Wednesday, April 9, 2014

ሰበር ዜና፡- ወ/ሮ አስቴር ማሞ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ ተሾሙ

ሪፖርተር  ጋዜጣ

ወ/ሮ አስቴር ማሞ
ወ/ሮ አስቴር ማሞ
በቅርብ የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ በኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት በተመረጡት አቶ ሙክታር ከድር ምትክ፣ ወ/ሮ አስቴር ማሞ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደርና ሪፎርም ክላስተር አስተባባሪ ሆነው ተሾሙ፡፡
ማክሰኞ መጋቢት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. በፓርላማ ሹመቱ የፀደቀላቸው ወ/ሮ አስቴር በተጨማሪ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አቅራቢነት በፓርላማው ሹመታቸው የፀደቀው ወ/ሮ አስቴር የመጀመርያዋ ከፍተኛ ተሿሚ ናቸው፡፡
‹‹ሴት ተሿሚ ለዚህ ከፍተኛ ሹመት በማቅረቤ ከፍተኛ ደስታ ይሰማኛል፤›› ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለፓርላማው አባላት ስሜታቸውን ገልጸዋል፡፡ ወ/ሮ አስቴር ሹመታቸው ከፀደቀ በኋላ ቃለ መሐላ ፈጽመዋል፡፡
በተለያዩ ከፍተኛ የፓርቲና የመንግሥት ኃላፊነቶች ላይ የቆዩት ወ/ሮ አስቴር፣ በፓርላማው የመንግሥት ተጠሪ የነበሩ ሲሆን እስከ ሹመታቸው ድረስ በምክትል ፕሬዝዳነት ማዕረግ የ ኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አማካሪ ነበሩ፡፡

No comments:

Post a Comment