነፃነት፤ የእኩልነት፤የፍትህና የሠላም አጀንዳ ነው። ኃይለማሪያም ደሳለኝ የዜጎችን ጥያቄ አድምጦ መልስ መስጠት ሲገባው እነዚህን የኢትዮጵያን ህዝብ አጀንዳ ተሸክመው የሚታገሉ ወገኖች ደካሞች አድርጎ ለመሳል የሚያደርገዉ ሙከራ አንድም በተቃዋሚዎቹ ዙሪያ የተሰባሰበውን የሰው ኃይል ካለማወቅ፤ አለዚያም ደግሞ “ሊበሏት ያሰቧትን አሞራ ይሏታል ጅግራ” እንደሚባለው ነገር ነው።
ሌላው ኃይለማሪያም የሚናገረዉ ቃል ጠፍቶት በተደጋጋሚ ሲንተባተብ የታየዉ በሽብርተኝነት አካባቢ የተጠየቀዉን ጥያቄ ሲመለስ ነዉ። በእኛ እይታ ኢትዮጵያ ዉስጥ ዋነኛው አገር በቀል አሸባሪ ህወሃት እና ህውሃት ብቻ ነው። ህወሃት ስልጣን ላይ ያቆየኛል ብሎ ከገመተ የማይመሰርተው የክስ ዓይነት፤ የማያፈሰው የንጹህ ሰው ደም ፤የማያፈነዳው የቦንብ እና የፈንጂ ዓይነት እንደሌለ ከሃውዜን እስከ አዲስ አበባ ያሉ መንገዶች ቋሚ ምስክሮች ናቸው። ይህንን እኩይ ተግባሩን ዓለም ሁሉ እንደሚያውቀው በዊክ-ሊክ ላይ የወጣው መረጃም አሳይቷል።
የህውሃት ታማኝ ሎሌ የሆነዉ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ሠላማዊ ትግሉን ለማፈን ከፈለገ በትግሉ ዙሪያ የተሰባሰቡትን ዜጎች ከሌላ ከማንም ጋር ማነካካት አያስፈልገውም። ኢትዮጵያ ውስጥ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ ሁሉ አንደ ኃይለማሪያም ሞቶ የተቀበረን ሰዉ ራዕይ የተሸከሙ የአመለካከት ደሃዎች ሳይሆኑ የራሳቸው አስተሳሰብና ህያዉ ራዕይ ያላቸው ዜጎች ናቸው። አነዚህን ሠላማዊ ታጋዮች ከማይገናኝ ሌላ ኃይል ጋር አቆራኝቶ ለመምታት መሞከር ለኃይለማሪያምም ሆነ ለጌቶቹ አይበጃቸዉም። ዛሬ በወያኔ ነብሰ ገዳይ ወታደሮች ተከብቦ እዩኝ እዩኝ የሚለዉ ኃይለማሪያም ደሳለኝም የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጣ የነደደ ቀን ደብቁኝ ማለት ይመጣልና ያ ቀን ከመምጣቱ በፊት የበደለዉን ህዝብ ይቅርታ ጠይቆ የነጻነት ኃይሎችን እንዲቀላቀል ወገናዊ ምክራችንን እንለግሳለን።
በመጨረሻም ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ስለ ግንቦት ሰባት ተጠይቆ ሲመልስ ግንቦት ሰባት “በህልም ውስጥ ያለ ድርጅት” ነው ብሏል። ታድያ ምነዉ ተኝቶ ህልም የሚያልም ድርጅት ኃ/ማሪያምንና ጌቶቹን እንዲህ ያቃዣቸዋል? ለምንስ ይሆን ወያኔና ታማኝ ሎሌዉ ኃ/ማሪያም ያገኙትን ሁሉ ግንቦት ሰባት እያሉ የሚያስሩት፤ የሚደበድቡትና የሚገድሉት? ያገኛችሁትን ሁሉ የግንቦት ሰባት አባል እያላችሁ ትከሳላችሁ? ለምንስ በግንቦት ሰባት ስም ታስራላችሁ? ትገርፋላችሁ? ትገድላላችሁ? ተኝቶ ለሚያንቀላፋ ድርጅት ለምን ትሸበራላችሁ፤ ለምንስ እንቅልፍ አጥታችሁ ትባዝናላችሁ? ግንቦት ሰባት እናንተ አልገባችሁም አንጂ መነሻውንና መድረሻውን አጥርቶ የሚያውቅ፤ ከደመናው ባሻገር ፍንትው ያለ የነፃነት ዉጋገን የሚታየው ባለ ታላቅ ራዕይ ድርጅት ነው። አስኪ ምናልባት ቢገባችሁ ተረት ቢጤ እንንገራችሁ፤
“አንዲት ሚዳቋ ነበርች አሉ። ሚዳቆ ከመሬት ገንዘብ ተበድራ ሲትኖር ከእለታት አንድ ቀን መሬት አፍ አውጥታ ብድሬን መልሽ አንጂ ብላ ትጠይቃታለች። ሚዳቆዋም ደንግጣ ከነበረችበት ቦታ ፈትለክ ብላ ወደ ተራራ ጫፍ ላይ ወጥታ እፎይ ያንን ድምጽ ከአሁን በኋላ አልሰማም አለች። መሬትም በይ ብሬን ክፈይኝ ስትል ዳግም ጠየቀቻት። እንዴ ይህች መሬት የሌለችበት ዬት አገር ሊሂድ ብላ ሚዳቆ ወደ ማይታወቅ ቦታ ተፈተለከች። ከዚያም እያለከለከች በቃ አሁንስ አታገኚኝም ስትል አሁንም መሬት ብቅ ብላ እየጠበኩሽ ነውኮ ብድሬን ክፈይ እንጂ ስትል ጠንከር አድርጋ ጠየቀቻት። ሚዳቆዋም መሬት የሌለችበት ልትደረስ ስትበር ስትበር ሳንባዋ ፈንድቶ ሞተች”ይባላል።
የፍትህ፤ የእኩልነት፤ የነፃነትና የዲሞክራሲ ጥያቄዎች እንደ መሬት ናቸው። የትም ሂዱ፤ የትም ግቡ ይከተሏችኋል። መስጊድ ዉስጥ አሉ፤ ቤተክርስትያናት ውስጥ አሉ። ቤተመንግሰት ዉስጥም አሉ። የሌሉበት ቦታ የለም። መፍትሄው እንደ ሚዳቆዋ መሸሽ አይደለም። መፍትሄው ዜጎች የሚያነሷቸውን የፍትህ፤ የእኩልነ፤ የነፃነትና የዲሞክራሲ ጥያቄዎችን አድምጦ ትክክለኛ መልስ መስጠትና ከዕዳ ነጻ መሆን ብቻ ነዉ ። ከዚህ ዉጭ ጥያቄን ላለመስማት ወይም ሰምቶ ለመደፍጠጥ የሚደረገው ከንቱ ሩጫ መጨረሻው እንደ ሚዳቆዋ መፈንዳት እንጂ ህይወት አይሆንላችሁም።
እኛ ግንቦት ሰባቶች ዘረኛዉንና አሸባሪውንና የወያኔ ስርዐት ለመደምሰስና ህዝብ በነፃነት ያለፍርሃት የሚኖርበትን አገር ለመፍጠር ቆርጠን ተነስተናል። ከእንግዲህ የሚያቆመን ምንም ነገር የለም። የምንታገለዉ ለህዝብ ጥያቄያችንም ህዝባዊ ጥያቄ ነዉና እኛም አንደጥያቄዉ በየመስጊዱ፤ በየቤተክርሲቲያኑና በየሰፈሩ ዉስጥ አለን።እኛ የሌለንበት ስፍራ የለም። በዚህ አጋጣሚ የዘመናት ትግላችን ፍሬዉ የሚታይበት ቀን እጅግ በጣም ቅርብ ነዉና የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም አገር ተረካቢ የሆነዉ ወጣቱ ትዉልድ እራሱን፤ ወገኖቹንና እናት አገሩን ለማዳን የሚደረገዉን የነጻነት ትግል እየመጣ እንዲቀላቀል ወገናዊ ጥሪያችንን አቅርበናል። ኑ እና ተቀላቀሉን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Ethiopia and Egypt face off over billion-dollar Nile dam project

By Nicholas Bariyo, The National
Ethiopia, Egypt and Sudan will hold discussions next week over the effect of a new billion-dollar hydro plant along the river Nile, which Egypt fears will hurt water supply to its 84 million people.

The meeting will be the first since experts submitted their recommendations on the $4.3bn (Dh15.79bn) Grand Ethiopian Renaissance Dam project more than three months ago.
“The meeting is scheduled to take place ... on Oct. 22, 2013 between officials of the three countries,” the Ethiopian foreign ministry said.
Egypt fears the 6,000 megawatt plant is likely to hurt its water supply when it comes on-stream around 2017. The majority of the Egyptian population is centred near the Nile valley and the desert nation depends on the river for around 95 per cent of its water.
In June, former Egyptian President Mohamned Morsi said that Egypt would “defend each drop of the Nile with our blood”. Egypt is fiercely opposed to the dam but years of political turmoil have weakened the nation’s influence in the region.
The experts’ report is yet to be made public but according to Fekahmed Negash, the director of boundary and trans-boundary rivers at Ethiopia’s Water, Irrigation and Energy ministry, the experts recommend further studies to analyse the effect of the dam on Egypt’s water supply. Ethiopia plans to take up to six years to fill the dam’s 74 billion cubic-metre reservoir but insists this will not adversely affect the river’s downstream flow.
Addis Ababa, which is fully funding the project, has pledged to sell excess power to Egypt. Early this year, Ethiopia ratified the Nile River Cooperative Framework deal, challenging the colonial-era treaty that guarantees Egypt “natural and historic rights” over the Nile waters. Lower basin nations including Ethiopia, Kenya, South Sudan and Uganda are all opposed to the treaty. In June, Uganda’s President Yoweri Museveni said that Egypt should not continue to “hurt countries” in the Nile River basin by restricting power projects along the river. Uganda is developing several hydro power projects along the Nile.

‘Freedom on the Net’ report says Ethiopia among the least free

According to the ‘Freedom on the Net 2013′ report, Ethiopia has been labeled as “least free” and ranked 79 from 100; 1 being the most free and 100 the least free. The report states that Ethiopia has one of the lowest internet and mobile telephone penetrations in the world as inadequate infrastructure, government monopoly over the telecom sector, and obstructive telecom policies have notably hindered the growth of information and communication technologies (ICTs).
The report further reads “Despite low access, the government maintains a strict system of control over digital media, making Ethiopia the only country in Sub Sahara Africa to implement nationwide internet filtering.”Ethiopia’s telecommunication infrastructure is among the least developed in Africa and is almost entirely absent in rural areas. As of the end of 2012, internet penetration stood at just 1.5 percent, up slightly from 1.1 percent in 2011. On the other hand, the number of fixed broadband subscriptions increased dramatically from 4,600 subscriptions in 2011 to nearly 38,000 in 2012, although the number still represents a penetration rate of only 0.4 percent.Mobile phone penetration in 2012 was roughly 24 percent, with a little over 20.5 million subscriptions, up from 17 percent in 2011.Regarding access, the report suggests that the combined cost of purchasing a computer, initiating an internet connection and usage fees makes internet access beyond the reach of many Ethiopians. It also suggests that Ethiopia’s internet connections are among the most expensive in the world when compared with monthly incomes of citizens.Most people rely on internet cafes to use the internet, but the connection at these places is indeed very slow. According to a 2010 study conducted by Manchester University’s School of Education, it was found that accessing an online e-mail account and opening one message took six minutes in a typical internet cafÉ.Internet access via mobile phones is also beset by slow connection speeds. “According to a 2012 report by the Internet Society, telecom policy issues and poor connectivity are largely to blame for the country’s “low internet speeds”, the report continued. The government has sought to increase access for government offices and schools in rural areas through different projects, although the report claims that the projects have been used to broadcast political messages from the central government in Addis Ababa to teachers, students and district administrators in remote parts of the country.According to the report, the Ethiopian government is reluctant to ease its grip on the telecommunication sector. The report also claims that, in addition to the state monopoly of the sector, increased corruption within its ranks has been highlighted as a major reason for poor telecom services in the country. According to a 2012 World Bank report, the telecommunication sector in Ethiopia has the highest risk of corruption compared to other sectors assessed, such as land, education and construction.
Source: HispanicBusiness’ Tech Channel