Monday, November 25, 2013

ህወኃት ወያኔ በሳዉዲ ዜጎቻችን ብቸኛ ተጠያቂ ነዉ


Author Roba Pawlos
ሮባ ጳዉሎስ
ኢትዮጵያ የህዝቦችዋ መኖርያና ሀገሪቷ ለህዝቦችዋ መሆንያለባትን እንዳትሆን ላለፉት ፪፪ አመታት ሲወጠን እና ሲደረግ የነበረ የኢሰብአዊና አረመኔያዊ የህወኃት ወያኔ የገማ የዘር ፓለቲካ ዉጤት መልስ ነዉ በሳዉዲ አረቢያ በዜጎቻችን ላይ የተፈፀመዉ መታረድና መደፈር።
እኩልነት መቻቻል ሰላም ፍትህና ነፃነት ዜጎችን በመከልከል በሀይማኖት በዘርና በጎሣ በመከፋፈል እየነጠለ በመምታት እንዲሁም ለይቶና ረግጦ መግዛት የማይችልባቸዉን ቦታዎች በኢንቨስትመንት ስም ለዉጪ ወራሪዎች በመስጠት ዜጎችን በዘመናዊ ባርነት ስር በመጣል ከገዛ መሬታቸዉ በማፈናቀልና በማሳፈን ሀገሪቷ ላይ ያለዉን የስራ እድል ለዉጭ ወራሪዎች እና ለገዳዮቻችን የሳውዲ ዜጎች ጭምር በመስጠት ወጣቱን ገሎ አስሮ አሰድዶ አዋርዶናል።በዚህ ስቃይ ዉስጥ ሀገሪቷ ላይ መኖር እና የመስራት ተስፋ ያጡ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን የገማ እና የበሰበሰ የህወኃት ፓለቲካ ሽሽት ጭምር ያላቸዉን ብቸኛ አማራጭ በመጠቀም በህጋዊም ሆነ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ዜጎቻችን ያለጠያቂ በአለም ላይ ተበትነዋል።ከዚህም ዉስጥ በብዛት ሴት እህቶቻችን የሚኖሩባት እና ህወኃት ወያኔ እራሱ በዘመናዊ ባርነት ተስማምቶ በፓስፓርት ጭምር ወደ ሳዉዲ አረቢያ የላካቸዉ ዜጎቻችን ተጠቃሽ ናቸዉ። ኢትዮጵያዉያን እህትና ወንድሞቻችን በአረብ ምድር ላይ እስራኤል የመን እና ግብፅን ጨምሮ አስከፊ ችግር እና የህይወት መስዋእትነት ሲከፍሉ የህወኃት ወያኔ መንግስት የሚፈልገዉና የዜጎቻችን በአረብ ሀገር መታረድ የሸተተ የፓለቲካዉ እድሜ ማስቀጠያ ዉጥን ሴራ ስለሆነ ዝም ሲል የኖረና የሳዉዲ አረቢያን ዘግናኝ ድርጊት የደገፈዉ፣ያስጀመረዉም ህወኃት ወያኔ ነዉ ።
በሌላም በኩል ዜጎቹ በሕገ-ወጥ ደላሎች አማካይነት በሁሉም የጎረቤት አገሮች በኩል ወደ ተለያዩ ሀገራት በመሰደድ መጉላላትና አደጋ ሲደርስባቸው የወያኔ/ህውሃት የሕገ-ወጥ ደላሎች ቁጥር መጨመሩን በልማታዊ ጋዜጠኞቹ በሚዲያው ከሚነግረን በቀር ጉዳዬ ብሎ ችግሩን ከምንጩ ለመቅረፍ የሚወስደው እርምጃ ባለመኖሩ መንግሥታዊ ኃላፊነቱን መወጣት ያቃተው መሆኑ በግልፅ አሳይቶናል፡፡
በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ በየሀገሩ የሚደርሰው ሰቆቃ አዲስ ባይሆንም በቅርብ ግዜ ወዲህ በማዕከላዊ ታንዛኒያ በጫካ ውስጥ ተጥለው የተገኙ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ እጅግ በጣም አሳዛኝና አስደንጋጭ ነው፡፡ እነዚህ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከሀገራቸው ከወጡ በኋላ በማላዊ አቆራርጠው ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ሲሉ በኮንቴይነር ተጭነው በታንዛኒያ በኩል ሲጓዙ አየር አጥተው በመታፈናቸው 43ቱ ሕይወታቸው ሲያልፍ በርካቶቹ ለጉዳት ተዳርገዋል፡፡ ይህ ድርጊት የወያኔ/ህውሃት መንግሥት በካድሬያዊ የአፈና አገዛዙ ከቀዬአቸው እያፈናቀለ በሰው ሀገር ለስቃይ የሚዳርጋቸው ዜጎች ስፍር ቁጥር የሌለው መሆኑን ማሳያ ነዉ።
ግንዛቤ ማጣትም ሆነ ገንዘብ ማጣት ሁለቱም ደህነት ነው፡፡ ስደት በየትም አልነው በየትም አሽሞነሞነው ስደት ድህነት ነው፡፡ ድህነት ደግሞ የብልሹ ፖለቲካ ስርዓት ውጤት ነው፡፡ ሰላም አጥቶ መብቱ ተረግጦ የሚሰደደው ኪሱ የዳለበውም ቢሆን የሰላም ደሀ ሆኖ ነው፡፡ ሌላ ታፔላ መለጠፉም ሆነ ማሽሞንሞኑ ስደትን አያጠቁረውም አያቀላውም፡፡ ጥናት አጥንተናል ባዮችም ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ እንዲሉ ነውና ይልቅ የመፍትሄ ሀሳብ አቅርቡ…ህገ-ወጥ ደላሎች ያላቸውን ተዋረድ እና ሰንሰለት መናገሩ ብቻ ምን ፋይዳ አለው፡፡ እዚህ የመን፣ሳውዲ ያለ ኤምባሲ ስንት የሚያዙትን ህገ-ወጥ ደላሎች ሲፈቱ ዝም ከማለት ውጭ ምን አደረገ? አሁን በቅርቡ ያየነው እንኳን ስልሳ ኢትዮጵያዊያንን አፍኖ የተያዘ ሰው ሲፈታ ዝም አይደል ያሉት ፡፡ አሁንስ ቢሆን በየመን ህገ-ወጥ አጓጓዦች ከኤምባሲው ምን ደረሰባቸው ገብተው ይወጣሉ፡፡ እጅና ጓንት ናቸው፡፡ የመንግስት ስራ ሁሉ የይምሰል ነው፡፡
በመጨረሻም ወያኔ የሳዉዲዉ የዜጎቻችን በደል የራሱ ስራ ስለ ነበረ ከችግሩ ተርፈዉ በተመለሱና ልጆቻቸዉ የታረዱ ባቸዉን እናትና አባቶች ጭምር ለተቃዉሞ በወጡበት በገዛ ሀገራቸዉ እንደ እባብ የቀጠቀጠዉ ያሳዝናል ያቃጥላል ያንገበግባል ነገር ግን የዜጎቻችን እንባና ደም በከንቱ ፈሶ አይቀርም።
ሞት ለሀይለማርያም ደሳለኝ ሞት ለቴዉድሮስ አድሀኖም ሞት ለህወኃት ወያኔዎች።

No comments:

Post a Comment