Thursday, January 2, 2014

የመቀለ ወጣቶች ከህወሓት መሪዎች ጋር ተጋጩ


የመቀሌ ከተማ (ፎቶ ፋይል)

አብርሃ ደስታ በፌስቡክ ገጹ እንደዘገበው፦
ዛሬ ሐሙስ ታህሳስ 24, 2006 ዓም በኮብልስቶን ስራ የተሰማሩና (ለመሰማራት በማህበራት የተደራጁየመቀለ ወጣቶች በመቀለ ከተማማዘጋጃቤት አዳራሽ ተሰብስበው ነበር። የተሰበሰቡበት ምክንያት በጨረታ የተወዳደሩበት የኮብልስቶን ግንባታ መሰረዙ ሊነገራቸው ተብሎነበር።
ባለፈው ዓመት በኮብልስቶን ስራ የተሰማሩ ወጣቶች አብዛኞቹ መክሰራቸው ይታወሳል። የከሰሩበት ምክንያት ደግሞ ለኮብልስቶን ስራተብሎ ከዓለም ባንክ የተከኘ ገንዘብ በሐላፊዎች አለ አግባብ መመዝበሩ ነበር። የኮብልስቶን ገንዘብ የሰረቁ ባለስልጣናት መታሰራቸውይታወሳል።
አሁን በወጣው ጨረታ መሰረት ግን ለስርቅ የሚሆን የሚተርፍ የኮብልስቶን ገንዘብ አይኖርም። በዚህ ምክንያት የህወሓት መሪዎችጨረታው ለመሰረዝና ሌላ አዲስ ጨረታ ለመክፈት ወስነዋል። ወጣቶቹም የህወሓት መሪዎች የወሰዱት እርምጃ ክፉኛ ተቃውሞውታል።ወጣቶቹ ለጠየቁት ጥያቄ ተገቢ መልስ ባለመግኘታቸው ስብሰባው ረግጠው ወጥተዋል። የአደራሹ በር በመዝጋት ስብሰባው ረግጠውእንዳይወጡ ጥረት የተደረገ ቢሆንም አልተሳካም።
ወጣቶቹ ነገ ጠዋት (ዓርብወደ ክልል ቢሮ ተሰባስበው ይሄዳሉ። የክልል መንግስት መፍትሔ ካልሰጣቸው የተቃውሞ ሰልፍ እስከማድረግይደርሳሉ።
ይህ የኮብልስቶን ጉዳይ ባብዛኞቹ የትግራይ ክልል ከተሞች ትልቅ አጀንዳ ሁኗል።

No comments:

Post a Comment