Tuesday, December 17, 2013

በኖርዌ በርገን ከተማ ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ ተካሔደ


በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖር በርገን ቅርንጫፍ በዲሴምበር 14, 2013 ዓም ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው ህዝባዊ ስብሰባ በተጋባዥ እንግዶች ዶ/ር ታደሰ ብሩ የግንቦት 7  የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ስራ አስፈጻሚ አባል፤ አቶ ዮሃንስ አለሙ ዊ ለውጥ  በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዎይ  ዋና ሊቀመንበር እና ዶ/ር ሙሉአለም አዳም  የዲሞክራሲያዊ  ለውጥ  በኢትዮጵያ ድጋፍ በኖርዎይ የድርጅት አባል በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ
ተከናል። በዝግጅቱ ላይ በመቶዎች የሚገመቱ ከተለያዩ የኖርዌ ከተሞች የተሰባሰቡ ኢትዮጵያውያን ተሳታፊ ነበሩ።
የውይይት መድረኩ ከመጀመሩ በፊት በሳውዲ አረቢያ እየተሰቃዩ፥ እየተገደሉ እንዲሁም በግፍ ኢሰብአዊ ድርጊት ለተፈፀመባቸው ወገኖቻችን የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ የተጀመረ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዎይ  የበርገን  ቅርንጫፍ / ሰብሳቢ አጭር የመክፈቻ ንግግር ካረጉ በኋዋላ ተጋባዥ እንግዶቹ በየተራ ስለሚመሩአቸው ድርጅቶችና የወቅቱን የሃገራችንን አስከፊ የፖለቲካ ሁኔታ በተመለከተና ሁሉም የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች አብረው በስምምነት የሚሰሩበትን ሁኔታ እንዳለብን እንዲሁም ስለ  መደራጀት አስፈላጊነት ሰፋ ያለ ማብራርያ  ሰጥተዋል፥፥
/ ታደሰ ብሩ ስለ ግንቦትየፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዓላማ ራእይና ግብ እንዲሁም ስለውጭ እምቢተኝነት ሰፋ ያለ ማብራሪያ ከሰጡ  በኋላ ሁሉም ኢትዮያዊ ግንቦት7ትን እንዲቀላቀልና ሃገራችን ኢትዮጵያ ከገባችበት አዘቅት ውስጥ ተባብረን እንታደጋት በማለት  ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በተለያዩ ድርጅቶች ስር ተደራጅቶና ታቅፎ መንቀሳቀሱ ያለውን ጠቀሜታና የሐይማኖትና የሲቪክ ማህበራትን ማደራጀትና ማጠናከር ጠቃሚ መሆኑን አሳስበዋል አቶ ዮሃንስ አለሙ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ  ዋና ሊቀመንበር ስለ ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ አመሰራረትና የደረሰበትን ደረጃ እንዲሁም ያከናወናቸውን ተግባራት በተመለከተ በሰፊው ገለጻ ያደረጉ ሴሆን ከህዝቡም ለቀረበላቸው ጥያቄም  ምላሽ ሰጥተዋል
በተጨማሪም / ሙሉዓለም አዳም ሁሉም የተቃዋሚ ድርጅቶች አንድ ላይ ሆነው እንዲሰሩ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን በመጨረሻም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌ የበን ቅርንጫፍ በተቋቋመ  በአጭር ግዜ ውስጥ የደረሰበት ደረጃም በጣም አስደሳች እንደሆነ በመግለፅ ለነፃነት በሚደረገው ትግል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል።

እንዲሁም በዝግጅቱ ላይ አጭር ግጥም የቀረበ ሲሆን በመቀጠልም በሎሚታ ገብረሚካኤል በምስል ተደግፎ በቀረበው የኢትዮጵያ የታሪክ ጉዞ ከነገስታት ስርአት እስከ ሐገራችን በወያኔ አገዛዝ ስር ወድቃ አሁን የደረሰችበትን ሁኔታ የሚያሳይ ዘገባ ለታዳሚው ቀርቧል
በመጨረሻም ለእንግዶቹ የተለያዩ ጥያቄዎች ቀርቦ ውይይት ከተደረገ በኋላ ዝግጅቱ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሐይል መዝሙርን በመዘበር በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
ዲቦራ ለማ 
ኖርዌ/ቬስትነስ

No comments:

Post a Comment