Sunday, April 28, 2013

! ….. ሰበር ዜና፡ የ አስገደ ገብረስላሴ ልጅ ቶርቸር እየተፈፀመበት ነው …….!

By zenebu on

አሕፈሮም አስገደ (የኣስገደ ገብረስላሴ ልጅ) መታሰሩንና ቤተሰቦቹ እንዲያዩት እንዳልተፈቀደላቸው ፅፌ ነበር። ከሰዓታት በፊት ግን አባቱ ኣቶ አስገደ ገብረስላሴ ልጁ እንዲያሳዩት የፖሊስ ኣዛዦችን ይጠይቃል። ፖሊሱ (የቀዳማይ ወያነ ወረዳ ኣዛዥ ኮነሬል ….. ዋና ኢንስፔክተር) ልጁ ወደ ሌላ እስርቤት መዛወሩ (ከማስፈራርያ ጋር) ነግሮታል።“ወደ የትኛው እስርቤት ተዛወረ ?” ብሎ ሲጠይቅ ኣስደንጋጭ መልስ ተሰጠው፤ “ወደ ባዶ ሽዱሽተ እሰርቤት” የሚል። “ባዶ ሽዱሽተ” (06 ዜሮ ስድስት) እስርቤት የህወሓት እስርቤት ነው። ህወሓቶች ተሰቃይቶ መረጃ እንዲሰጥ የሚፈለግ ሰው ሲገኝ ወደ “ባዶ ሽዱሽተ” ይወሰዳል። ከዛ ቶርቸር ይፈፀምበታል፤ በመጨረሻም ይገደላል (ይረሸናል)። “ባዶ ሽዱሽተ” የስቃይ እስርቤት ነው። ይሄ እስርቤት ህወሓቶች ጫካ እያሉ የሚጠቀሙበት የነበረ ነው።
ko
እስካሁን ድረስ ይሄ እስርቤት መኖሩ ገርሞኛል። (ህወሓቶች ስልጣን ይዘው እያሉም …. ለምን ኣስፈለገ???) ልጁ ቤተሰቦቹና የሕግ ኣማካሪው እንዲያዩት ያልተፈቀደው በቀዳማይ ወያነ ወረዳ ማረምያ ቤት ስላልነበረ ነው። ወላጆቹ ይሉክለት የነበረው ምግብ (ካለፈው እሮብ ጀምሮ) ለልጁ ሳይሰጥ በእስርቤቱ ተበላሽቶ ይገኛል።ሰው እንዲያየው ያልተፈቀደው ያለበት እስርቤት (ባዶ ሽድሽተ) ሕጋዊ ስላልሆነ ነው። በመቀለ ከተማ የሚገኙ ሕጋዊ እስርቤቶች ሰባት ብቻ ናቸው። “ ባዶ ሽድሽተ” ግን ሕጋዊ አይደለም፤ ፍርድቤት አያውቀውም። ወደዛ የገቡ እስረኞ ች ያለፍርድ ቶርቸር (ግርፋት) ይደርሳቸዋል (በቶርቸር ህይወታቸው ሊያልፍ ይችላል)።ባጭሩ “ ባዶ ሽድሽተ” ለቶርቸር ብቻ የተዘጋጀ ሕቡእ (hidden) እስርቤት ነው። አንዳንድ ስለ እስርቤቱ (እስካሁን መኖር የሚያውቁ) የመቐለ ኗሪዎች “ቤርሙዳ” ብለው ይጠሩታል: “እዛ እስርቤት የገባ መውጭያ የለውም” ለማለት። ። ይሄን ሕቡእ፣ ንፁህ ዜጎች የሚሰቃዩበት እስርቤት (ባዶ ሽድሽተ) ሚላኖ ሆተል አከባቢ ከባሎኒ ስታዲዮም ወደ ምስራቅ 100 ሜትር ገባ ብሎ፣ ጀወርግስ ቤተክርስትያን፣ ወደ እንዳየሱስ (ኣሪድ ግቢ መቐለ ዩኒቨርስቲ) ጠጋ ብሎ በሚገኝ (ተራራና ሸለቆ የበዛበት) ጫካ ያለበት ስፍራ ሲሆን underground prison ነው።በኣሁኑ ሰዓት እየተገረፈ እንዳለ መስማቴ ኣሳዝኖኛል። ለምን underground እስርቤት? ለምን ሕጋዊ ያልሆነ እስርቤት????
አሳዛኝ ነው።
! ….በለው ! ማስፈራራት ተጀመረ …..!

ይሄው ሓሳባችንን በገለፅን ፌስቡካችንን (ኣፋችን) ለመዝጋት ተረባረቡ። ተሳካላቸው። ፌስቡካችን DISABLED ሆነ። ከዚህ የምንረዳው ነገር ቢኖር ገዢዎቻችን በፌስቡክ ፅሑፎቻችን መሸበራቸው ነው። የኔ ፌስቡክ መዝጋት መፍትሔ የሚሆን ኣይመስለኝም። (ፓስፖርቴን በመላክ በራሴ ስም እንደምጠቀም ለማስረዳት ሞክርያለሁ። እንደሚከፈትልኝ ተስፋ ኣለኝ። )

በዚሁ ኣላቆሙም። እየደወሉም …….. ማስፈራራት ተያይዘውታል።በትግራይ የሚከናወኑ የፍትሕ ችግሮችና ሙስና ባጋለጥኩበት ፅሑፌ ብዙ ማስፈራርያዎች እየደረሱኝ ነው። የትግራይ ህዝብ ተጨቁኖ ሲያበቃ ጭቆናውን እንዳይጋላጥ መታፈን ኣለበት እንዴ??? ቢቻል ቢቻል ……. ህዝብ መጨቆን ተገቢ ኣይደለም፤ መቆም ኣለበት። ካልሆነ ግን በህወሓት መጨቆናችንና መታፈናችን ሌሎች ወንድሞቻችን ቢያውቁልን ምንድነው ችግሩ???ህወሓት ድጋፍ እንዳያጣ ተብሎ እኛ እንሰቃይ? የትግራይን ህዝብ የፍትሕ ጉድለቶች ማጋለጥ ማንነት መለወጥ ኣይደለም። እንደኔ እንደኔ የህዝብ ዓፈናዎች ማጋለጥ ለህዝብ ነፃነት መቆም እንጂ የህዝብ ጠላት መሆን ኣይደለም። የህዝብን ጠላትነት የሚገለፀው ህዝብን በመጨቆን እንጂ የህዝብን በደል በማጋለጥ ኣይደለም።ማስፈራርያው ……. (ከተወሰነ ውይይት በኋላ ችግር መነሩ ኣምኖ) “ምስጢራችንን እያጋለጥክ ለጠላቶቻችን መሳርያ እየሆንክ ነው (ምሽጥርና እናቃላዕኻ ኣደዳ ፀላእትና ኣይትግበረና)።” የህዝብ ‘ጠላቶች’ መኖራቸው እርግጠኛ ኣይደለሁም (የገዢው ፓርቲ ጠላቶች ሊኖሩ ይችላሉ)።ደግሞ ቢኖሩስ??? ‘ጠላቶች’ እንዳይሰሙ፣ ገመናችን እንዳያውቁ ተብሎ ይበልጥ መታፈን ኣለብን? መሪዎቻችን እንደፈለጉ ይጫወቱብን? ጠላቶች እንዳይሰሙ ተብሎ ህወሓቶች እንደፈለጉ ይጨቁኑን??? በዚ ኣልስማማም።
ገመናቹ እንዳይጋለጥ ከፈለጋቹ ጥሩ መስራት ኣለባቹ፤ ፍትሕ ማስፈን ይጠበቅባችኋል፣ ለሰዎች ነፃነት መፍቀድ ይኖርባችኋል። ለችግሩ መፍትሔ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት እንጂ ዓፈናን የሚያጋልጡ መረጃዎች እንዳይወጡ ማፈን ኣይደለም። ዜጎች መጨቆን ብሎም ጭቆናውን እንዳይጋለጥ ማፈን ችግሩን ማባባስ ነው።
ጭቆናን ስላጋለጥኩ የህዝብ ጠላት ተባልኩ፤ ህዝብን የሚጨቁኑ ደግሞ የህዝብ ወዳጆች ተባሉ። እንዴት ነው ነገሩ??? ህዝብን የበለጠ ለመጨቆን (በስልጣን ለመቆየት) ድጋፍን ያሰባስባሉ። ድጋፍ ኣግኝቶ የስልጣን ዕድሜ ማራዘም የኣንድ ህዝብ የህልውና (በነፃነት የመኖር) ዋስትና ሊሆን ኣይችልም። የህዝብ ዋስትና ፍትሕ ማስፈን ነው። ፍትሕ ለማስፈን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት ያስፈልጋል። ነፃ፣ ገለልተኛና ጠንካራ የመንግስት የፍትሕ ተቋማት መዘርጋት ኣለባቸው።
እንደውጤቱም የህዝብ መብት ይከበራል፤ ሰው ለነፃነቱና ህልውናው ዋስትና ያገኛል። ኣሁንም ኣልመሸም። ችግሩን ማቃለል እንጂ ሓሳባቸው በነፃነት ለሚገልፁ ዜጎች ማስፈራራት ግን መፍትሔ ሊሆን ኣይችልም። እኔ ስላስፈራራቺሁኝ መፃፌን ባቆም ችግሩ ኣቆመ ማለት ኣይደለም። እኔ ባልኖር ሌሎች ይፅፉታል።
! …… የመተካካት ሙስና በህወሓት …….!

ጥያቄ“የምትፅፈው ነገር የተወሰነ እውነት ኣለው። ግን ከውጭ ሁኖ ህወሓት ለት ተቀን ከመውቀስ በህወሓት ውስጥ ሁነው ማስተካከል ኣይሻልም?” (ኣንድ የህወሓት ኣባል)።መልስኣንድህወሓት በቤተሰባዊነትና ሙስና (ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ) የተጨማለቀ ድርጅት ሆነዋል። ኣብዛኛው መዋቅሩ በስብሰዋል። በቀላሉ ሊስተካከል የሚችል ኣይደለም። የመዋቅር ሙስናው በጭቃ እንመስለው፤ ኣብዛኞቹ የህወሓት ባለስልጣናት በሙስና (በጭቃው) ተጨማልቀዋል። ይሄንን ለማስተካከል ታድያ በ’መተካካት’ ስም ኣዲስ ሰው ወደ ጭቃው በመወርወር ጭቃው ማስወገድ ኣይቻልም። የሚያስፈልገው ኣዳዲስ ሰዎች ወደ ጭቃ መክተት ሳይሆን ጭቃው ማስወገድ ነው።
ሁለት
በህወሓት ዉስጥ ግለሰዎች ድርጅቱን የማስተካከል ዕድ ል ኣያገኙም። ምክንያቱም ድርጅቱ ከተዘፈቀበት ዓዘቅት ለማስወጣት ባለ ኣዲስ ራእይ ኣዲስ ወጣቶች፣ ኣዲስ ኣመለካከትና ኣሰራር ኣስገብተው ድርጅቱን መምራት ኣለባቸው። ኣሁን ያለው የህወሓት ኣመራር ይሄንን ይፈቅዳል???
በህወሓት ኣዲስ ራእይ (የራሳቸው ራእይ) ያላቸው ወጣቶች (የፖለቲካ ዓቅም ያላቸው ባለ ራእይ ወጣቶች) የህወሓት ጠላቶች ተደርገው ይቆጠራሉ። የህወሓት ኣባል የሆነ ሰው የራሱ ራእይ ሊኖረው ኣይገባም። ምክንያቱም የራሱ ራእይ ካለው እንዴት የራሱን ትቶ የመለስን ራእይ ለመተግበር ይሯራጣል? ኣሁን የሚፈለገው ‘የመለስ ራእይ’ የሚተገብር ብቻ ነው። ሙሉ በሙሉ የመለሱን ለመተግበር የራሱ ባይኖረው ይመረጣል።
ባለፈው ጉባኤያቸው ተሳታፊዎችን ሲመለምሉ የፖለቲካ ታማኝነት (በዝምድናና ኣመለካከት) ዋነኛው መስፈርት ነበር። ታማኝነት የሚገለፀው ‘የመለስን ራእይ እንዳለ ሳይከለስ ሳይበረዝ ለማሳካት’ የተዘጋጀ ነው። የራሱ ሓሳብ ማፍለቅ የሚችል (የፖለቲካ ዓቅም ያለው) ኣባል ኣይፈለግም (በጉባኤም እንዲሳተፍ ኣልተመረጠም)፣ ሓላፊነትም ኣይሰጠውም። ብቃት ያላቸው ወጣቶች ቦታ (ሓላፊነት) ካልተሰጣቸው እንዴት ውስጥ ገብተው ማስተካከል ይችላሉ? በህወሓት ውስጥ ጥሩ ከሚሰራ ሰው ይልቅ ለኣለቆቹ ውሸት የሚያመላልስ ኣቃጣሪ የበለጠ ተጠቃሚ ነው።
እነ ኣርከበ ዕቁባይ ቡድን የተመታበት መንገድ ….. እነዚህ ሰዎች የራሳችን በራሳችን ኣካሄድ እንስራ በማለታቸው ‘የመለስን ራእይ በራሳቸው ለመቀየር ጥረት እያደረጉ ናቸው’ በሚል ነበር። ኣሁን ያሸንፈው ቡድን የራሱ የሆነ ራእይ (የኣመራር ብቃት) ስለሌለው ‘የመለስ ራእይ እናሳካለን’ እያለ የሚዘምር ነው። ‘የመለስ ራእይ’ ምንድነው የሚለውን ጥያቄ እንኳ መመለስ የማይችል ነው። ኣብዛኞቹ የኣሸናፊው ቡድን ኣባላት በመለስ ግዜ በተለይ በ 1993ቱ የክፍፍል ግዜ ከመለስ ጎን ተሰልፈው ያ ተገንጣይ ቡድን እንዲ ሸነፍ የረዱት ስለሆኑ በፖለቲካዊ መዋቅሩ በብዛት ነበሩ።
ሦስት
ህወሓት በምን መልኩ ማስተካከል ይቻላል??? በመተካካት? ኣይመስለኝም። ለመሆኑ ‘መተካካት’ ምንድነው? መስፈርቱ ምንድነው? ብቃት? ዕድሜ ? የስልጣን ሲኔሪቲ? ወይስ የትግል ቆይታ (Former Fighter vs Civil)? ህወሓቶች የመተካካት መርሁ ወይ ሂደቱ ግልፅ ለማድረግ ኣልፈለጉም። ምክንያት ኣላቸው። የመተካካት መርህ መተግበር ስላስፈራቸው ይመስለኛል። በመልስ ግዜ (ከሁለት ዓመት ተኩል በፊት በነበረ ግባኤ) መተካካት በዕድሜና በስልጣን ሲኔሪቲ እንደሚሆን ሂንት ተሰጥቶን ነበር።
ከመለስ ሞት በኋላ መተካካት በትግል ዕድሜ እንደሆነ ተነገረን (የድሮ ታጋዮች በኣዲስ ትውልድ እንዲተኩ ማድረግ)። ይህን መስፈርት በኢህኣዴግ ደረጃ እየተሰራበት ያለ ይመስላል። በህወሓት ግን ተቀባይነት ኣላገኘም። ለዚህ ነው የህወሓት ሊቀመንበርና ምክትሉ እንዲሁም ሁሉም የስራ ኣስፈፃሚ ኣባላት የድሮ ታጋዮች የተመረጡት። በማእከላዊ ኮሚቴ ኣባላትም ከ45ቱ 9 ብቻ ናቸው ሲቪል።
‘መተካካት’ መቀያየር ወይ መሸጋሸግ ሆነ። እርስበርሳቸው ይቀያየራሉ። ኣንድ በልቶ የጠገበ የድሮ ባለስልጣን በሌላ ሆዱ ያጠበ ይቀየራል። ያልበላ ይበላል። ሁሉም ግን ኣንድ ናቸው። የተለወጠ ነገር የለም። የፖለቲካዊ ኣቅጣጫ ወይ የፖሊሲ ለውጥ ኣይኖርም። ምክንያቱም ሁሉም የነበረ ነው፣ ‘የመለስ ራእይ’ ለመተግበር ተዘጋጅተዋል። (የራሳቸው ከየት ያመጣሉና!)።
ለስልጣን ሲታገሉ ራሱ ‘እኔ ብዙ ዓመት የታገልኩ ነኝ። ስለዚ ስልጣን ይገባኛል’ ይላሉ (እኛ መተካካት ስንጠብቅ)። ባጠቃላይ ግን በህወሓት ‘የመተካካት መርህ’ ከሽፈዋል። እነዚህ ከስልጣን የወረዱም ቢሆኑ ተሸንፈው እንጂ ወደው ኣይደለም ስልጣን የለቀቁ። የሚገርመው ደግሞ ታጋዮቹ ሄዱ፣ ታጋዮቹ መጡ። ወጣቶች ሳይመረጡ ቀሩ።
ኣራት
ኣሸናፊው ቡድን (የነ ኣባይ ወልዱ) ማሸነፉ፣ ባቀደው መሰረት ጉባኤው መከናወኑ የራሱ ኣባላት እየመሰከሩ ናቸው። ትናንት ማታ ብርሃነ ኪዳነማርያም (የማእከላዊ ኮሚቴ ኣባልና የጉባኤው ቃል ኣቀባይ)ና ትርፉ ኪዳነማርያም (ስራ ኣስፈፃሚ ኣባል) ከVOA ትግርኛ ጋር ቃለ መጠይቅ ባካሄዱበት ግዜ ጉባኤው ባለሙት፣ በጠበቁበት፣ በፈለጉት ‘በድል መጠናቀቁ’ ጠቁመዋል። እኔም የተለየ ሓሳብ የለኝም። ኣዎ! እነሱ ባደራጁት መሰረት ኣሸናፊ ሁነው ወጥተዋል። (ኣርከበ “ሽልማት ኣልቀበልም” ብሎ ሳይገኝ ሲቀር ኢቲቪ “ኣቶ ኣርከበ በስራ ምክንያት ሳይገኙ ቀርተዋል” ኣለን። ይገርማል።)
‘ትርፉ ኪዳነማርያም …. የባለስልጣን ሚስት (የኣባይ ወልዱ) ስለሆነች ነው የተመረጠች የሚል ነገር ኣለና እንዴት ታይዋለሽ?’ ብሎ ሲጠይቃት፣ ‘እንደዚህ ልንባል ከሆነ ታድያ ለምን ዕድሜ ልካችን ተታገልን? የተታገል’ኮ ለእኩልነት ነው።’ ኣለች። ጋዜጠኛው ኣስከትሎ ‘ብዙ ታጋይ ሴቶች ነበሩኮ በማእከላዊ ኮሚቴ የተመረጡት ግን ስምንት ብቻ ናቸው’ ኣላት። ትርፉም ‘ የትምህርት ጉዳይ ኣለ፣ የፖለቲካዊ ኣቅጣጫ ግንዛቤ ኣለ፣ የፓርቲው values ማወቅ ነገር ኣለ …. (ምናምን)’ ኣለች። ዓቅማቸው በሚፈቅድላቸው በዞን ኣስተዳደርና በፓርላማ እንደሚሳተፉም ገልፃለች።
ከዚህ የምንረዳው ነገር እነዚህ የድሮ ታጋዮች (ለምንድነው የታገልነው ታድያ? እያሉ ) ስልጣን ለወጣቱ ትውልድ ለማስረከብ ዝግጁነት እንደሚያንሳቸው ነው። ሌላው ለእኩልነት የታገሉ ሴቶች እነዚህ የባለ ስልጣን ሚስቶች ብቻ ናቸው እንዴ??? በሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች ለእኩልነት ታግለዋል። ስልጣን ለመያዝ ግን የባለስልጣን ሚስት መሆን ኣስፈላጊ ሳይሆን ኣይቀርም። (ኣዜብ የመለስ፣ ፈትለወርቅ የኣባይ ፀሃየ፣ ቅዱሳን ነጋ የፀጋይ በርሀ፣ ትርፉ የኣባይ ወልዱ፣ ሮማን ገብረስላሴ የተወልደ ዓጋመ …….) ኣብዛኞቹ ስልጣን የያዙ ሴቶች ከባለስልጣን ወንዶች ጋር የደም ወይ የጋብቻ ዝምድና ኣላቸው።
ሌላው የትምህርት ደረጃ ኣንስታለች። ከትርፉ ያነሰ የትምህርት ደረጃና የፖለቲካ እውቀት ያላት ታጋይ ሴት የምታውቁ ከሆነ ኣስረዱኝ። ይሄ ንቀት ነው ወይ ስልጣን ላለማስረከብ ተብሎ ነው። ብዙ ጎበዝ ሴቶች ኣሉ፣ ቦታ ያላገኙ።
ኣምስት
ህወሓት ብቃት ላላቸው ወጣት ሙሁራን ፈተና ነው። ደሞ ወጣቶች ገብተው ምን ሊያስተካክሉ ነው? ፖሊሲው፣ ራእዩ፣ ኣሰራሩ ምናምኑ ኣይስተካከልም ተብሏል። የመልስ ራእይ ብቻ ማስፈፀም። ስለዚ ኣይስተካከልም። በህወሓት ከተሳካልህ ልታገኘው የምትችለው ነገር ኢኮኖሚያዊ ጥቅም (በሙስና) ወይ ፖለቲካዊ ስልጣን (ከነሱ በ ደም ወይ ጋብቻ በመዛመድ) ነው። ሃብትና ስልጣን ነፃነት ሊያመጣ ኣይችልም። ነፃ ለመሆን ከሞከርክ ታገኛታለህ!!!
ስድስት
በሙስና በበሰበሰ ስርዓት ‘የመተካካት መርህ’ ዉጤት ኣያመጣም። ምክንያቱም መሪዎቹ በሙስና ከተዘፈቁ ብቁና ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ተተኪ ወጣት የመመረጥ ዕድሉ ኣነስተኛ ነው። ወጣት ተተኪዎቹ ማነው የሚመርጣቸው? ኣለቆቻቸው ናቸው (ገምግመው የሚያቀርብዋቸው)። ሲመለምሉ ታድያ ለነሱ ታማኝ ሁኖ ያገለገለ፣ ሙስና ሲበሉ የማያጋልጣቸው (ወይም የተባበራቸው ……. ኣብሮ ሙስና የበላ ቢሆን ይመረጣል ምክንያቱም በኋላ እንዳያሳስራቸው)፣ የነሱ ዘመድ የሆነ (እንደማይጥላቸው የሚተማመኑበት)፣ ባጭሩ የራሳቸው ኣምሳያ ተክተው ይሄዳሉ (ተተኪዎች የመመልመል ስልጣን ስለተሰጣቸው)።
ስለዚ መተካካት እንኳ ቢደረግ (ዘሮ ዘሮ ከእጃቸው ስለማይወጣ) ስርዓቱ የሚፈለገው የመልካም ኣስተዳደርና የኢኮኖሚ ልማት ማስመዝገብ ኣይቻለውም። ለውጥ ለማምጣት መጀመርያ ሙስና ማጥፋት ኣለባቸው፤ ሙስና ካጠፉ ደግሞ ገዢው ፓርቲ ጠፋ ማለት ነው። ምክንያቱም ፓርቲው የተገነባ በሙስና ነው። ግንቡ ከፈረሰ ፓርቲው ወደቀ ማለት ነው።
ወይ ሙስና! ደግሞ ህወሓት ምኑ ሊስተካከል???!!!
ሰባት
ባለፈው ዓመት ስለ ሙስና ኣስፈላጊነት በህወሓት የፃፍኩት እነሆ:
“It is true that you should not only be members of the ruling party but also very loyal ones …. in order to get ‘good’ jobs and ‘promising’ titles. As the government’s administrative structure is being used for party purposes, corruption (besides nepotism) has become the best (for carrot and stick) strategy of the ruling party in order to play with its members.
Corruption serves both ways: to pull members in (to the party) and push them out (of the party). Party officials directly or indirectly promise individuals that … When they join (and/or remain loyal) to the ruling party, they may get material benefits such as access to more jobs, money, power or whatsoever. Such discrimination by itself is corruption. Then corruption helps them to get more members.
When the officials want to ‘cheat’ their members, they allow (or encourage) them to engage themselves in corruption. This strategy of creating ‘conducive’ environment for new members to share the advantages of corruption helps the top officials in three ways:
(1) Through corruption, members may satisfy their own personal interests by having more material benefits. Here, corruption is serving as a pulling factor (carrot) for new members to join to the party thereby strengthening and lengthening the life span of their party.
(2) With corruption, the top officials create their own copies for when the new members become corrupt, then the possibility of (the top corrupt officials) to be exposed reduces dramatically. The new entry becomes part of the old one. Both become like-minded.
(3) If the new members are engaged in corruption, then their right to an ‘independent thinking’ is lost. These individuals would not have the chance to oppose the ruling party. If they oppose or express a different opinion, they will be charged with corruption scandals. They will be defamed and/or removed from party membership. Yet, this will not be done as long as they remain loyal to the officials.
To this end, the EPRDF party officials encourage corruption (to their members). They simply register what the new members do. Hence, corruption is important for party politics. This is why the members of the ruling party do not want to avoid it. Yet, whenever the political consciousness of the people (the ruled) rises (the people demands for good governance), the corruption scandal endangers the existence of the party in question. The people may tend to overthrow the corrupt officials.
My message goes that ……..
Dear members, please refrain from engaging yourselves in corruption. Your higher officials may keep silent for the time being (as long as you are loyal to them), but the people is watching you. I do not want you to sell your freedom for material benefits. You should always remember that EPRDF is a dying horse.
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/2515

No comments:

Post a Comment