Sunday, April 13, 2014

በሞት አፋፍ ላይ ተቀምጠው እውነትን የፈሩ


ብሩክ ሲሳይ (አዲስ አበባ)
ያለወትሮዬ ሴንትራል ሆቴል ቁጭ ብያለሁ ከጎኔ ሁለት ሽማግሌዎች ተቀምጠዋል ብቻዬን በመሆኔ እና የሽማግሌዎች ወግ ስለምወድ እነዚህ ሁለት አዛውንቶች የሚያወሩት ወሬ ላይ ጆሮዬን ጥያለሁ፤ ከአገራችን ፖለቲካ ጀምሮ እስከ ልጅነት ህይወታቸው እና ሌሎችም ብዙ ነገሮችን እያነሱ ያወራሉ። ከወሬያቸው እንደተረዳሁት አንደኛው አዛውንት ከአሜሪካ ቨርጂኒያ ለእረፍት የመጡ ዲያስፖራ ናቸው ሌላኛው ደግሞ በኢህአዴግ የፖለቲካ ስልጣን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃወች ያገለገሉ እና ኢህአዴግ መጥጦ መጥጦ የወረወራቸው አዛውንት ናቸው። ወሬያቸው ግሏል ግንቦት 7 እና የግብፅ እና የሻብያ ተላላኪዎች፣ የጨረቃ ቤቶች፣ የመተማ እና የሱዳን ጠረፍ መሬቶች፣ መለስ ዜናዊ፣ ብርሀኑ ነጋ፣ ሟች ጳጳስ ጳውሎስ፣ አልማ፣ የዲያስፖራው አክራሪነት ወዘተ አይነት ነገሮች እየተወሩ ነው። ጋባዥ ስለሆኑ ነው መሰለኝ ብዙ የሚያወሩት ዲያስፖራው አዛውንት ናቸው ተጋባዥ አዛውንት ደግሞ ራሳቸውን በመነቅነቅ ድጋፍ ይሰጣሉ።Russian old Lada's in Addis Ababa, Ethiopia
የጨረቃ ቤት መፍረስ ትክክል ነው አሉ ዲያስፖራው ብዙ ማብራሪያ በመስጠት ፣ ያኛው አዛውንት ደግሞ የተዋጠላቸው አይመስልም ወደ እኔ ዞሩ እኔ ደግሞ ያልሰማሁ ይመስል ሞባይሌን መነካካት ያዝኩኝ ግን ጆሮየም ልቤም ወሬው ላይ ነው። አዛውንቱ ዲያስፖራ የሚናገሩት በሙሉ ያበሽቃል ብቻ ግን እኔ እያዳመጥኩኝ ነው፤ በመቀጠል አልማ አሜሪካ ላይ ገቢ ማሰባሰቢያ ሲያደርግ ቶምቦላ እንደገዙ (ያኔ ደመቀ መኮነን፣ ህላዊ ዮሴፍ፣ ካሳ ተክለብርሀን ወዘተ ሲዋረዱ ማለት ነው)፣ ለአማራ ልማት ብር እንደለገሱ፣ አቡነ መርቀርዮስ የሚባሉት ጳጳስ መለስ ዜናዊ እና አቡነ ጳውሎስ የሞቱት በህዝብ እንባ እና በእግዚአብሄር ቁጣ ነው ብለዋል፣ ወደ ኤርትራም ሶስት ጊዜ በመሄድ አርበኞች ግንባርን አበራትተዋል የአሜሪካን ምዕምናንም ገንዘብ እየዘረፉ ነው በማለት ከላይ ከታች አብጠለጠሉ፣ ሙስሊም ኢትዮጵያውያንንም እንደ ኢራቅ ሊያደርጉን ነው አሏቸው፣ ሰ’ማያዊ ፓርቲዎችንም እነሱ ከእንጦጦ መጥተው ስለ መተማ መሬት ምና አገባቸው እና መንግሥት ያልሰጠውን መሬት ለሱዳን ሰጠ ብለው በውሸት አመፅ ሊያስነሱ የሚፈልጉት እያሉ ሲቀጥሉ አላስችለኝ አለ አቁነጠነጠኝ አፌን በላኝ እኚህ የሽማግሌ ወራዳ አናደዱኝ ከዚያም “ይቅርታ አድርጉልኝ በወሪያችሁ ጣልቃ ገባሁ” በማለት
“የመተማ እና ሌሎች የሱዳን አዋሳኝ መሬቶች እንዳልተሰጡ በምን አወቁ?” አልኳቸው እሳቸው ሲመልሱ
“መንግስት አልሰጠሁም እያለ ነው፣ ጠ/ሚኒስተሩ በቴሌቪዥን ውሸት ነው ብለዋል ይሄን የሚያወሩት ተቃዋሚዎች ናቸው በውሸት ህዝብን ሊያሳምፁ ነው” አሉኝ እኔ ደግሞ ጥያቄየን ቀጠልኩ
“መንግስት መሬት ቢሰጥስ በአደባባይ ሰጥቻለሁ ብሎ የሚያወራ ይመስልወታል? እንዴትስ መንግስትን እና የመንግስት ሜዲያን ያምናሉ? የኛ መንግስት ባለስልጣናት እና ሜዲያዎች እኮ መለስ ዜናዊ መሞቱ እየታወቀ የአዲስ አመት ዘመን መለወጫ ይመጣል የሚሉ ናቸው፣ የባድመ እና ዛላንበሳ መሬቶች በአለም አቀፍ ፍርድ ቤት ዳኝነት ለኤርትራ ተወስኖ እያለ ነገር ግን የኛ መንግስት በውሸት ለኢትዮጵያ ነው የተወሰነው በማለት ህዝብን ሰላማዊ ሰልፍ የሚያስወጣ ነው፣ በ97 ምርጫ የ14 አመት ህፃን ገድለው ባንክ ሊዘርፍ ሲል ነው የተገደለው የሚል መንግስት፣ ሜዲያ እና ማፍያ ባለስልጣናት እንዴት ያምናሉ? ከፈለጉ ደግሞ መሬቱ በሱዳን መንግስት የተወሰደበት ተማሪየን ላገናኘወት እችላለሁ………”
ሰውየው ትንሽ ረጋ አሉ እና “በድንበር አካባቢ ችግር ሊኖር ይችላል ነገር ግን ከግብፅ እና ሻብእያ ጋር በመላላክ እነ ግንቦት 7 እና ብርሀኑ ነጋ ኢሳትን በመጠቀም የሚያናፍሱት ወሬ ነው” አሉኝ። እኔም
“ለምንድን ነው ብርሀኑ ነጋ እና ግንቦት 7 ከሻቢያ ጋር የሚሰሩት?” ብዬ ስጠየቃቸው። እሳቸውም
“ብር ነዋ ሆዳም ስለሆኑ በግብፅ በኩል ገንዘብ ለማግኘት ነው” አሉኝ። እኔም
“ይህ ዶ/ር ብርሀኑ የሚባሉ ሰውየ አገር ውስጥ በነበሩበት ጊዜ ባለሀብት ናቸው፣ ቤተሰቦቻቸውም እንደዚያው ናቸው። ታዲያ ይሄን ሰው ብር ፈልገው ነው ማለት አይከብድም ወይ? ደግሞስ ብር ቢፈልጉ ይህ ሰውየ ከኢህአዴግ ጋር ተሞዳሙደው አገሪቱን መዝረፍ ያቅታቸዋል ብለው ነው? ህሊናን ሽጦ ከዚህ መንግስት ጋር ተሞዳምዶ ሀገር መዝረፍ እኮ በጣም ቀላል ነገር ነው ምናልባት ለእርሰዎ ከብዶዎት ካልሆነ?” ስላቸው መልሳቸውን ወደ ምክር በማዞር
“እናንተ ወጣቶች እየተሸወዳችሁ ነው፣ በዚህ እድሚያችሁ መስራት፣ መማር፣ ገንዘብ መያዝ ነው ያለባችሁ እዚያ አሜሪካ ሁሉም ስራ ላይ ነው ታች ላይ የሚለው፣ እንደ እኛ ጊዜ አትሸወዱ እየው ሀገሪቱ እያደገች ነው በዚህ እድል መጠቀም አለባችሁ” አሉኝ እኔ ደግሞ ቀጠልኩኝ
“እርሰዎ ከአሜሪካ መጥተው የነፃ መሬት ከመንግስት ተበርክቶለዎት ለንግድ ቤት የሚሆን ህንፃ እየሰሩ ነው። እኔ ግን ህዝቤን እያገለገልኩ ለቤት መስሪያ የምትሆን ቁራጭ መሬት መንግስት ነፍጎኛል፣ ይህች አገራችን ለልጆቿ በቀላሉ የምታበረክተው ነገር ቢኖር መሬት ነበር ነገር ግን ይህንን ቀላሉን ነገር ተነፍገናል። ታዲያ የእርሰዎ ሀገር ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰአት ለእኔ አገሬ ናት ማለት እችላለሁን? ኢትዮጵያ ውስጥ በሀገሬ ያለኝ መብት ከአንድ ሱዳናዊ ወይም ህንዳዊ ግለሰብ ያነሰ ነው” ስላቸው “ተሳስተሀል መሬት ኢትዮጵያ ውስጥ አይደለም ለዜጋው ለውጭ ሰዎች እየተሰጠ ነው ግን እኛ ሰነፎች ስለሆነ እና መስራት ስለማንወድ መሬቱን አንጠቀምበትም” አሉኝ። እኔም በመቀጠል
እርሰዎ ዕድሜዎ እየገፋ ነው፣ ከዚያ ላይ ሃይማኖት አለዎት እንደው ቢያንስ እንኳን በአይንዎት እያዩ ያሉትን ነገር እንዴት እንዳላዩ ይሆናሉ፣ ውስጠዎ ምን እያሰበ እንደሆነ እረዳዋለሁኝ እውነታውን በልበዎ ያውቁታል ነገር ግን እንደ እርሰዎ አይነት ሽማግሌ ሆኖ ያውም መረጃ በቀላሉ ከሚገኝበት አሜሪካ ተቀምጠው በዚህ ደረጃ ማሰብዎ ይገርመኛል” አልኩኝ።
ሌላ ተጋባዥ የእሳቸው ጓደኛ መጣ እና በሰላምታ ምክንያት ክርክሩ ተቋረጠ እኔም ተነስቸ ሄድኩኝ። ነገር ግን እስካሁን በህይወቴ እንደዚህ አይነት አይነ ደረቅ ሆዳም ሽማግሌ አጋጥሞኝ አያውቅም። ያውም እኮ እድሜው ወደ 70 አካባቢ ይሆናል። አገር ሲዘቅጥ እንደዚህ ነው በሞት አፋፍ ላይ ተቀምጠው እውነትን የፈሩ የሚያናድዱ ሽማግሌ ናቸው።

አዎ ማኅበረ ቅዱሳንን ተጠንቀቁ! ትልቁ ስጋት እሱ ነውና


አዲሱ ተስፋዬ
መነሻ
ይህንን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ሰንደቅ ጋዜጣ በሚያዝያ 1/2006 ዓ.ም እትሙ ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ ያወጣው ቃለ መጠይቅና ሀተታ ነው [i] :: ሶስቱም አስተያየት ሰጭዎች “ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ነው:: ስለዚህም መንግስት ሊያፈርሰው ነው ” የሚለው ወቅታዊ ዜና ምንጩ ከየት እንደሆነ ግልጽ እንዳልሆነ ጠቅሰዋል :: በፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አበበ ወርቁ ጉዳዩን “በሬ ወለደ ነው” ብለው ሲያጣጥሉት ፣ የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ደግሞ ” የዚህ ወሬ ምንጩ ከየት እንደሆነ አናውቅም” ሲሉ ተመሳሳይ ነገር ተናግረዋል።Mahibere Kidusan EOTC
ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው እንዴ?
በ 1955 እ. ኤ. አ የተመሰረተውና መቀመጫውን በኔዘርላድና በዩናይትድ ስቴትስ ያደረገው  Open Doors : Serving Persecuted Christians Worldwide [ii] የተሰኘው ግዙፍ ድርጅት 2013 እ. ኤ. ኣ ባወጣው World Watch List ላይ ክርስትያኖችን በማሰቃየት በ63 ነጥብ ኢትዮጵያ 15ተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝና ፣ ለዚህም ስቃይ ዋና ተዋናይ ከሆኑት አካላት አንዱ ማኅበረ ቅዱሳን እንደሆነ ጽፎ ፣ ሊስቱንም በመላው ዓለም በትኗል [iii] ። ይሄው በመላው ዓለም በድረ ገጽና በተለያዩ ኤለክትሮኒክ ሚድያዎች (hard and soft copy) የተበተነው ሪፖርት ከመስክ የመረጃ ሰራተኞቼ ፣ ከምሁራንና ከሰላዮቼ አገኘሁ ባለው መረጃ መሰረት አቶ መለስ ዜናዊን ሞት ቀደማቸው እንዲ ማኅበረ ቅዱሳንን እንክትክቱን ሊያወጡት አቅደው እንደነበረ ፣ ቀጣዩም ግዜ ማኅበረ ቅዱሳን የሚገንበት ግዜ እንደሚሆንና ይሄም ለተሐድሶዎች አስቸጋሪ ግዜ ስለሚሆን ከማኅበረ ቅዱሳንን እንዲጠበቁ እንዲህ በማለት ያትታል
“The death of Prime Minister Meles Zenawi, who sought to crush Mahibere Kidusan, the fanatical group inside EOC, is considered a big blow for the renewal movements. Zenawi was not a supporter of those movements, but his actions against Mahibere Kidusan for political survival were considered by the EOC renewal movements as helpful for less squeeze. His replacement, Haile Mariam Desalegn, does not possess the political and religious background required to confront the fanatical group. Mahibere Kidusan is currently riding high and…. In addition to this, the death of the EOC leader is a big shock for the renewal movements as he was reluctant to take action against them. “ [iv]
ይሄው ዓለማቀፋዊ “የክርስትያኖች እንባ ጠባቂ” ነኝ የሚለው ድርጅት ማኅበረ ቅዱሳን በመንግስት የደህንነት መዋቅር ውስጥ ዘልቆ እንደገባና የመንግስትን ስልጣን በመቆጣጠር በተለይ “የተሐድሶን ቡድን ” ለማጥፋት መነሳቱን በዚህ መልኩ ሪፖርቱ ላይ ገልጾታል
(MK) normally monitor the churches. The fanatic group inside the EOC (Mahibere Kidusan) has to be mentioned here. Particularly Open Door Field experts report that the group is now a growing threat for non-traditional protestant churches and renewal movements with in the EOC. The group ( MK) allegedly has an ambition to influence and control the government policies to restrict the activities of other religions. There are reports that Mahibere Kidusan has managed to infiltrate the government security and administrative apparatus. In the absence of a powerful leader and the death of a relatively moderate patriarch (late leader of EOC) the next move of the group is nervously watched.[v]
እስካሁም “ያዋጣናል ፤ ማኅበሩን ለመምታት ጥሩ መላ ነው”  ብለው ያሴሩት “ማኅበሩ አስራት ይወስዳል፣ ግብር አይከፍልም ፣ ሕንጻ ገንብቷል ወዘተ” የሚል ነበር። ማኅበሩ አስራት እንደማይወስድ ፣ ሂሳቡንም በተመሰከረላቸው የሂሳብ ባለሙያዎች ኦዲት በማስደረጉና ከግብርና መሰል ክፍተቶች የጸዳ መሆኑን በማረጋገጡና የውንጀላ ክፍተት በመጥፋቱ ሌላ ዜማ ጀምረዋል። አሁን ደሞ ክሱ “ማኅበሩ መንግስት ደህንነት መዋቅር ውስጥ ገብቶ ሊያፈርሰን ነው” የሚል ሆኗል።ይሄም እንደማያዋጣ ያወቁት እኩያን አሁን ደሞ የመጨረሻ ጥይታቸው ተቀይሯል። ማኅበሩ ፖላቲካ ውስጥ ገብቷል እና መንግስት ወዮልህ አይነት ዝባዝንኬ።
እናም  ማኅበረ ቅዱሳንን ተጠንቀቁ !
ይሄው ሪፖርት  ኦርቶዶክሳዊት ቅድስት ቤተ ክርስትያን ውስጥ ገብተው፣ ቤተ ክርስትያንን እየገዘገዙ ላሉ ራሳቸውን ተሐድሶ ብለው ለሰየሙ ውስጠ ተኩላ ወገኖቹ ያስተላለፈው ጥሪ አንድ ነው :: “አክራሪው ማኅበረ ቅዱሳንን እየበረታና እየጠነከረ ስለሄደ የሚቀጥሉት አመታት ለተሐድሶዎች እጅግ አስቸጋሪ ነውና … ማኅበረ ቅዱሳንን ነቅታችሁ ጠብቁ:: ከዚህም ስጋት የመነጨ ይመስላል ግብረ አበሮቻቸው ማኅበረ ቅዱሳንን ለማወክ ያለ የሌለ ሃይላቸውን አስተባብረው መንጫጫት ከጀመሩ ሰነባተዋል
Now, in his absence and with the government’s reduced leverage, this fanatic group (Mahibere Kidusan) appears to be taking charge. The coming months may bring difficult times for the renewal movements inside the EOC…the next move of the group is nervously watched.[vi]
ይሄ ድርጅት መንደርተኞች የፈጠሩት የሰፈር እቁብ አይደለም:: በመላው ዓለም ኔት ወርክ ያለው መሰረተ ሰፊ ድርጅት ነው:: የሚያወጣቸውንም ሪፖርቶች ሚሊዮኖች ያነቡታል:: የኢትዮጵያ “ክርስትያኖችን ዋይታ” በተመለከተ ያወጣው ጽሁፍ ግን ይገርማል:: ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ክርትስትያኖች ተገድለዋል:: ተሳደዋል:: አብያተ ክርስትያናትም ተቃጥለዋል:: ገዳማትም ተደፍረዋል:: ክርስትና ለሚገደው አካል እነዚህ ብዙ የሚያስጽፉ ነበሩ:: ይሄ ሪፖርት ግን ያተኮረው ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ነው:: የማኅበሩም ወንጀሎች ብሎ ሊነገረን የሚፈልገው አንድ ነገር ” ማኅበረ ቅዱሳንን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያንን ትምህርትና ዶግማ አፍርሰው ወደ ሌላ እምነት ድርጅት ለመቀየር የተነሱ ተሐድሶዎችን አላስቀምጥ አለ:: ለተሐድሶ እንቅስቃሴ እንቅፋት ሆነብን “ የሚል ነው:: እንግዲህ የማኅበሩ ወንጀል ይሄ ነው:: ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር የተናገሩትንም አስተያየት ጠምዝዞ ” ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ሞት ቀደማቸው እንጂ ሊያፈራርሱት ነበር” በማለት እውነቱን ሳይሆን ምኞቱን ተርኮልናል:: የሚገርመው ” ማኅበረ ቅዱሳንን በማፍስ ሂደት ጉልህ ሚና አልተጫወቱምና ተተኪው ጠቅላይ ሚኒትር አቶ ኃይለማርያምን “አቅም ያነሳቸው” እስከማለት ደፍሯል:: ፓትርያርክ ጳውሎስንም ” ተሐድሶ ላይ እጃቸውን ማንሳት የማይፈልጉ ለዘብተኛ” ሲል አሞግሷቸዋል:: እንደዚህ ድርጅት ዘገባ ቤተ ክርስትያንን ለመሰርሰር ሰርገው የገቡ መናፍቃን ሰማዕታት ሲሆኑ፣ የአባቶቼን ርስት አልሰጥህም በሚል ለቤተክርስትያን ትውፊትና እምነት መጠበቅ የሚደክመውን ማኅበረ ቅዱሳንን ደግሞ አሸባሪ ፣አክራሪ የሚል የስም ጥላሸት እንዲቀባ ተደርጓል:: እንግዲህ የማህበረ ቅዱሳን ወንጀሉ ይሄ ነው::
ማኅበረ ቅዱሳን ወሳኝ ሃይል ሆኗል
ከቅርብ ግዜ ወዲህ ማኅበረ ቅዱሳንን በአክራሪነትና በነውጠኛነት የመፈረጁ አባዜ በአካዳሚክ ጽሁፎች ላይም እየታየ ነው :: ለምሳሌ የዶክተር ጥበበ እሸቴን የዶክትሬት ማሟያ ጽሁፍ ማንሳት ይቻላል:: ዶክተር ጥበበ በ 1960ዎቹ ውስጥ በነበረው የተማሪዎች እንቅስቃሴ ተሳትፎ የበራቸው እና በኋላ ደግሞ የፕሮቴስታንቱን ዓለም በመቀላቀል በዛው ድርጅት ውስጥ የአስተዳደር ቦታ እስከመያዝ የደረሱ ሰው ናቸው:: እኚህ ሰው 2009 ላይ The Evangelical Movement in Ethiopia : Resistance and Resilience በሚል ርዕስ የጻፉትን የዶክትሬት ሟሟያ ጽሁፋቸውን አሳትመዋል[vii]:: በዚህ አወዛጋቢ መጽሐፍ ዶክተር ጥበበ ማህበረ ቅዱሳንን militant, aggressive, anti evangelical በማለት ጥላሸት በመቀባት አንባቢን የሚያደናግር አንቀጽ አስፍረዋል:: ያይጥ ምስክሯ ድንቢጥ ነው ነገሩ::
The emergence of a highly aggressive and more militant movement that arose with in the Orthodox Church under the name of Mahibere Kidusan in recent years should be seen in multidiscrusive context…     (Mahibere Kidusan) as a nationalistic and strongly anti-evangelical movement enjoying the backing of some orthodox conservative intellectuals and elements of the urban youth , the new religious strain is becoming a significant force [viii]
ዶክተር ጥበበ ለምን ዓላማና በምን መረጃ militant ( ነውጠኛ) anti evangelical (ጸረ ወንጌል) እሰከማለት እንደደረሱ ባላውቅም እሳቸውም ግን ገና በ2009 ማኅበረ ቅዱሳን significant force ሆኖዋልና አስቡበት ሲሉ አስገንዝበው ነበር:: ምንም እንኳን ዶክተር ጥበበ እሸቴ በዚህ ጥናታዊ ጽሁፋቸው ላይ በርካታ አመኔታ የሚጎድላቸው ነጥቦችን ቢያስነብቡንም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን ውስጥ፣ ቤተክርትስያኗን ወደ ሌላ እምነት ድርጅት ለመቀየር በስውር የሚሰሩ የተጠናከሩ ህቡዕ ቡድኖች እንዳሉና ተጽኗቸውም በሰንበት ትምህርት ቤቶች፣ በየማህበራቱ ፣ በየአጥቢያ ቤተክርትያንቱ እንዲሁም ገዳማቱን ሳይቀር መታየት መጀመሩን የውስጥ አዋቂ በሚመስል ሁኔታ እንዲህ በማለት ገልጸውታል::
Today, many underground movements are operating with in Ethiopian Orthodox Church, some with evangelical and others with Pentecostal convictions. ..Some of these movements exemplify attempts at religious innovation, though it is hard to plot their trajectories because of their hidden nature and complex character. Such developments are affecting wide ranging areas of the established structure of the Orthodox institutions, such as Sunday Schools, the mahibers, the monastic centers, and even the local churches in major cities. [ix]
የፕሮቴስታንቱ ዓለም ፓስተሮችም ከ34,000 የማያንሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርትያናት ውስጥ ገብተው ቤተ ክርስትያኗን ወደ ፕሮቴስታንቱ ዓለም ለመገልበጥ አባላትን እየመለመሉና ስልጠና እየሰጡ እንደሆነ በጀብዱ መልክ በአደባባይ እየተናገሩ ነው::
The evangelist is hopeful that the seeds of revival are being planted and nurtured in the estimated 34,000 Orthodox churches in Ethiopia and abroad. So far more than 600 people have successfully completed the two-week course.[x]
አልፎ ተርፎም ማኅበረ ቅዱሳንን ባይኖር የተሐድሶ እንቅስቃሴ ቤተክርትያኗን ሙሉ ለሙሉ ይቆጣጣራት እንደነበር በይፋ እየተጻፉ ነው:: ማኅበረ ቅዱሳንም ላይ ጥርሳቸውን የሚያገጫግጩት ለዚህ እኩይ ዓላማቸው እንቅፋት ስለሆነባቸው ነው ።ለዚህም ዓላማቸው ስኬት ማኅበረ ቅዱሳንን ሊያፈስርና ሊበትን የሚችል ዘርፈ ብዙ ስራ በመስራት ላይ ይገኛሉ:: ቤተ ክህነቱ ውስጥ በገንዘብ የገዟቸው ቅጥረኞቻቸው ማኅበሩን ለማፍረስ የቻሉትን ያህል ሄደዋል::
ግን ከኪሳራ ውጭ ማኅበሩ ላይ ምንም ያመጣው ጉዳት አለመኖሩ ያሳሰባቸው አካላት አሁን ደግሞ ቤተ ክህነቱ ውስጥ ሰግስገው ላስገቧቸው ቅጥረኞቻቸውና በገንዘብ ለገዟቸው ይሁዳዎች የመጨረሻ ትንቅንቅ እንዲያደርጉ እንደላኳቸው በየቀኑ የምናየው ሃቅ እየሆነ ነው::
ዝነኛው ጋዜጠኛ ተመስገን ዘውዴ የማኅበረ ቅዱሳን የመጨረሻዎቹ ቀናት በሚል ርዕስ በቅርቡ ባስነበበን ግሩም ጽሁፍ ላይም የማኅበሩ ተቃዋሚዎች ቤተ ክህነት ውስጥ አዳራሽ ተፈቅዶላቸው ማድረጋቸውንና የአቋም መግለጫ እስከማውጣት መድረሳቸውን እንዲህ ሲል ነበር ያስነበበን
ለመጽሔቱ ዝግጅት ክፍል የደረሰው በድምፅ የተቀረፀ የውይይቱ ሙሉ ክፍል እንደሚያስረዳው፣ ተሰብሳቢዎቹ ማኅበሩን በተመለከተ ያወጡት የአቋም መግለጫ÷ የማኅበሩና የዋነኛ መሥራቾችና አባላት የባንክ አካውንት፣ ቀላልና ከባድ ተሸከርካሪዎች ጨምሮ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረቶች፣ ት/ቤቶች፣ የንግድ ተቋማት፣ የአክስዮን ተቋማት፣ የንዋያተ ቅድሳት ማምረቻዎችና ማከፋፈያዎች፣ ከቀረጥ ነጻ የገቡና በመግባት ላይ ያሉ ዕቃዎች በሚመለከታቸው የመንግሥት መሥ/ቤቶች እንዲታገዱ በቅ/ሲኖዶስ አማካይነት ደብዳቤ እንዲጻፍ፤ ከምእመናን በቀጥታም ኾነ በተዘዋዋሪ የሚቀበለው ዓሥራት እየፈረጠመበት ስለኾነ እንዳይቀበል ይከልከል፤ የግቢ ጉባኤያት(የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት) እርሱ በሚቀርፀው ትምህርት እንዳይወሰዱብን በደንብ መሥራት፤ ተጠሪነቱ ከዋና ሥራ አስኪያጅነቱ ሥር ወጥቶ በሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ውስጥ አንድ ንኡስ ክፍል ይኹን የሚሉና የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡[xi]
ይሄን የአቋም መግለጫ ላይ በግልጽ እንደተቀመጠው የተሰብሳቢዎቹ አንዱና ዋና እቅድ የግቢ ጉባኤያት(የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት) እርሱ በሚቀርፀው ትምህርት እንዳይወሰዱብን በደንብ መሥራት፤የሚል ነው። ማኅበረ ቅዱሳን ለየግቢ ጉባ ኤያት ቀርጾ ያዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት እና መመርያ መጻሕፍቱ በሙሉ ይታወቃሉ። ቢጋሮቹም ፣ መጻሕፍቱም በሊቃውንቱ ታይተው የተመረመሩና የታረሙ ፍጹም ኦርቶዶክሳዊ ናቸው። እርሱ በሚቀርጸው ትምህርት እንዳይወሰዱብን ማለት ትርጉሙ ምንድነው? ይሄ እንግዲህ እየተካሄደ ያለው ቤተ ክህነት አፍንጫ ና ብብት ስር ነው።
ማኅበረ ቅዱሳን የኔ ነው ! ያንተ ነው!  ያንቺ ነው! የኛ ነው!
ምንም እንኳን ቤተ ክርስትያን ከፈተና ተለይታ ባታውቅም ቅድስት ቤተ ክርስትያናችን አሳሳቢ ፈተና ውስጥ ወድቃለች። ከአውሮፓና አሜሪካ ድረስ ሳይቀር ድርጎ የሚታሰብላቸው ሆድ አምላኪዎች የቤተ ክርስትያንን አባቶችን ክብር በማጉደፍ፣ የቤተ ክርስትያንን ትውፊትና ትምህርት በመገዝገዝ፣ ቤተ ክርስትያንን ወደ መናፍቃኑ ጎራ ለማስረከብ ሌት ተቀን እየሰሩ ይገኛሉ። በተለይም ራሳቸውን ተሐድሶ በሚል የሰየሙ ቡድኖች ቤተ ክርስትያኗን ለማፍረስ ቆርጠው ተነስተዋል። ለዚሁ እኩይ ዓላማቸው መሳካት ማኅበረ ቅዱሳን እንቅፋት ስለሆነባቸው ከምሁር እስከ ተርታው አባል ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ዘመቻ ከፍተዋል። የማኅበሩን ስም ለማጥፋት በርካታ ብሎጎች ሥራ ላይ ውለዋል። ብዙ ብር ወጥቶባቸው መጻሕፍት ታትመዋል።ህሊናቸውንና ሃይማኖታቸውን በብር በሸጡ ይሁዳ የቤተ ክህነት ሰዎችም ማኅበሩን ለመምታት ዘርፈ ብዙ ሙከራ ተደርጓል። አንዱም ማኅበሩን ለማፍረስ አቅም ባይኖረውም።አረቦቹ እንደሚተርቱት ውሾቹ ይጮሃሉ።ግመሉ ግን ይጓዛል።
እኛስ ለሃይማኖታችን የሚገደን ኦርቶክሳውያንስ ምን እያደረግን ነው? ማኅበረ ቅዱሳን የቤተክርስትያን እጅ ነው[xii]። የቤተ ክርስትያን አካል ነው።ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር የሚደረግ ትግል ሁሉ ቤተ ክርስትያንን ለመጣል የሚደረግ ሰይጣናዊ ትግል ነው። ማኅበረ ቅዱሳን ላይ የሚታወጅ ጦርነት በሙሉ ቤተ ክርትያን ላይ የተቃጣ ጥቃት ነው ።ማኀበረ ቅዱሳንንም ኢላማ ውስጥ እንዲገባ ያደረገው ዋነኛ ምክንያት፣ ይሄ ትውልድ ስለ ኦርቶክሳዊ ማንነቱ የላቀ ግንዛቤ እንዲኖረው ማስተማሩና ከቤተ ክርስትያን ጎን መቆሙ ነው ። የማኅበረ ቅዱሳን ጥንካሬ የቤተ ክርስትያን ጥንካሬ ነው። ማኅበረ ቅዱሳን ላይ የሚቀሰሩ ጣቶች በሙሉ ቤተ ክርስትያን ላይ የሚቀሰሩ ጣቶች ናቸው ።ስለዚህ ማኅበሩ ላይ የሚደረጉ ትንኮሳዎች ቤተ ክርስትያን ላይ እይሚደረጉ ትንኮሳዎች ናቸውና እያንዳንዳችን ኦርቶዶክሳውያን ቆመን ማሰብ አለብን አለብን።
ማኅበረ ቅዱሳን ይፈርሳል እንዴ ?
“ማኅበረ ቅዱሳን ይፈርሳል” ብለው ለሚቃዡ ሰዎችም እውነታውን አውቀውት ከወዲሁ እርማቸውን እንዲያወጡ ትንሽ ልበል። ዛሬ እኮ የትኛውም ዓለም ብትሄድ የማኅበረ ቅዱሳን ሴል (Cell)  የሌለበት ክፍለ ዓለም የለም።ኢትዮጵያ ውስጥ እያንዳንዱ ቀበሌ ድረስ ” እምቢ ለቤተክርስትያኔ” የሚሉ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት አሉልህ።ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ እያንዳንዱ አብያተ ክርስትያናት ውስጥ ለቤተ ክርስትያን ሁለንተናዊ እድገት ነቅተው የሚሰሩ የማኅበሩ አባላት አሉ ። የማኅበሩ መመርያ እንደሚያዘው እያንዳንዱ የማኅበር አባል የሰንበት ትምህርት ቤት አባል ነው። የትኛውም ቤተ ክርስትያን ሰበካ ጉባኤ ውስጥ ቤ ክርስትያንን ባላቸው አቅም ለማገልገል ቁርጥ አቋም ያላቸው የማኅበሩ አባላት አሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ የትኛውም የመንግስትም ሆነ የግል ድርጅት ውስጥ የማኅበሩ አባል የሌለበት የለም ። እያንዳንዱ መስሪያ ቤት ያለ ተቀጣሪ የማኅበረ ቅዱሳን ተጽዕኖና አሻራ የሌለበት የለም ። የማኅበሩ ቋሚ አባል ባይሆን እንኳን የማኅበሩ ግን ሙሉ ደጋፊ ነው ።ወይም በዘመኑ ቋንቋ ስትፍቀው ማኅበረ ቅዱሳናዊ ነውማኅበረ ቅዱሳን በየቀኑ ለቤተክርትስያንን ጉዳይ የሚንገበገብ ፣  የሚያስብ ትውልድ ፈጥሯል።ይህ ትውልድ ማኅበረ ቅዱሳናዊ ነው። ቢመረንም ፤ቢዋጠንም።
ከኢትዮጵያም ውጭ የማኅበሩ ቅርንጫፍ የሌለበት ቦታ የለም። በተለይ በሰሜን አሜሪካ እና አውሮፓ ። ዛሬ ዛሬ በሰሜን አሜሪካና በአውሮፓ የሚደረጉ የማኅበሩ ጠቅላላ ጉባኤያት ከሀገር ውስጡ የማይተናነሱ እየሆኑ ነው። በዓረቡ ዓለምና በዕሥያ ያለው የማኅበሩ እድገትም ቀላል አይደለም። የትኛውም ክፍለ ዓለም ላይ የቤተ ክርስትያን ጉዳይ የሚገደው በቤተ ክርስትያን ጉዳይ ዝም የማይል የማኅበረ ቅዱሳን ሕዋስ አለ። ባጭሩ ማኅበሩ global ሆኗል። ወይ ደግሞ ነፋስ ሆኗል።አትይዘው አትጨብጠው። ነፋስ የማይነፍስበት ቦታ እንደሌለ ሁሉ ማኅበሩ የሌለበት ቦታ የለም።ማን ነበር ማኅበረ ቅዱሳን የሃሳብ መስመር ( Imaginary line) ሆኗል ያለው። ማኅበረ ቅዱሳንን ልዝጋው ብሎ የሚያስብ አላዊ እንኳን ቢመጣ አዲስ አበባና በየዞኑ ያለውን ጽፈት ቤት ሊዘጋ ይችል ይሆናል።ማኅበረ ቅዱሳንን ማጥፋት አይችልም::  ዋናው የማኅበሩ ሥራ የሚሰራው በያንዳንዷ ደብር ፣ በየሰበካ ጉባኤው ፣ በየሰንበት ትቤቱ ፣ በየ አባላቱ ቤት ስለሆነ ማኅበረ ቅዱሳን ላይ የሚያመጣው ለውጥ insignificant ነው። ሰሜን አሜሪካ ያለው ማዕከል ብቻውን አዲስ አበባ ያለው ማስተባበርያ የሚሰራውን ሥራ የምስራት አቅም አለው። እድሜ ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዛሬ አሜሪካ ሆነህ በያንዳንዱ ቀበሌ ፣በያንዳንዱ አጥቢያ ያለውን አባል ለቤተ ክርስትያን ሥራ ማስተባበር ከባድ አይደለም። It is a click or one call away. ማኅበሩ በአንድ የጸሎት ቋንቋ የሚናገሩ ፣ በአንድ የእምነት ልብ የሚመሩ ፤ እንደ አንድ ቃል ተናገሪ እንደ አንድ ልብ መስካሪ የሆኑ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኦርቶክሳውያን ስብስብ ነውና እንዲህ በቀላሉ እንደ አንቧይ ካብ አትንደውም።ብትሰረስረውም መሰረቱ ጠንካራ አለት ነውና አታፈርሰውም። ከሁሉም በላይ የማኅበሩ ጠባቂ እመብርሃን ናትና ገና ይሄ ማኅበር ያድጋል። ይሰፋል።
ማስገንዘቢያ
ይህ ጽሁፍ የኔ የራሴ የግል ምልከታዬ እንጂ ሌላ ማንንም አይወክልም:: አስተያየት ሊሰጡኝ ከወደዱ በዚህ ኢ ሜይል ይላኩልኝ
redawube@gmail.com

[i] http://www.sendeknewspaper.com/images/Sendek-Pics/448/448.pdf
[iii] http://www.opendoors.no/vedlegg/1988472/WWL2013-FullReport-en
[v]  ibid
[vi] Ibid
[vii]  Eshete,Tibebe  The Evangelical Movement in Ethiopia : Resistance and Resilience 2009 Bayor University press
[viii]  Ibid ( page 313)
[ix] Ibid ( page 61)
[x] http://www.charismamag.com/blogs/189-j15/features/africa/530-revival-and-persecution-in-ethiopia
[xi] ፋክት፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፴፱፤ መጋቢት ፳፻፮ ዓ.ም.

አባይን ለመንከባከብ የጎሰኛነት አገዛዝ በዲሞክራሳዊ አገዛዝ መተካት አለበት (ዶ/ር አክሎግ ቢራራ)


April 12, 2014
አክሎግ ቢራራ (ዶ/ር)

Click here for PDF

Ethiopia's dam on Abbay/Nile river
ክፍል አንድ
“ለምንወደው ለዛሬው ሕዝባችንም ሆነ፤ ከዘመን ወደ ዘመን ለሚከተለው ትውልድም ጭምር፤ የዓባይን የውሃ ሃብት ለሕይወቱ ደህንነትና ለፍላጎቱ ማርኪያ እንዲውል ማድረግ፤ ኢትዮጵያ ከፍ ያለ ግምት የምትሰጠውና በቅድሚያ የሚያሳስባት ጉዳይ ነው።
አምላካችን ያበረከተላትን ይህን ሃብቷን ለሕዝባቸው ህይወትና ደህንነት በማዋል እንዲጠቀሙበት ከጎረቤት ወዳጅ አገሮች ጋር በለጋስነት በጋራ ለመካፈል ዝግጁ ብንሆንም፤ ይህን የውሃ ንብረቷን በቁጥር እየጨመረ ለሚሄደው ሕዝቧና በማደግ ላይ ላለው ኢኮኖሚ ጥቅም እንዲውል ማድረግ የኢትዮጵያ ተቀዳሚና የተቀደሰ ግዴታዋ ነው።”
ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፤ ጥቅምት 1957 ዓም
“ወንዞችን በጋራ ፈሰስ የሚጋሩ አገሮች ሁሉ ውሃውን አግባብ፤ ፍትሃዊ፤ ለሁሉም ጠቃሚ በሆነ መንገድ የመጠቀም መብትና ግዴታ አለባቸው። ይህን ሲያደርጉ በተቻለ መጠን ለጋራ ጥቅም በመመካከርና አንዱ ሌላውን ሳይጎዳ፤ ውሃውንና አካባቢውን ዘላቂነት ባለው መንገድ በመንከባከብ ይሆናል።”
Convention on the Law of the Non-navigational Uses of International Watercourses, UN General Assembly resolution 43/52 of December 1994.
አባይን የመጠቀም ጥያቄ አጼ ኃይለ ሥላሴ ከላይ ከተናገሩት በበለጠ ደረጃ ዛሬ ወሳኝ ሆኗል። ባሁኑ ወቅት በዓለም አከራካሪ፤ አሳሳቢና ጦርነትን ፈጣሪ ከሆኑ አንኳር ጉዳዮች አንዱ ውሃንና ወንዞችን የመጠቀም መብት ነው። ከፍተኛ ሽሚያና ሴራ አለ። ጉዳዩን ያጠኑ ግለሰቦችና ተቋሞች እንዲህ ይላሉ። “የዛሬ አስራ ስድስት ዓመት (2030) የዓለም ሕዝብ ብዛት እየጨመረ፤ ፍላጎት እያደገ፤ ከተሜነትና ልማት እየተስፋፋ ስለሚሄድ፤ አራት ቢሊዮን ሕዝብ የውሓ እጥረት ያጋጥመዋል። ከዚህ ውስጥ ብዙ መቶ ሚሊዮን የሚገመተው በአፍሪካ ቀንድ፤ በሰሜን አፍሪካ፤ በሳሄል አገሮች ይገኛል።” ከሳሃራ በታች የሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ሕዝብ ዛሬ አንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ሲገመት፤ በተባበሩት መንግሥታት ስሌት፤ በ2050 ይህ ቁጥር ወደ ሁለት ነጥብ አራት ቢሊዮን ከፍ ይላል። የውሃ ተፋሰስ ተፎካካሪ ወደ ሆኑት ግብጽና ኢትዮጵያ ብናተኩር የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር ዛሬ ካለው እጥፍ ይሆንና ቢያንስ መቶ ሰማንያ አምስት ሚሊዮን ይደርሳል። ቀድሞ የተባበሩት መንግሥታት ከገመተው ዝቅ ብሏል ማለት ነው። በአንፃሩ፤ የግብፅ ሕዝብ ብዛት መቶ ሃያ አምስት ሚሊዮን ይሆናል። ኢትዮጵያ በሕዝብ ብዛት ግብፅን በስድሳ ሚሊዮን ሕዝብ ትበልጣለች ማለት ነው። ሆኖም፤ ከግብፅ ጋር ለመወዳደር፤ የኢትዮጵያን ብሄራዊ አንድነት፤ የመላዊ ሕዝቧን ኢትዮጵያውይነት መቀበል ወሳኝ ነው። በተጨማሪ ሁሉም ኢትዮጵውያን የሚሳተፉበትና ክፍጹም ድህነት የሚላቀቁበትን ዘላቂና ፍትሃዊ ኢኮኖሚ መመስረት ያስፈልጋ። ማንኛውም አገር በአፈና፤ በጎሰኛንትና በስደት በተበከለ አገዛዝ ጠንካራ ሕብረተሰብና ጥንካራ አገር ለመመስረት አይችልም። ኢትዮጵያ ታሪክ ያላት፤ መነሻና መድረሻ ያላት፤ ታላቅ ለመሆን የምትችል፤ የብዙ ብሄር/ብሄረሰብ ደሴት መሆኗን ተቀብለን ከልዩነቶች በላይ የሚገልጻት ዋናው እሴት ኢትዮጵያ አንድ አገር መሆኗን መቀበል፤ ዜግነት ኢትዮጵያዊ እንጅ ጎሳዊ አለመሆኑን በማንኛውም ግንኙነት ማስተጋባት የወቅቱ ጥያቄዎች ናቸው እላለሁ። ይኼን የተቀደሰ መርህ እንደዋዛ ካየነው፤ ኢትዮጵያን ለሌሎች (ጥቂት ተጠቃሚዎችና ለፈረንጆች) እንደምናስተላልፋት በአይናችን እያየን ነው። ዛሬ ኢትዮጵያውያን በጎሳ ስለተከፋፈሉ፤ መብታቸውና ነጻነታቸው ስለታፈነ በሃገራቸው የተፈጥሮ ሃብት፤ በቤታቸው፤ በመሬታቸው፤ ብህይዎታቸ፤ በሃብታቸው፤ ለማዘዝ አይችሉም። ለመጀመሪያ ጊዜ ፈረንጆች ከኢትዮጵያዊን የበለጠ ተሰሚነትና መብት አላቸው። አስደናቂውና የሚያኮራው የመሰረታዊ ለውጥ ምልክት ወጣቱ ትውልድ “መብት ይጠየቃል፤ አይለመንም፤ ፍርሃት አልወለደንም፤ በህሊናየ አታዝም” እያለ በደሴ፤ በሃህር ዳር፤ በጎንደር፤ በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች የሚያሰማው ድምፅ ነው። ሌሎቻችን እጆቻችን አጣጥፈን የምንመለከት ጊዜ ያለፈ ይመስለኛል። [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

The Disgraceful State of Higher Education in Ethiopia: How TPLF/EPRDF Killed Higher Learning


by Alem Mamo
TPLF/EPRDF’s major bragging source over the last number of years has been its ‘achievements’ in the education sector, particularly in university education. The ruling group constantly brandishes its statics about the ‘expansion’ of higher learning in Ethiopia. What is not included in the fraudulent statistics is the obliteration of quality and depth of teaching and learning in these so-called ‘universities.’  As we have seen in most of the TPLF/EPRDF failed and corrupt policies the establishment of these so called ‘universities’ is nothing more than a construction contract to its own business conglomerates and university administration appointment to its loyal cadres.
Addis Ababa University (formerly Haile Selassie I University) is a university in Ethiopia.
Addis Ababa University
A university is more than a building. A university in its true form requires several contextual, philosophical, and logistical grounds to fully carry out its historical and traditional role as a place of higher learning.
The higher learning landscape in Ethiopia under TPLF/EPRDF suffers from four acute problems. First, there is a chronic lack of academic freedom and autonomy, which is an essential component for any university to discharge its responsibilities. Second, there is an absence of qualified and competent instructor and mentors. Third is the almost non-existent nature of 21st century tools, such Internet communication, and finally there is the occupation and control of higher learning institutions by uneducated TPLF/EPRDF cadres. These key factors, coupled with the overall social, economic, and political problems, continue to plague the country’s higher learning landscape equating to a level similar to the mass wedding ceremonies orchestrated by a religious group lead by a self-proclaimed messiah, such as Reverend Sun Myung Moon[1]
In fact the assault on higher learning began in 1993 when TPLF/EPRDF fired 42 seasoned academics from Addis Ababa University and replaced them with its loyal cadres.[2] Ever since then the ruling group has continued to destroy higher learning under the guise of ‘expanding’ education. Universities and educational institutions in general are places where students are taught how to think, instead of what to think. Furthermore, universities are places in which curious learners are provided with the tools and the support to conduct research that has practical values in the social, economic, and political life of the society. Instead, the regime has built political re-education camps[3] where political cadres have the final word on the academic, social, and administrative life of an institution.
Indeed merit and qualification has never been TPLF/EPRDF’s s strong suit. Starting from senior cabinet positions to all the way to the lowest level of the administrative body they have appointed their cadres to run the country, and, quite frankly, the regime is not going to treat universities in any different way.
‘Massification’ of higher learning in Ethiopia, preferring quantity of graduates to quality, has reached a critical stage, and it is becoming very problematic to use the term ‘university’ to describe these diploma mills. In TPLF/EPRDF’s Ethiopia every institution is forced to be subordinate to the twisted ideology of the regime. The first and foremost pillar of a university anywhere in the world is autonomy and academic freedom. These two elements are the oxygen of a free learning and teaching environment. Contrary to this the ruling group maintains full control over these institutions depriving them the oxygen of freedom they desperately need to breath and function freely.
Maintaining its well-established destructive role TPLF/EPRDF is moulding higher learning institutions in its own image, and the image is not pretty. Infused with ugly and hate filled propaganda, the image of these so-called universities looks like this: (a) all of these institutions must maintain perceived or real ethnic polarization and tension;
(b) These institution must serve to promote TPLF/EPRDF’s divisive agenda; (c) all ‘university’ senior management, including presidents, must be members of the TPLF or TPLF manufactured political organizations; (d) critical thinking and questioning the prevailing orthodoxy equals terrorism; and (e) university campus informants are part and parcel of the security and surveillance structure of the regime.
The overall decline of the quality of higher learning in Ethiopia is evident in the African and world university rankings.  Currently, according to the African Economist University Rankings, only one university out of 35 so-called universities in Ethiopia appears on the ranking chart.[4] The rest are nowhere to be seen on any of university rankings.
We have come to be accustomed with TPLF/EPRDF lies, such us tyranny is democracy, repression is freedom, concentration of wealth in the hands of its inner circle is economic growth and development. The most tragic one is their political re-education camp ‘universities’.
Finally, one cannot understand the sad state of higher education in Ethiopia without understanding TPLF/EPRDF’s distractive political and economic agenda. Ultimately, these daunting challenges are intertwined and interconnected, therefore they only can find a solution when the fundamentals of the governance parameters are addressed.  Freedom, justice, and democratic accountability are the only solution. In the meantime, those who are enrolled in these institutions should continue to demand better quality as part of their struggle for a free, just, and democratic society.
The writer could be reached at alem6711@gmail.com

“Yegna Band” under fire for receiving £4m UK aid


The popular UK media “Mail Online” attracted massive UK citizens followed by up roars for its recent reporting of £3.8m UK Department for International Development aid to “Yegna Band”

How you pay £4m to fund the Ethiopian Spice Girls: New aid storm over project that’s even ridiculed in African country

  • Yegna are a five-strong group that aim to empower women
  • Is part of a £30million scheme called Girl Hub that also operates in Nigeria
  • Have their own radio show but it only reaches half the population
  • Group given £3.8m by the UK Department for International Development
UK taxpayers have picked up a £4million bill to fund Ethiopia’s own Spice Girls.
Yegna, a five-strong group, have launched a radio show and released a string of videos that aim to empower women in the African country.
But even Ethiopian critics of the project say the money is being wasted because the show reaches only a quarter of the population.
Like the original Spice Girls, the band members each have a nickname. Teref Kassahun, 26, plays the spoiled brat, Lemlem Hailemicheal, 26, a tomboy known as the defender, Zebiba Girma, 22, the mysterious character, Eyerusalem Kelemework, 27, is the genius and Rahel Getu, 22, the dependable one.
Lyrics to one of their songs, This House, included: ‘Women are sisters, women are mothers, women are wives. Let’s respect them. Tell that guy to respect girls and we will respect him.’
Yegna is behind a twice-weekly radio drama and talk show for adolescent girls. They have been given £3.8million by the Department for International Development and £800,000 by the Nike Foundation.
A DfID spokesman said girls in Ethiopia faced challenges such as forced marriage, violence, teen pregnancy and dropping out of school.
‘Yegna addresses these issues using role models to champion the potential of Ethiopian girls in ways which are accessible and relevant,’ said the spokesman. But the Yegna radio broadcasts on Sheger FM in Addis Ababa and on other radio stations in the Amhara region, reach only 20million of the country’s 80million people.
Last year the Girl Hub project was condemned by the Independent Commission for Aid Impact. Its report warned of serious deficiencies in governance and told of an unacceptable lack of child protection policies. Girl Hub has also been accused of ‘poor budgeting and financial monitoring’.
Matthew Sinclair of the TaxPayers’ Alliance said: ‘Taxpayers are fed up of their hard-earned cash being spent on projects that don’t deliver meaningful aid to recipients.
‘It’s time to reassess DfID spending and focus money on things like disaster relief, so that taxpayers and recipients get a good deal.’
Tory MP Philip Davies described Girl Hub as ‘a complete waste of money’. ‘It can only reinforce the view that DfID have got far too much money,’ he said. ‘They have got so much that they are struggling to find ways to spend it and you end up with projects like this.’
A source told the Mail that Yegna had proved lucrative for the five young women: ‘They came from poor backgrounds, three of them worked for a theatre company. Now they are rich in comparison.’ Overseers of the three-year project allegedly spent £16,000 of the funding on having a famous singing star in one of the girls’ music videos. DfID has denied this claim.
The managing director of an Ethiopian media company working to empower women said he could run his project for 154 years at the same cost as the Yegna initiative. Moges Tafesse, from Synergy Habesha, said: ‘To me, the project does seem very expensive.’
Mr Tafesse said his show, Finote Heawan, will be broadcast on FM97 – a government-owned radio station the entire country can listen to.
A media commentator, who did not want to be named, said: ‘Putting on the radio show is nonsense.
This kind of empowering women has to be aimed at the people in the countryside – it is those girls who are abandoned.
Those girls who are in the city with access to the show have got their education and know about their rights.’
Lemlem told the Mail: ‘It is definitely worth the cost – it is an amazing issue. It means a lot to Ethiopia and we are using the money effectively. It is a big change.
‘We are like the Spice Girls except our music is not just for entertaining – it is educational.’