Sunday, January 12, 2014

የምንናገርበትን የመገናኛ ብዙሃን ማንም እንዲመርጥልን ወይም እንዲወስንልን አንፈቅድም!


ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
ጥር 1 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የብሔራዊ ደህንነት መረጃ እና የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል የጋራ ኃይል አድርጎ ራሱን የሚጠራ አካል የዜጎችንና የተቋማትን ሕገ-መንግስታዊና ዲሞክራሲያዊ መብት በመጣስ ጥፋተኝነታቸው በፍርድ ቤት ሳይወሰን ወንጀለኛ ሲያደርጋቸውና ስማቸውን ሲያጎድፍ ማየት እየተለመደ የመጣ ተደጋጋሚ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ይህ ከላይ ከተጠቀሱት ሁለት ተቋማት ተውጣጥቶም ይሁን ተቀናጅቶ የሚሰራ አካል በተደጋጋሚ ጊዜ በሽብር ወንጀል ጠርጥሬአቸዋለሁ የሚላቸውን ሁሉ በመክሰስ ወደ እስር ቤት እንዲወርዱ እያደረገ ጉዳያቸው የፍርድ ቤት ውሳኔ ሳያገኝ እንደፈለገ በሚቆጣጠረው ወይም በሚያዘው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት አማካኝነት የፈለገውን ዓይነት ፍረጃና ሥም ማጥፋት ሲያካሒድባቸው ቆይቷል፡፡
ይህ ራሱን ከሕግ በላይ የሰቀለ አካል ያለምንም ገደብ ከሚሰራቸው ተግባራት እንዲታቀብ በሕግ የሚያስቆመው በመጥፋቱ እስካሁን የፈፀማቸውን የማንአለብኝነት ተግባራት እንደጥፋት ሳይሆን እንደ መልካም ሥራ ቆጥሯቸው በተመሳሳይ የሥም ማጥፋትና የፍረጃ ተግባሩ እንዲገፋበት አድርጎታል፡፡ በዚሁም መሰረት ታህሳስ 25 ቀን 2006 ዓ.ም ምሽት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ባስተላለፈው የዘጋቢ ፊልም ፕሮፓጋንዳ አሸባሪ ያላቸውን ድርጅቶችና ግለሰቦች አድርሰውታል ያለውን ጥፋት በዝርዝር አቅርቧል፡፡ ፓርቲያችንን በዚሁ ዘገባ ከተጠቀሱት “አሸባሪ” ድርጅቶች ጋር በማገናኘት ስም ለማጉደፍና ለማስፈራራት የተደረገውን መፍጨርጨር አይተናል፣ ሰምተናል፣ ተገርመናል በመጨረሻም አዝነናል፡፡
በዘጋቢ ፊልሙ የቀረቡ ፓርቲያችንን የማይመለከቱ ጉዳዮችን ትተን ከፓርቲያችን ጋር በማገናኘት የተጠቀሰው “ኢሳት” የተባለ የመገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ መንግስት በሽብርተኝነት ከተፈረጀ ድርጅት የገንዘብ ድጋፍ እንደተደረገለትና በሰላማዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች በተለይም ሰማያዊ ፓርቲ በዚህ የመገናኛ ብዙሃን እንዳንጠቀም የማስጠንቀቂያ ዛቻ ተላልፎልናል፡፡ ይህ አስፈራሪ አካል ራሱን ሕግ አውጭና ሕግ ተርጓሚ በማድረግ የፈለገውን አካል ለመፈረጅ፣ ለመክሰስና ለመፍረድ ሥልጣኑን ከየት እንዳገኘ የማይታወቅ ሲሆን የዚህች ሐገር ዜጎችም ሃሳባችንን የምንገልፅበትንና የማንገልፅበትን የመገናኛ ብዙሃን እየመረጠልንና እየወሰነልን ይገኛል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እንዲህ ዓይነቱን የእብሪት መልዕክት ከተራ ርካሽ ፕሮፓጋንዳነት የማያልፍ የሕግና የዲሞክራሲያዊ መብት ገደብን ካለማወቅ የሚመነጭ አስተሳሰብ ነው ብሎ ያምናል፡፡
የገዥው ቡድን ሰዎች ሀሳብን በሃሳብ ማሸነፍ እንደማይችሉ ስለሚያውቁት የቀራቸው አማራጭ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ሃሳባቸውን የሚያሰራጩባቸውን መንገዶች መዝጋት ብቻ መሆኑን ፓርቲያችን ይገነዘባል፡፡ ነገር ግን ማንም አካል በሕግም ሆነ በሞራል ተጠያቂ የሚሆነው የሚያስተላልፈው መልዕክት ይዘት የሌሎችን ዲሞክራሲያዊና ሞራላዊ መብት የሚጋፋ መሆን አለመሆኑ እንጂ ገዥው ቡድን በጠላው ወይም በወደደው የመገናኛ ብዙሃን መልዕክቱን ማስተላለፍ አይደለም፡፡ መልዕክትን የገዥው ቡድን ሰዎች በጠሉት የመገናኛ ብዙሃን ማስተላለፍ በራሱ ወንጀለኛ ወይም ሽብርተኛ ለማድረግ የሚያበቃ ምንም ዓይነት የሕግ መሰረት የለም፡፡ ማንም መልዕክት የሚያስተላልፍ አካል የሚያሰራጨው ሃሳብ የሌሎችን ዲሞክራሲያዊና ሞራላዊ መብት የሚጋፋ ከሆነ መልዕክቱ የተላለፈበት መገናኛ ብዙሃን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም ይሁን ሌላ ህጋዊ የተባለ የመገናኛ ብዙሃን መሆኑ ብቻ መልዕክት አስተላላፊውን አካል ከተጠያቂነት ሊያድን እንደማይችልም ለማንም የተሰወረ ይሆናል የሚል እምነት የለንም፡፡
በመሆኑም ሰማያዊ ፓርቲ መልዕክቱን የሚያስተላልፍበትን መገናኛ ብዙሃን ማንም አካል እንዲመርጥለት ወይም እንዲወስንለት የማይፈልግ መሆኑን ግልፅ እያደረገ በሕገ መንግስቱ የተረጋገጠውን ማንም ሰው በመረጠው መንገድ ሃሳቡን የማስተላለፍ መብቱን በመጠቀም በኢሳትም ሆነ እድሉን ካገኘ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አቋሙንና እምነቱን ማስተላለፍ የሚቀጥል መሆኑን ማረጋገጥ ይወዳል፡፡ በዚሁ አጋጣሚም የፓርቲያችንን መልካም ስም በሃሰት ለማጉደፍ የተሰነዘሩ ቃላትን በቀላሉ የማንመለከታቸው መሆኑን ሕግ ባለበት ሐገር ራስን ከሕግ በላይ በማስቀመጥ ማንንም አካል መፈረጅና ስም ማጉደፍ በሕግ የሚያስጠይቅ መሆኑን የዘጋቢ ፊልሙ ባለቤቶች እንዲያውቁትና ወደፊትም ተመሳሳይ ድርጊት ከመፈፀም እንዲቆጠቡ እናሳስባለን፡፡

ሻምበል ጉታ ዲንቃ፤ ጊዜውን ጠብቆ ይነጋል (ፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም)


ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
በአሁኑ ጊዜ ወያኔ ሰውን እያፈረሰ፣ ማህበረሰብን እያፈረሰ ሰማይ-ጠቀስ ሕንጻዎችን በሚሠራበት ጊዜ፣ ከትናንት ወዲያ የሰዎችን ቤቶች አፍርሶ ትናንት የመኪና መንገድ ከሠራ በኋላ ዛሬ መንገዱን አፍርሶ የባቡር መንገድ እየተሠራ አዲስ አበባ በትራፊክ መጨናነቅ መኪና መንዳት አደገኛ በሆነበት ጊዜ፣ ዛሬ ባለሥልጣኖች የሚሠሩት ጠፍቶአቸው የጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ የሚባለውን በአማካሪዎች ከሞሉት በኋላ ለሚኒስትሮችም አማካሪ መሾም በተጀመረበት ጊዜ፣ ዛሬ በሳኡዲ አረብያ ኢትዮጵያውያን እንደአደገኛ አውሬ እየታደኑ በሚደበደቡበት፣ በሚታሰሩበት፣ በሚደፈሩበትና በሚገደሉበት ጊዜ፣ ዛሬ በኬንያና በዩጋንዳ እንዲሁም በእሥራኤል ኢትዮጵያውያንን የማንገላታት ዝንባሌዎች በሚታዩበት ጊዜ፣ ዛሬ ኢትዮጵያውያን ከስዊድን እስከአውስትራልያ እየተሰበሰቡ በመጮህ ለማይሰሟቸው ሁሉ አቤቱታቸውን በሚያቀርቡበት ጊዜ፣ ዛሬ በተለያዩ አገሮች በኢትዮጵያውያን ላይ በሚፈጸመው ጥቃትና በደል፣ አለሁላችሁ የሚል መንግሥት በሌለበት ጊዜ —- ዛሬ ታሪካዊትዋ ኢትዮጵያ፣ ራሳቸውን የሚያከብሩና ኩራት ራታችን የሚሉት ኢትዮጵያውያን አልቀው ለሆድ በየሰው አገር መሰደድ ባህል በሆነበት ጊዜ፣ ዛሬ ዶር. በድሉ ዋቅጅራ ስለኢትዮጵያና ስለኢትዮጵያውያን ውርደት ደጋግሞ የነፍሱን ኡኡታ ባሰማበት ጊዜ በድንገት አንገታችንን ቀና አድርጎ ኩራታችንን ሊያስጎነጨን የሞከረ ሰው ተገኘ! ኢትዮጵያ ሁሌም የተአምር አገር ነች።Capitain Guta Dinka an Ethiopian soldier, responsible for Madiba's safety during his stay
በታላቁ ሰው በኔልሰን ማንዴላ እረፍት ምክንያት አንድ ተደብቆ የኖረ ክቡር ኢትዮጵያዊ ብቅ አለ፤ ማንዴላ ለሥልጠና በኢትዮጵያ በነበረበት ጊዜ ምናልባትም እንግሊዞች ማንዴላን ሊያስገድሉ ከጠባቂዎቹ አንዱ የነበረውን ወታደር በገንዘብ ገዝተው ዓላማቸውን ለመፈጸም አቅደው ነበር፤ ወታደሩ ገንዘቡን ከተቀበለ በኋላ ሀሳቡን ለውጦ ገንዘቡን ለአለቃው ሰጠ፤ ማንዴላ ከሞት ተረፈ፤ አንድ ተራ ኢትዮጵያዊ ራሱንና አገሩን የሚያስከብር ሥራ ሲሠራ የሚኮሰኩሳቸው ባለሥልጣኖች ለእነሱ የማይተላለፍ ክብር በመሆኑ ተዳፍኖ እንዲኖር አደረጉት፤ እነሱ ሞተው ወይም ተሰድደው ሲያልቁ የተዳፈነው ምሥጢር ብቅ አለ፤ ባለሥልጣኖቹ ሸልመውት ይሆናል፤ ግን አላከበሩትም፤ ሻምበል ጉታን ያከበረው የማንዴላ ሞት ነው፤ የሚያሳዝነው ማንዴላ ይህንን የሱን ሕይወት ለማትረፍ ሁለት ሺህ ፓውንድ ያጣውን ኢትዮጵያዊ ወታደር ሳያውቀው መሞቱ ነው።
የኢትዮጵያ አርበኞች ታሪካቸው ተቀብሮ የቀረው እንዲህ እየሆነ ነው፤ ታዴዎስ ታንቱ ሥራዬ ብሎ የተረሱ አርበኞችን ከመቃብር እያወጣ ያስተዋውቀናል፤ በሌሎች አገሮች እንደዚህ ለአገር ትልቅ ፋይዳ ያለው ሥራ በአንድ ሰው በበጎ ፈቃድ የሚሠራ ሳይሆን ዋና የመንግሥት ተግባር ነው።
ሻምበል ጉታ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ባይሆንም ራሱን ችሎ ለኔልሰን ማንዴላ መቃብር ደርሶአል፤ በአገር ደረጃ በሥልጣን ወንበሮቹ ላይ ለአገር የሚያስቡ ሰዎች አለመኖራቸውን ለማወቅ ግሩም ማስረጃ ነው፤ ለቀብር የሄደው ባለሥልጣን ሻምበል ጉታን ይዞ ቢሄድ ኖሮ ለራሱም ሆነ ለአገሩ ክብርና ጌጥ ይሆንለት ነበር፤ ለደቡብ አፍሪካ ሕዝብም ሆነ ለዓለም በመላ አንድ ኢትዮጵያዊ ወታደር አልሸጥም-አልለወጥም ብሎ የኔልሰን ማንዴላን ሕይወት ማትረፉን በማስታወቅ አገሪቱን ያስከብር ነበር፤ የታፈነው ታሪክ አፈትልኮ ሲወጣ ከስደተኞች ጋር ተያይዞ መሆኑ ኢትዮጵያ የደረሰችበትን የአደባባይ መክሸፍ የሚያሳይ ነው፤ ባለቤት ያቀለለውን አሞሌ ባለዕዳ ተቀበለው፤ መንግሥት ያፈነውን ክብር ስደተኞች አጌጡበት!
ለእኔ አሁን አንድ ጥያቄ ይቀራል፤ ሻምበል ጉታ የአገሩን ክብር ከራሱ ጥቅም በላይ በማድረጉ፣ የተቀበለውን አደራ በመጠበቁ ቢያንስ ሁለት ሺህ ፓውንድ አጥቷል፤ እንዳጣ ሊቀር ነው? ቢያንስ የከፈለውን ሁለት ሺህ ፓውንድ ወይስ ያንን አሥር እጥፍ አድርገን እንከፍለዋለን? ሻምበል ጉታን የምናመሰግነው በርጥቡ ነው በደረቁ? እኛ ያለጥርጥር ኮርተንበታል፤ ሁላችንም በኢትዮጵያዊነታችን የሱን ክብር በመጋራት ራሳችንን አክብረናል፤ ሻምበል ጉታም በእኛ እንዲኮራና በእኛ እንዲከበር ማድረግ ያለብን ይመስለኛል፤ ስለዚህ ምን እናድርግ? ለራሱ ክብር፣ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን ክብር ሲል የከፈለውን እስቲ ከወሬ ያለፈ ነገር እናስብና ለዚህ ጀግና የምንችለውን አድርገንለት እግዚአብሔር ዕድሜ ይስጥህ እንበለው።

የቀደምቶቹን ወንጀል ለማጋለጥ መቃብር ሲምስ የኖረው ወያኔ በራሱ ጦር ካምፕ ውስጥ የተገኘውን አስከሬን መደበቅ ለምን አሰፈለገው?


Ginbot 7 weekly editorialአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ፈረንሳይ ለጋሲዮን በሚገኘው የክብርዘበኛ ጦር ካምፕ ውስጥ ማንነታቸው ያልታወቁ የ6 ዜጎች አስከሬን ለመንገድ ሥራ በተሠማሩ ቆፋሪዎች አማካኝነት መገኘቱ የሰሞኑ አሳዛኝ ዜና ነው።
አንድ አይነት ቀለም ባላቸው ብርድ ልብሶች ተጠቅልለው ከተገኙ 6 አስከሬኖች የመጀመሪያዎቹ ሁለት ሰለባዎች ታስረውበት የነበረው የእጅ ሰንሰለታቸው እንኳ እንዳልወለቀና ከተቀሩት የአንዱ እጆች ደግሞ የፍጥኝ ወደ ኋላ እንደታሰሩ መገኘታችው ግድያው በቅርብ እንደተፈፀም አንዱ አስረጂ ነው።
በእንዲህ አይነት ጭካኔ የተገደሉ ዜጎች አስከሬን መገኘት በመንግሥት ተብየው አካል ካለመገለጹም በላይ ግቢውን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው 3ኛ ክፈለ ጦርም ሆነ በግብር ከፋይ ገንዘብ የሚተዳደሩ መገናኛ ብዙሃን እስከዛሬ አንድም ቃል መተንፈስ አለመፈለጋቸው ጉዳዩን እጅግ የሚያሳዝን ብቻ ሳይሆን የሚያስገርምም አድርጎታል። ይባስ ተብሎም በመንገድ ሥራ ቁፋሮው የበለጠ አስከሬን ሊወጣ ይችላል በሚል ስጋት አካባቢው በፖሊስ እንዲታጠር ከተደረገ በኋላ ሥራውም እንዲቋረጥ ተደርጓል።
በፓለቲካ መስመር ልዩነት ምክንያት ደርግ ያለ ርህራሄ የጨፈጨፋቸውን ከመቃብር እያወጣ ዘመድ አዝማድ በማላቀስ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ሲዳክር የኖረ አገዛዝ በእንዲህ አይነት አሳዛኝ ሁኔታና አጋጣሚ የተገኘውን የጅምላ አስከሬን አይቶ አንዳላየ ለማለፍ መሞከሩ ለምን ይሆን?Mass grave found in Military camp in Addis Ababa
አብዛኛው የአዲስ አበባ ነዋሪ እንደሚያስታውሰው የክብር ዘበኛ ጦር ካምፕ በመባል የሚታወቀው የጃን ሜዳ 3ኛ ክፍለ ጦር ግቢ ድህረ ምርጫ 97 ወያኔ ለጅምላ እስር ቤትነት ከተጠቀመባቸው የማጎሪያ ቦታዎች አንዱ ነበር። ከዚያን ጊዜ በፊትና በኋላም ቢሆን ካምፑ በወያኔ ጠላትነት ተፈረጀ በጸጥታ ሠራተኞች ከታገቱ በኋላ አድራሻቸው እስከዛሬ ተሰውሮ ላሉ በርካቶች በምስጢር እስርቤትነት በማገልገል ላይ ከሚገኙ ወታደራዊ ካምፖች አንዱ እንደሆ ይታወቃል።
ዘመድ አዝማዶቻቸው ይመለሳሉ ብለው ሲጠብቋቸው ሳይመለሱ እንደወጡ የሚቀሩ በርካታ ዜጎች አሉ። በእንዲህ ሁኔታ ወጥተው ከቀሩ መካከል ከሰሞኑ የስድስቱ መቃብር በአጋጣሚ ተገኝቷል። የተገነዙበት ብርድ ልብስ ይነትብና ምንም ዓይነት ብልሽት ሳይደርስበት መገኝቱ ግዲያው በህወሃት ዘመነ መንግስት ስለመፈፀሙ ጥሩ ማስረጃ ነው። ለህወሃት ሰው መግደል ሥራ እንጂ ወንጀል አይደለም። በህወሃት ነፍሰ ገዳይ ይሞገሳል ይሾማል እንጂ አይወቀሰም አይጠየቅም። የስድስቱ ስዎች አስከሬን ሲገኝ መንግስትነኝ የሚለው ህወሃት አይቶ እንዳላየ መሆን ብቻ ሳይሆን ሌሎች አካላትም የሥፍራውን ሚስጢር እንዳያዩ ከልክሏል።በቁጥጥሩ ሥር ያሉ መገናኛ ብዙሃንም ዜናውን እንዳይናገሩ ታግደዋል። ህወሃት ከሚሰራቸው አስገራሚ ወንጀሎች መካከል አንዱይሄው ነው። ይሄ ግድያ በሌላ አካል ተፈፅሞ ቢሆን ኑሮ በረከት ስምዖንና እና ሺመልስ ከማል እየተፈራረቁ ያደነቁሩን ነበር።ይሄ የራሳቸው የእጅ ሥራነውና አይነገርም። የሄንንም የሚናገር እንደ ኢሳት ያለ ነፃ ሚዲያ ካለም ይታፈናል። አሸባሪም እየተባለ ይፈረጃል።
ግንቦት ሰባት የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እነዚህ ዜጎች በህወሃት ተግድለው እንደተጣሉ ያምናል። ውሎ አድሮ እውነቱ እስከሚወጣ ድረስ ግን ዜጎች በሙሉ ይሄን ግድ በተመለከተ መረጃ የመሰብሰብና የማሰረጫት ሥራችውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ እናሳስባለን። ይሄን ወንጀል የፈፀሙ አካላት መጠየቅ አለባቸው። የዜጎች ደም እንዲሁ በከንቱ ፈሶ መቅረት የለበትም።
ለኢትዮጵያ ህዝብ መብትና ጥቅም እንታገላለን የሚሉ የፖለቲካና የስቪክ ድርጅቶች እንዲሁም ለሰው ልጆች የሰብአዊ መብት የሚሟገቱ ሁሉ የተገኘው አስከሬን በአስቸኳይ ተመርምሮ ማንነታቸው ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲገለጽ፤ ተጨማሪ አስከሬን ሊገኝ ይችላል በሚልስጋት የመንገድ ቁፋሮውን ከሰዎች እይታውጪ ለማካሄድ እንዲቋረጥ የተደረገው ሥራ ለህዝብ እይታ ግልጽ በሆነመንገድ በአስቸኳይ እንዲጀመር የመጠየቅ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ግንቦት 7 ያሳስባል::
በዚህአጋጣሚ ወያኔ ሥልጣን ከተቆጣጠረበት ጊዜጀምሮ በሱማሌ፣ በጋምቤላ፣ በአዋሳ፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባና ሌሎች የአገራችን ክፍሎች በጠራራ ጸሃይ ካስጨፈጨፋቸው በተጨማሪ በፖለቲካ እምነታቸው ምክንያት ታግተው በየእሥርቤቱ የተወረወሩትንና ከታገቱበት ዕለት ጀምሮ እስከ ዛሬ የደረሱበት ያልታወቁ ወገኖቻችንን ዝርዝር በአስቸኳይ ያሳውቅ ብለን አንመክረውም።እኛ ግን ህወሃት የደበቀውን ወንጀል ሁሉ ህዝብ እንዲያውቀው ለማድረግ ያለምንም ማቅማማት ጠንክረን እየሰራን ነው። መንግስት ነኝ ብሎ በሥልጣን ላይ የሚወጣ ማንኛውም አካል የህዝብ አገልጋይ እንጂ ነፍሰገዳይ እንዳይሆን የጀመርነው ትግል ተጠናክሮ ይቀጥላል።
እንግዲህ ህወሃት በህዝባችንና በአገራችን ላይ የሚፈጽመውን ሰቆቃ ለማስቆም ግንቦት 7 የጀመረውን የነጻነት ትግል አጠናክሮ እንደሚቀጥል እያስታወቅን እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እንዲህ በየቦታው ተገድሎ ከመጣል ራሱን ለመታደግ ሲል የነፃነቱ ትግል አካል እንዲሆን ጥሪያችንን አሁንም ደግመን እናቀርባለን::
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

Call for Protest! TPLF to hand out Ethiopian territory to Sudan


Click here for Amharic version

We shall not keep quiet while TPLF displaces Ethiopian people and hand out territory to Sudan!!!TPLF displaces Ethiopian people and hand out territory to Sudan

The anti-Ethiopia TPLF regime is making its final preparation to hand over 1200 km of legitimate Ethiopian territory to Sudan to please its ally in dictatorship– the war criminal Al Bashir. This border for which our great fathers paid in blood and our poor Ethiopian people are being displaced from is being given out in a secret deal without the knowledge and approval of the Ethiopian people. Such a treasonous act cannot and should not be allowed to happen. It is every Ethiopian’s, especially those living abroad in the free world, historical and moral obligation to let the Sudanese people as well as the entire world know that this deal is illegal and invalid, that the Ethiopian people will, sooner or later, do all needed to get it back.
Let us all come out and be a voice to our voiceless people by attending these historical protests at the Sudanese and later at the Woyane-TPLF Embassy
Date – Monday January 13, 2014
Time – 9:00 AM
Place – Embassy of Sudan
2210 Massachusetts Ave NW
Washington, DC 20008
Organizers – DC Joint Task Force
dcjointtaskforce@gmail.com
(202) 556-3078 begin_of_the_skype_highlighting (202) 556-3078 FREE  

Woyane’s jungle justices: Guilty until the evidence is manufactured?


When people get drunk on beer they become obnoxious but, by lust for power and money they become deadly. Playing zero-sum games of ‘us against them’ and ‘guilty until proven innocent by trumping on the rights and freedoms of our people is crude joke of diversions.
by Teshome Debalke
Ethiopia became a comedy club of TPLF‘s crude jokes In the last two decades but, nobody is laughing. It is another tragedy we as people are going through in our history where our rights became a commodity bought-and-sold by ethnic warlords.TPLF jungle justices
The stooges of Woyane masquerading as officials, cadres, parliamentarians, judges, journalists… are nothing more than impersonators of TPLF’s deadly jokes. That isn’t all, if you don’t take their crude jokes as real you are guilty of violating one thing or another—‘terrorism’ being their favorite joke these days for obvious reason. If that don’t work, there is always ‘corruption’,  ‘violating the constitutional order’ or my favorite one, ‘to change constitutionally elected government by unconstitutional means’ — as the former comedian chief extraordinary Birket Simon use to put it.
As a result, ‘guilty until proven innocent’ became Woyane’s trademark and weapon of mass terror at the cost of thousands of our people’s lives, rights and freedom.
When they say ‘little knowledge is dangerous’ they weren’t kidding. Thus, when a constitution became a cookbook of ethnic peddlers, it turned into a weapon-of-mass-division. When the courts became lodges of ethnic cadres, they turned into weapon-of-mass-punishments. When the security apparatuses became the club of ethnic assassins, it became a weapon-of-mass-terror. When Election Board becomes a coffee shop of ethnic stooges, it turned into a weapon-of-mass robbery of votes. When the Media becomes a studio of headless cadres, it turns into the weapon-of-mass-deception. When public resources fall under corrupt ethnic officials/cadres, it becomes the weapon-of mass-robbery, and on and on. Welcome to Revolutionary Democracy and Developmental State designed by self-declared minority warlords.
The former High court Judge Israel Feyesa interview on ESAT radio, (a must listen interview)  describing the lawless jungle justices of Woyane and the crude jokes of TPLF on the rights of our people. A true professional and patriotic Ethiopian we can’t afford not to listen to understand when justice falls in the hand of headless ethnic gangs of cadres. Moreover, we can’t seat idle when an out of control TPLF goons are dividing and destabilizing our community using ethnic warlords to sustain Minority Rule.
Woyane stooges and apologists must either be dumb enough to go along with the jungle justice or corrupt enough to clap with one hand and laughing their way to the bank with the other. There is no other explanation why their behaviors like headless chickens at the expense of the rights and freedom of the people of Ethiopia.
Ever since TPLF’s comedian extraordinary Meles Zenawi departed, the headless ethnic stooges seem to run out of material to humor us and are increasingly sounding silly.  Apparently, the ethnic warlord that replaced him wasn’t good enough to come up with his own crude jokes he was assigned deputy comedians to help him. In fact, at best the new warlord and his deputies can come up with is recycling the late TPLF’s warlord/comedian’s jokes.  Everywhere you look; it is like watching a re-run of the same crude jokes over-and-over again.
Likewise, Woyane cadres/comedians in Diaspora with privilege of seeking knowledge under the safety of the free world are parroting the same crude jokes.   The ‘terrorist are coming’ and’ the economy is growing by double digit’ seems the only line their miserable lives depended on.   The reality– the self-declared minority ethnic tyranny’s stooges are the only terrorist in the house that are terrorizing and robbing the people of Ethiopia by double digit don’t seem to cross their mind for the obvious reasons.
Cruder cadres/comedians among the Diaspora are those masquerading as journalist and Media–running around in circle like headless chickens.  It isn’t knowledge they are  lacking nor deprived of freedom to express it, but lack of character made them ride the low road on behalf of ethnic tyranny that are committing heinous crimes on Ethiopians.
Unfortunately, a little perk for people confined in ethnic cage can go a long way of making headless stooges talk with both sides of their mouth. How long they remain accessory to crime–playing these deadly crude jokes remain to be seen.
Don’t get the wrong impression, stooges and apologists of Woyane are not the only crude comedians in our community. There are many comedians more than we need. Some in the ‘opposition’ camp can be as crude jokers as Woyane stooges and apologists.  The more visible and vocal one that comes in mind is ‘Oromo First’ comedian Jawar Mohamed and Co. The young and confused ethnic comedian that often  throws the ‘baby with the bathwater’ every time he opens his mouth continue to reduces the rights and freedom of our people into comedy show. He reminds me of the Eritrean Liberation Front’s comedians that played the crude joke on our people to end up dividing them from motherland and ended up with no liberation, freedom, rights or mother or fatherland.
I think this liberation movement is a deliberate ploy of opportunists to divide and deprive our people their freedom, their rights and their country and the evidence is compelling.
Jawar and Co. isn’t any different following the footsteps of his mentors.  His group last crude joke of the year was when they  render Emperor Menlik II guilty until proven innocent for the loss of’ 5 million ‘Oromos’ during his rule.   When we found out the entire population of Ethiopia was only seven million at that period, the ‘Oromo First’ comedian of the year and the Colombian University student- expert in ‘peaceful movement’ and ‘political analyst’ was mute to man-up. The man that is willing to pile up numbers of our people’ killed that were not even born at the period in order to render guilty verdict on the legendary ‘King of Kings’ Menilik II isn’t expert of anything nor liberator of anybody or freedom fighter for anyone, but an out of control bigot that charge, prosecute and convict by manufacturing evidence. The machete intellectual is no good for our people, Oromo or otherwise. Turning the basic tenant of democracy –due process of law in its head, he is swinging his machete indiscriminately against our people following the foot step of TPLF.
His latest crude joke was boycotting a beer factory for sponsoring Teddy Afro concert. No one knows whether he is calling on Ethiopians of only ‘Oromo’s’  and  Muslims he claim to belong  or crossing boundaries Woyane erected when it serves his interest. But, whatever it is, his target wasn’t the beer factory or Teddy Afro but Guilt by association of Emperor Menilik II with the ‘Amharas’   –  rendering then guilty until proven innocent as he manufactures more evidence.
Don’t get me wrong, I enjoy Jawar making good points for our people and as much as I am digested with his crude jock when it serve his agenda.  But, when I hear any self-appointed ethnic peddlers play opportunistic politics — cherry-picking what suites them, as he does it makes me sick to my stomach.
For example, from all pressing issues of our people under Woyane ethnic tyranny is boycotting a beer brand the best Jawar can come up with? Where are boycotting Woyane’s factories of corruption; robbing our people blind? How about boycotting ethnic peddlers like him that make up stories to create conflicts among our people? And most importantly, how about advocating the democratic rights of the people he claims to represent to choose their destiny with their people and country?
Such crude joke is what is wrong with our contemporary elites or ‘the functionally illiterate intellectuals’, as Professor Ayatee refer them.  More saddening, what is the young 20 plus years’ old doing—peddling ethnicity and religion of the ‘hippo generation’ than democracy and the rule of law of ‘the cheetah generation’? Don’t beat on snake oil salesmen that promise milk and honey and deliver…
Comedian aside, the people of Ethiopia are not pawns for opportunist politicians of one form or shape masquerading as one thing or another.  Nor, the lives and rights of the people an academic exercise of out of control ethnic peddlers, religious zeolites, ideology pushers or Merchants-of- death. Let’s get it in our head; the rights of the people of Ethiopia can’t be retailed by adventurist. Whatever we do — peddling our political or economic interest, we have to understand, not only the crude comedians of Woyane have to go but, we all have to come to grips with the reality to surrender to the rights and freedom of our people.  No matter what kind of crude jokes the ‘revolutionary democracy’ or ‘developmental state’ that comes out of Woyane ethnic tyranny or all kinds of promises from anyone else nothing short of democracy is acceptable.
Therefore, there is no argument or disagreement on the rights and freedom of our people. Thus, if one claims to be political party, Media, advocacy group, liberator of one form or another there is nothing left worth talking but doing — surrender for the democratic rights of the people and reject everything else. Is it too much to ask or too hard to comprehend?
Coming back to our contemporary crud comedians, it seems their relevancy depends on the constant conflict they create among our people to divert the issue.  I say, when people get drunk by beer they become obnoxious but, by lust for power and money they become deadly. Playing a zero-sum game of ‘us against them’ and ‘guilty until proven innocent’ by trumping on the rights and freedom of our people is crude jock of diversion that must end now.
Our contemporary ethnic elites are losing their mind — drunken by the lust for power and money to think our people are pawns for their crud and deadly jocks.  The only advice I can offer them is; don’t act like headless chickens on the expenses of our people.
The democratic rights of our people can’t and wouldn’t be negotiated by anyone with anybody. There is no us and them, but us and tyranny of all form starting with Woyane.  Woyane and its comedian stooges must surrender. The rest of us must submit to the will of our people. There is nothing more or less to say.
It’s about time every Ethiopian speaks now or never. The silence is leaving our people and country pawns and playground of ethnic and religion peddlers and the Merchant-of-Death.
If we love our people and country as we claim; ‘don’t ask what your people and country should do for you ask what you can do to your people and country’.  In our case, it is only to respect the democratic rights and freedom of our people no matter what the peddlers tell us otherwise.
The line is drawn; Woyane’s stooges are running like headless chicken to sustain ethnic tyranny. Ethiopians are chasing the stooges and demanding surrender to the democratic rule. If I may suggest for all current supporters and stooges of Woyane and the Regime, take the money as it will dry up in the coming years but come clean with your conscience and give up the information you know and have that will shake the regime and uproot it once and for all.  You all know who to feed the stories keep it coming and play your part.  You can hide from your people that are yearning for change but not from your God and your consciences.
Which side you want to be? If and but is not going to do it and my dog ate my homework is not an option.

የ 2013 የዓለም የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት፡- ኢትዮጵያ

 

600px-Hrw_logo

ኢትዮጵያን ለረጅም ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የመሩትና ሰፊ ስልጣን የነበራቸው መለስ ዜናዊ በነሃሴ ወር በድንገት መሞት በሃገር ውስጥም ሆነ በኢትዮጵያ ዓለማቀፍ አጋሮች ዘንድ የሀገሪቱን ፖለቲካዊ ሽግግር የሚመለከቱ ጥያቄዎችንና አጠራጣሪ ሁኔታዎችን አስነስቶ ነበር።በኢትዮጵያ ያለው የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በተለይ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ እየከፋ ሄዷል።አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በመስከረም ወር ስልጣኑን የተረከቡ ቢሆንም መንግስት በርሳቸው አመራር ሰብአዊ መብቶችን የሚመለከቱ ለውጦች ያደርግ ወይስ አያደርግ እንደሆነ ገና የሚታይ ነው።
እ.ኤ.አ በ2012ም የኢትዮጵያ ባለስልጣናት መሰረታዊ የሆኑትን ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣ የመደራጀት እና የመሰብሰብ መብቶች በጥብቅ መገደባቸውን ቀጥለዋል።ለኣሻሚ ትርጉሞች በተጋለጠውና በ2002 ዓ.ም በወጣው የሀገሪቱ የጸረ ሽብርተኝነት ሕግ 30 ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባላት ተከሰው ተፈርዶባቸዋል።በዋና ከተማዪቱ አዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል የእስልምና እምነት ተከታዮች ላካሄዷቸው የተቃውሞ ሰልፎች የጸጥታ ሃይሎች የሰጡት ምላሽ የዘፈቀደ አፈሳ፣ እስር እና ድብደባ ነበር።
የኢትዮጵያ መንግስት በአምስት ክልሎች የሚኖሩ የገጠር ነዋሪዎችን የተሻለ የመሰረታዊ ግልጋሎቶች አቅርቦት ሊያገኙ ወደሚችሉባቸው አካባቢዎች ለመውሰድ በሚል ምክንያት 1.5 ሚሊዮን የገጠር ነዋሪዎችን መልሶ ለማስፈር የሚያካሂደውን የሰፈራ ፕሮግራም ቀጥሎበታል።በጋምቤላ ክልል የሚገኙ በርካታ ነዋሪዎች ከፍላጎታቸው ውጭ በሃይል እንዲፈናቀሉ በመደረጋቸው ለከፍተኛ ችግሮች ተጋልጠዋል። ከዚህ በተጨማሪም መንግስት ለሚያካሂደው ሰፊ የስኳር ልማት መሬት ለማስለቀቅ ሲባል በኢትዮጵያ የታችኛው ኦሞ ሸለቆ ነዋሪ የሆኑትን አርብቶ አደር ማህበረሰቦች ከመኖሪያቸው እንዲፈናቀሉ እያደረገ ነው።
ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣የመደራጀት እና የመሰብሰብ መብቶች
መንግስታዊ ያልሆኑ ደርጅቶችን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር  የበጎ አድራጎት ደርጅቶች እና ማህበራት አዋጅ እንዲሁም የጸረ ሽብርተኝነት ሕግ በ2002 ዓ.ም ከታወጁ ወዲህ በኢትዮጵያ ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች ከፍተኛ ገደብ ተጥሎባቸዋል። እነዚህ ሁለት ሕጎች መንግስት በሲቪል ማህበረሰብ መሪዎች፣በጋዜጠኞች እና በሌሎችም የመንግስትን ፖሊሲ በሚተቹና መንግስት እንዲነሱ በማይፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ ሃሳባቸውን በሚገልጹ ሰዎች ላይ ካካሄደው ሰፊ እና የማያቋርጥ ማዋከብ፣ዛቻ እና ማስፈራራት ጋር ተዳምሮ ያስከተሉት  ውጤት የከፋ ነው።
ኢትዮጵያ ውስጥ እጅግ የጎላ እንቅስቃሴ ያደርጉ የነበሩ የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች እንቅስቃሴዎቻቸውን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲቀንሱ ወይም ሰብአዊ መብቶችን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ከስራ ዝርዝራቸው ውስጥ እንዲያወጡ የተገደዱ ሲሆን ቁጥራቸው ያልታወቀ ድርጅቶችም ጭራሹኑ ተዘግተዋል። በደረሰባቸው ማስፈራሪያ ምክንያት ሰፊ ልምድና መልካም ስም የነበራቸው ብዙ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ሃገሪቱን ለቀው ሄደዋል። አሁን ሰፍኖ የሚገኘው ሁኔታ ለነጻ ፕሬስ እንቅስቃሴም እንዲሁ የተመቸ አይደለም።ባለፉት አስር ዓመታት በደረሰባቸው ዛቻ እና ማስፈራራት ሳቢያ ሃገራቸውን ለመልቀቅ በተገደዱ ጋዜጠኞች ቁጥር በዓለም ኢትዮጵያ ቀዳሚዋ ናት። የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች የሆነው ድርጅት ሲፒጄ እንደሚገልጸው ቢያንስ 79 ጋዜጠኞች ሃገራቸውን ለቀው ለመሰደድ ተገደዋል።
የጸረ ሽብርተኝነት አዋጁ፣ ተቃዋሚ ናቸው ተብለው የሚታሰቡ ሰዎችን ዒላማ ለማድረግ፣ተቃውሞን ለማፈን እና ጋዜጠኞችን ዝም ለማሰኘት ስራ ላይ እየዋለ ነው። እ.ኤ.አ በ2012 ዓ.ም 30 የፖለቲካ መሪዎች፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት እንዲሁም ጋዜጠኞች በግልጽ ባልተብራሩ የሽብርተኝነት ወንጀሎች ተከሰው ተፈርዶባቸዋል።ከ2011 ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ 11 ጋዜጠኞች በዚሁ ሕግ ተከሰው ተፈርዶባቸዋል።
ጥር 17 ቀን 2004 ዓ.ም አሁን የተዘጋው አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ምክትል አዘጋጅ በነበረው ውብሸት ታዬ እና የጋዜጣው ዓምደኛ በነበረችው ርዕዮት ዓለሙ ላይ በአዲስ አበባ የሚገኝ ፍርድ ቤት የ 14 ዓመታት እስር ፈርዶባቸዋል።የርዕዮት ዓለሙ ፍርድ በኋላ በይግባኝ ወደ አምስት ዓመታት የተቀነሰ ሲሆን ከቀረቡባት ክሶች ውስጥም አብዛኞቹ ተሰርዘዋል።
ከፍተኛ ክብር ያለውን የፔን አሜሪካ ፍሪደም ቱ ራይት ሽልማት በሚያዝያ ወር 2004 ዓ.ም ያሸነፈው አንጋፋው ጋዜጠኛ እና ብሎገር እስክንድር ነጋ ሐምሌ 6 ቀን 2004 ዓ.ም ከሌሎች ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ጋር በቀረበበት ክስ የ 18 ዓመታት እስራት ተፈርዶበታል። በስደት ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞች አብይ ተክለማርያም እና መስፍን ነጋሽም እስካሁን ድረስ ጋዜጠኞች ላይ ብቻ ተግባራዊ በተደረገው የጸረ ሽብርተኝነት ሕጉ አንቀጽ መሰረት ጥፋተኛ ተብለው እያንዳንዳቸው የ 8 ዓመታት እስራት ተፈርዶባቸዋል። በይፋ ተመዝግቦ የሚንቀሳቀሰው ተቃዋሚ ፓርቲ አንድነት ለፍትሕ እና ለዲሞክራሲ አባል የሆነው አንዷለም አራጌ በስለላ፣ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በመናድ እንዲሁም የሽብር ተግባር ለመፈጸም ምልመላ እና ስልጠና በማካሄድ ወንጀሎች ጥፋተኛ ተብሎ የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበታል።
በመስከረም ወር 2004 ዓ.ም የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእስክንድር ነጋ እና በስደት ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ አበበ በለው  እንዲሁም የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባሉ አንዷለም አራጌ ንብረቶች እንዲወረሱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ፍትሕ ጋዜጣ የእስልምና እምነት ተከታዮች የሚያካሂዱትን ተቃውሞ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩን የጤንነት ሁኔታ አስመልክቶ ያዘጋጃቸው ዘገባዎች የሃገሪቱን ብሔራዊ ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ናቸው በማለት መንግስት ሀምሌ 20 ቀን ጋዜጣው እንዳይሰራጭ አግዷል። ነሃሴ 18 ቀን 2004 ዓ.ም የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝ በቁጥጥር ስር ውሎ ዋስትና ተከልክሏል። ተመስገን ነሃሴ 24 ቀን ከእስር የተለቀቀ ሲሆን ተጨማሪ ምርመራ እስኪካሄድ ድረስ ሁሉም ክሶች ተነስተውለት ነበር።
ሀምሌ 13 ቀን 2004 ዓ.ም ‘የሙስሊሞች ጉዳይ’ የተሰኘው ተወዳጅ የሙስሊሞች መጽሄት ዋና አዘጋጅ የሆነው የሱፍ ጌታቸው ቤት በፖሊሶች የተፈተሸ ሲሆን በዚያው ዕለት ምሽትም የሱፍ በቁጥጥር ስር ውሏል። መፅሄቱ ከዚያ በኋላ መታተም ያቆመ ሲሆን ይህ ዘገባ እስከሚዘጋጅበት ጊዜም የሱፍ በቁጥጥር ስር ይገኛል።
በሕገ ወጥነት ከተፈረጀው አማጺው የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር ጋር በምስራቃዊ ኢትዮጵያ ሲንቀሳቀሱ በቁጥጥር ስር የዋሉት ማርቲን ሺብዬ እና ዮሃን ፒርሰን የተባሉ ሁለት ስዊድናውያን ጋዜጠኞች ለሽብርተኛ ድርጅት ድጋፍ በመስጠት ወንጀል  ታህሳስ 17 ቀን 2004 ዓ.ም የጥፋተኝነት ውሳኔ ተሰጥቶባቸዋል። በተጨማሪም በሕገ ወጥ መንገድ ወደሃገሪቱ በመግባት ጥፋተኞች ተብለዋል።ፍርድ ቤቱም በ 11 ዓመት እስራት እንዲቀጡ ወስኗል። ሁለቱ ጋዜጠኞች አዲሱን ዓመት በማስመልክት በየዓመቱ ለእስረኞች በሚሰጠው ምህረት ከሌሎች 1950 በላይ ከሚሆኑ እስረኞች ጋር ምህረት ተደርጎላቸው ጳጉሜ 5 ቀን 2004 ዓ.ም ከእስር ተለቀዋል።
መንግስት በሃገሪቱ የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ጉዳዮች ምክር ቤት ውስጥ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት በመቃወም ለታቃውሞ የወጡ የእስልምና እምነት ተከታዮችን ለመበተን በሐምሌ ወር 2004 በተለያዩ ቀናት የፌደራል ፖሊስ ድብደባን ጨምሮ ከልክ ያለፈ ሃይል ተጠቅሟል።ሀምሌ 6 ቀን አዲስ አበባ ወደሚገኘው  የአወሊያ መስጊድ በሃይል በመግባት ፖሊሶች መስኮቶችን የሰባበሩ ሲሆን በመስጊዱ ውስጥ አስለቃሽ ጭስ ተኩሰዋል። ሐምሌ 14ም  በመስጊዱ ለተቃውሞ ተቀምጠው የነበሩ ሰዎችን ሃይል በመጠቀም እንዲበተኑ አድርገዋል። ከሐምሌ 12 እስከ 14 በነበሩት ቀናትም በርካታ ሰዎች የታፈሱ ሲሆን 17 ከፍተኛ የእምነቱ መሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ክስ ሳይመሰረትባቸው ከአንድ ሳምንት በላይ በእስር ቆይተዋል።ብዙዎቹ ታሳሪዎች በእስር ላይ እያሉ ማንገላታት እንደተፈጸመባቸው ገልጸዋል።
ተገዶ መፈናቀል
ሰፈራ በሚባለው ፕሮግራሙ የኢትዮጵያ መንግስት በአምስት ቆላማ ክልሎች ማለትም በጋምቤላ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣በአፋር፣ በደቡብ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦች እና ሕዝቦች እንዲሁም በሶማሌ ክልሎች የሚኖሩ 1.5 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎችን የተሻለ የመሰረታዊ አገልግሎቶች አቅርቦት ወደሚያገኙባቸው አካባቢዎች ለማዛወር በሚል ወደሌሎች ቦታዎች ወስዶ ለማስፈር እቅድ አለው።
በጋምቤላ እና በደቡብ ኦሞ ሸለቆ ከነዋሪዎች ጋር በቂ የቅድሚያ ምክክር ሳይደረግ እና የካሳ ክፍያ ሳይፈጸም አስገድዶ የማፈናቀል ተግባር እየተፈጸመ ነው።ሂዩማን ራይትስ ዎች እንዳረጋገጠው በተለይ በጋምቤላ ወደሌሎች አካባቢዎች አዛውሮ የማስፈሩ ሂደት የሚከናወነው ብዙ ጊዜ ነዋሪዎቹን ለም የሆኑ መሬቶቻቸውን በማስለቀቅ አነስ ያለ ለምነት ወዳላቸው መሬቶች በማስፈር ነው።ወደ አዳዲሶቹ መንደሮች እንዲሰፍሩ የሚላኩት ሰፋሪዎች አብዛኛውን ጊዜ መሬታቸውን መመንጠር እና ጎጆዎቻቸውን መስራት ያለባቸው ሲሆን ይህንንም በወታደሮች ተቆጣጣሪነት ያከናውናሉ።ቃል የተገቡላቸው አገልግሎቶች ማለትም ትምህርት ቤቶች፣ክሊኒኮች እና የውሃ ፓምፖች የተሟሉ አይደሉም።
በደቡብ ኦሞ ቁጥራቸው ወደ ሁለት መቶ ሺህ የሚደርስ ተወላጅ ሕዝቦች መንግስት ለሚያካሂደው የስኳር ልማት ቦታ ለማስለቀቅ ሲባል መሬታቸው ተወርሶ ወደሌሎች አካባቢዎች እንዲሰፍሩ እየተደረገ ነው። ነዋሪዎቹ ከመሬቶቻቸው ላይ በሃይል እነደሚነሱ፣የግጦሽ መሬቶቻቸው በጎርፍ እንዲጥለቀለቁ እንደሚደረግ፣ ማሳዎቻቸው እንደሚገለበጡ እንዲሁም ለህልውናቸው እና ለአኗኗር ዘይቤአቸው እጅግ አስፈላጊ የሆነውን የኦሞ ወንዝ ውሃ እንዳያገኙ እንደሚከለከሉ ተናግረዋል።
ሕገ ወጥ ግድያ፣ማሰቃየት እና በቁጥጥር ስር ባሉ ሰዎች ላይ የተፈጸሙ ጥሰቶች
በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በጋሸሞ ወረዳ ራቅዳ በተባለች መንደር ከነዋሪዎች ጋር የተፈጠረን ግጭት ተከትሎ ‘ልዩ ሃይል’ በሚል ስያሜ የሚታወቅ፣ በኢትዮጵያ መንግስት የሚደገፍ ታጣቂ ቡድን በቁጥጥሩ ስር የነበሩ 10 ሰዎችን እና ሌሎች 9 የመንደሩ ነዋሪዎችን የገደለው መጋቢት 7 እና 8 ቀን 2004 ዓ.ም ነበር።
በሚያዝያ ወር 2004 ዓ.ም ማንነታቸው ያልታወቀ መሳሪያ የታጠቁ ሰዎች በጋምቤላ ክልል በሚገኝ እና ባለቤትነቱ የሳውዲ ስታር ኩባንያ በሆነ ሰፊ እርሻ ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል። ይህ የእርሻ ልማት በክልሉ የሰፈራ ሂደት በተካሄደበት ወቅት የከፋ የመብቶች ጥሰቶችና ማንገላታት ከተፈጸመባቸው አካባቢዎች በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው። ለዚህ ጥቃት ምላሽ ለመስጠት የኢትዮጵያ ወታደሮች ቤት ለቤት በመዞር ድርጊቱን ፈጽመዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎችን የፈለጉ ሲሆን የአካባቢውን ነዋሪዎችም ‘አማጺያኑ’ የሚገኙበትን ቦታ አጋልጡ በማለት ሲያስፈራሯቸው ነበር። ወታደሮቹ በርካታ ወጣት ወንዶችን በዘፈቀደ ከማሰራቸውም በላይ ስለ ጥቃቱ መረጃ ለማግኘት ባደረጉት ሙከራ ማሰቃየት፣አስገድዶ መድፈር እንዲሁም ሌሎች ጥሰቶችን በብዙ ነዋሪዎች ላይ ፈጽመዋል።
ሂዩማን ራይትስ ዎች በአዲስ አበባ ማዕከላዊ በመባል በሚታወቀው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጣቢያ እና በክልሎች በሚገኙ የእስር ቦታዎች እንደዚሁም በሶማሌ፣ በኦሮሚያ እና በጋምቤላ ክልሎች በሚገኙ ወታደራዊ ካምፖች ውስጥ የሚፈጸሙ የማሰቃየት ድርጊቶችን የሚመለከቱ መረጃዎችን ማሰባሰቡን ቀጥሏል። በእነዚህ የእስር ጣቢያዎች ከፖለቲካ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች የተያዙ ታሳሪዎች ከጠበቆቻቸው ጋር የሚገናኙበት እድል በጣም የመነመነ ሲሆን በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎች ከፍርድ ሂደት በፊት እና በፍርድ ሂደት ወቅት ሊከበሩላቸው የሚገቡ መብቶችን ለማክበር ያለው ፍላጎትም  በጣም አናሳ ነው። ይህም ታሳሪዎቹን ለከፉ ጥሰቶች ያጋልጣቸዋል።
የስደተኛ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች አያያዝ
በሊባኖስ የቤት ሰራተኛ የነበረቸው ኢትዮጵያዊት ዓለም ደቻሳ ደሲሳ ድብደባ ሲፈጸምባት የሚያሳየው ቪዲዮ ከተሰራጨና ይህነኑ ተከትሎም ዓለም መጋቢት 5 ቀን 2004 ዓ.ም ሕይቷን ካጠፋች በኋላ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩት በመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት በቤት ሰራተኝነት የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ሴቶች የሚደርስባቸው መከራ የተጠናከረ ትኩረት አግኝቶ ነበር። ብዙ በስደት የሚሰሩ የቤት ሰራተኞች ወደ ውጭ ሃገራት ሄደው ከመቀጠራቸው በፊት ከባድ የገንዘብ ዕዳ ውስጥ ይገባሉ፤ እንዲሁም ከቅጥር ሂደቱ ጋር የተያያዙ ሌሎች ማንገላታቶች ይፈጸሙባቸዋል።ውጭ ሀገር ሄደው ስራ ከጀመሩም በኋላ ለረጅም ሰዓታት ከመስራት በተጨማሪ ባርነት በሚመስሉ የስራ ሁኔታዎች ውስጥ እንዲሰሩ ይደረጋሉ፣ እንዲሁም ሌሎች  መጠነ ሰፊ ጥቃቶች ይደርሱባቸዋል።(የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ሳኡዲ አረቢያ እና ሊባኖስን የሚመለከቱትን ምዕራፎች ይመልከቱ)።
ዋና ዋና ዓለማቀፍ አጋሮች
በመለስ ዜናዊ አመራር ኢትዮጵያ በአካባቢ ጉዳዮች ላይ የጎላ ሚና ትጫወት ነበር።ወደ አወዛጋቢው የሱዳን አቢዬ ክልል በተባበሩት መንግስታት ስር የሰላም አስከባሪ ሃይሎችን አሰማርታለች፣በሱዳን እና በደቡብ ሱዳን መካከል የነበረውን አለመግባባት ሸምግላለች እንዲሁም አል ሸባብን ለመውጋት የተደረገውን ዓለማቀፍ ጥረት ለማገዝ ሰራዊቷን ወደሶማሊያ ልካለች። እ.ኤ.አ ከ 1998-2000 ድረስ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተካሄደውን ከፍተኛ ዋጋ ያስከፈለ ጦርነት ተከትሎ ኢትዮጵያ ከጎረቤቷ ኤርትራ ጋር ያላት ግንኙነት መልካም አይደለም። ኤርትራ ለግጭቱ መነሻ የነበሩ ቦታዎች ለኤርትራ እንደሚገቡ የወሰነውን የድንበር ኮሚሽን ውሳኔ የተቀበለች ሲሆን  ኢትዮጵያ ግን ውሳኔውን አልተቀበለችም።
ኢትዮጵያ ለምዕራብ መንግስታት ጠቃሚ ስትራተጂያዊና የደህንነት አጋር ስትሆን ከእነዚህ መንግስታት በአፍሪካ ከፍተኛውን የልማት እርዳታ የምታገኝ ሀገርም ናት።በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በዓመት  ወደ 3.5 ሚሊዮን የሚደርስ የአሜሪካን ዶላር በረጅም ጊዜ የልማት እርዳታ መልክ ታገኛለች።የለጋሽ ሃገራት ፖሊሲዎች በሀገሪቱ እየከፋ ከሄደው የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ጋር በተያያዘ ብዙም የተለወጡ አይመስሉም።
እ.ኤ.አ በመስከረም ወር 2012 የዓለም ባንክ ራሱ እና ሌሎችም የልማት ተቋማት ዘለቄታ ላለው ልማት እጅግ አስፈላጊ ናቸው የሚሏቸውን የሰብአዊ መብቶች እና የመልካም አስተዳደር መርሆች ብዙም ከግምት ውስጥ ያላስገባ አዲስ ብሔራዊ የጋራ ሰትራተጂ ባንኩ አጽድቋል።ባንኩ በተጨማሪም ሦስተኛውን ዙር የመሰረታዊ አገልግሎቶች ጥበቃ ፕሮግራም (ፒቢኤስ 3)ያለፈቃድ የሚደረግ ሰፈራን የሚከለክሉ እና ለተወላጅ ሕዝቦች ጥበቃዎችን የሚያደርጉ ድንጋጌዎችን ሳያካትት አጽድቋል።