በእለቱ የእስልምና እና የክርስትና መሪዎች በየተራ ንግግር ያሰሙ ሲሆን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በእስልምናና በኦርቶዶክ ቤ/ክ ሃይማኖቶች ላይ እያደረገ ያለውን ጣልቃ ገብነት በማውገዝ ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ አሳስበዋል። ከዚህ በተጨማሪም የተቋውሞ ሰልፈኞቹ የጸረአሸባሪነት ህግ ከለላ በማድረግ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች፡የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና ደጋፊዎቻቸውን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈታ በአንድ ድምጽ ጠይቀዋል።
በእለቱ የስዊድሽ ሶሻል ዴሞክራትስ ፓርቲ ተወካይ ባደረጉት ንግግር ዛሬ በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እንዲሰፍንና የዜጎች የመናገር የመጻፍ እና የሃይማኖት ነጻነት እንዲሰፍን ከሚታገሉ ወገኖች ጋር ያላቸውን የትግል አጋርነት ለማሳየት መሆኑን ጠቅሰው የኢትዮጵያ መንግስት በዜጎቹ ላይ እያደረገ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች አፈናና እስር በማውገዝ በሃገሪቱ በሚገኙ የተለያዩ እስርቤቶች ያጎራቸውን በሺዎች የሚቆጠሩ የህሊና እስረኞች እንዲፈታ ጠይቀዋል። ከዚህ በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት በጸረ ሽብር ክስ ተወንጅለው በእስር ላይ በመንገላታት ላይ የሚገኙትን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችና ሌሎች የህሊና እስርኞች የሚዘክር ግጥም ቀርቧል። ሰላማዊ ሰልፈኞቹ የኢትዮጵያን ሰንደቅዓላማ እና ድምጻችን ይሰማ የሚለውንና ሌሎች የተለያዩ መፈክሮችን በማሰማት መንግስት በእምነት ነጻነት ላይ እያደረገ ያለውን ጣልቃ ገብነት በአስቸኳይ እንዲያቆም በተለይም ጅሃዳዊ ሃረካት የተባለውንና በሰላማዊ ዜጎች መካከል ቅራኔ እንዲፈጠር ሆን ተብሎ በመንግስት ሃላፊዎች ተዘጋጅቶ የቀረበውንና በኢቲቪ የተላለፈውን ፊልም አጥብቀው እንደሚቃወሙ ገልጸዋል። ቴዎድሮስ አረጋ መጋቢት፳፻፭ ስቶክሆልም ስዊድን
No comments:
Post a Comment