Friday, March 15, 2013

ትግላችን ይቀጥላል

            ድምፃችን ይሰማ
             አንዋር መስጊድ ነገ ጭር ይላል!
ትግላችን ይቀጥላልየድምጻችን ይሰማ ሕዝባዊ መነሳሳትና ተቃውሞ በግፍ ለእስር በተዳረጉት መሪዎቹ ቃል ኪዳን ታስሮ የስኬት ጉዞውን ቀጥሏል፡፡ ትግላችን ድንበሮችን አቋርጦ ክልሎችን ከክልሎች፣ ከተሞችን ከከተሞች እንዲሁም ሕዝቦችን ከሕዝቦች ከምንም በላይ ልቦችን ከልቦች ጋር አስተሳስሮ እየነጎደ ነው፡፡ አልሀምዱሊላህ! ይህን ክብር እና ስኬት ያሳየን አላህ (ሱ.ወ) ምስጋና ይገባው፡፡ በዚህ ሳምንት በሚደረጉ ሁሉን አይነት ተቃውሞዎች የምናንጸባርቀዉ ዋነኛ ሀሳብም ትግላችን እያደገ፣ መስዋእትነታችንም እያየለ ግን ደግሞ ጥንካሬያችንና ስኬታችን በአስተማማኝ መሰረት ላይ እየተገነባ መሆኑን ማሳየት እና ትግላችንም እንደሚቀጥል ማስገንዘብ ነው፡፡
በዚህም መሰረት በአዲስ አበባ የሚኖረው ተቃውሞ ወደ ታላቁ አንዋር መስጊድ ባለመሄድና መስጊዱን ጭር በማድረግ የሚገለጽ ነው፡፡ ዘወትር ለተቃውሞም ሆነ ለጁምአ ሰላት የምንሄድ ሁሉ የነገውን የጁምአ ሰላት በሌሎች አማራጭ መስጊዶች በመስገድ ብቻ የሚገለጽ ይሆናል፡፡
ተቃውሞአችን በድምጽ በሚደረግባቸው ከተሞች የሚኖረው ጠንከር ያለ ተቃውሞ ዝርዝር የአፈጻጸም መርሐ ግብሩ ይህን ይመስላል፡፡
ኢማሙ የጁመዓ ሰላት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ በአንድ ከፍ ያለ ድምፅ:-
• የአላህን ታላቅነት ለማሳየት ለሦስት ደቂቃ ‹‹አላሁ አክበር!››
• የተቃውሞችንን መሪ ቃል እና የተቃውሞችንን መንፈስ ለመግለጽ ለሦስት ደቂቃ ‹‹ድምፃችን… ይሰማ!››
• መንግስተ የመብት ጥያቄ ሂደታችንን ከሽብር ተግባር ጋር በማያያዝ ሕዝቡን አሸባሪ ለማለት ደፍሯል እኛ ግን ሰላም መርሁ የሆነው የኢስላም ተከታዮች መሆናችንን ለማስገንዘብ ለሦስት ደቂቃ ‹‹ኢስላም… ሠላም!››
• መሪዎቻችንን ጨምሮ ያለጥፋታቸው ሙስሊም በመሆናቸው ብቻ ታስረው በመላዋ አገሪቱ ወህኒ ቤት የሚገኙ ሁሉ እንዲፈቱ ለሦስት ደቂቃ ‹‹የታሰሩት….ይፈቱ!››
• ብሄራዊ ውሸታቸውን በየእለቱ እየጋቱን ላሉት መንግስት ብዙሀን መገነኛዎች ከሀሰተኛ ዘገባዎች እንዲቆጠቡ ለመንገር ለሦስት ደቂቃ ‹‹ውሸት …. በቃን!››
• ጥያቄዎቻችን በማያዳግም መልኩ እስካልተመለሱ ድረስ ትግላችን እንደማይቋረጥ እና ሕዝባዊ መሰረት ላይ የተገነባ መሆኑን ለማመልከት ለሦስት ደቂቃ ‹‹ትግላችን….ይቀጥላል!››
• በመጨረሻም ሁላችንም ባለንበት ለሦስት ደቂቃ ወደ አላህ ሱብሐነሁ ወተዓላ የመጣብንን በላእ እንዲያነሳልን ዱዓ በማድረግ የዕለቱ ተቃውሞ ይጠናቀቃል-ኢንሻ አላህ፡፡
ይህን በቁጥር በርካታ በሆኑ ከተሞች የሚደረገው ተቃውሞ ላይ ሁሉም በተጠቀሱት ከተሞች ላይ የሚገኝ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ሁሉ በነቂስ ወጥቶ እንደሚሳተፍበት ጥርጥር የለንም፡፡ ይህ እለት ዳግም አንድነታችንን፣ ጥንካሬያችንና ለመሪዎቻችን ያለንን ታማኝነት የምናሳይበት ነው፡፡
አላሁ አክበር!

No comments:

Post a Comment