Saturday, March 22, 2014

የዋሸው ማን ነው? – ለመምህር ግርማ ከቤተክርስቲያን የተጻፉላቸው 14 ደብዳቤዎችና ምስክር ወረቀቶች እጃችን ገቡ




“ለምንድ ነው የምትገፉኝ?” – መምህር ግርማ
(ዘ-ሐበሻ) ዘ-ሐበሻ የመምህር ግርማ ወንድሙን ጉዳይ ተከታትላ በመዘግብ ላይ ትገኛለች። አንባቢዎቻችን እውነታውን እስኪጨብጡ ድረስ ዘገባዎችን ማቅረቧ የሚቀጥል ይሆናል። በትናንትናው የዜና እወጃችን ቤተክርቲያን በአቡነ ገሪማ አማካኝነት የተጻፈን ደብዳቤ በመጥቀስ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን “መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ” በሚል ስያሜ የተበተነው ደብዳቤ ሕገ ወጥ በመሆኑ የሚመለከተው ሁሉ ይህን ግንዛቤ እንዲወስድ አሳሰበች፡፡” በሚል የተጻፈውን ደብዳቤዎች አቅርበን ነበር።
ቤተክርስቲያን መምህር ግርማን በፎርጂድ ደብዳቤ ማሰራጨት የሚወነጅል ደብዳቤ ቢወጣም ዘ-ሐበሻ ለመምህር ግርማ ከቤተክርስቲያን የተጻፉ 14 ደብዳቤዎችና የምስክር ወረቀቶች ደርሰዋታል። ይህም ፎርጂድ ደብዳቤ ጽፈዋል በሚል የወነጀላቸውን አካል ወይም መምህር ግርማ ህጋዊ ደብዳቤ ተሰጥቶኛል ብለው ያሰራጩትን ደብዳቤ ለተመለከተ ማን ነው የዋሸው ለሚለው ጥያቄ ምላሽ ሊሆን ይችላል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ። ያንብቡ ና የዋሸው ማን ነው ለሚለው ምላሽ ይስጡ።
“አንድ ሙዚቀኛ የሙዚቃ ትምህርት ቤት አንድ ሰርተፊኬት ብቻ ካለው ተቀባይነትና የታዋቂነት ክብር ይሰጠዋል፤ የሥራ መስኩም ይወደዳል፣ ይፈቀራል። ማንም የሚቃወመውም የለም፤ በሁሉም ዘርፍ ተፈላጊ ተወዳጅ ተሸላሚ ነው። በክፉ መንፈስ ከተጠቁት ጋር ለምውለው ለእኔ ግን የተገላቢጦሽ ነው። በሺህ የሚቆጠሩ የጥሪ አገልግሎትና የምስጋና ሰርተፊኬት አለኝ። ዛሬ ይህ ሁሉ ውሸት ሆኖ የመንደር አስማተኛ፤ የሱዳን ጠንቋይና የማይታወቅ አጭበራባሪ መለያ ስሜ ሆነ፤ ግን ለምን? ከጥቁር ፀጉር እስከ ነጭ ሽበት ያገለገልኩባት ቤተክርስቲያን ትምህርትና ፈውስ የሚፈልገው ሕዝብ ሲበዛ የፈውሱ ሂደት ከሃገር ውስጥና ከውጭ ዓለም ነጮችን ጨምሮ ሲከናወን የቤተክርስቲያን የወር ባጀት እና የዓመት ገቢ በእጥፍ ሲያድግ ለአባቶች እና በየአገረ ስበከቱ ላሉ አባቶች ሕዝቡ የፈውስና የትምህርት ፍላጎት ጥያቄ ሲበዛ ለምንድ ነው አስማተኛና ጠንቋይ የተባልኩት? ከነ ሙሉ መረጃው በሚቀጥለው… “አጥርቶም አየ… ከሩቅም ሳይቀር ሁሉን ተመለከተ” (ማር.23) መቆሚያና ማብቂያ የለውም ፈተና… ግን ለምን? ለምንድን ነው የምትገፉኝ?”
- መልአከ መንከራት ግርማ ወንድሙ
ደብዳቤዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

No comments:

Post a Comment