March 21, 2013
ኢሳት በአባይ ወንዝ ላይ የሚሰራውን የህዳሴውን ግድብ ፕሮጀክት በቅርብ የሚያውቁ ሰዎችን ዋቢ በማድረግ እንደዘገበው ግድቡን እየገነባሁ ነው ከሚለው ሳልኒ በመቀጠል ከፍተኛ የሆነ ትርፍ የሚያገኘው ኦርቺድ፣ ከየትኛውም ድርጅት ጋር ሳይወዳደር በእነ አዜብ መስፍን አማካኝነት የስሜንቶና ማሸንሪዎች አቅራቢ ሆኖ ቀርቧል ብሏል።
ይሄው ኩባንያ ቦዲ ዋይዝ ጂም፣ ካፌ ፓኒኒ፣ ኦርቺድ ጄኔራል ኮንትራክተር፣ ኦርቺድ ትራንስፖርት፣ ኦርቺድ ትራንዚት፣ ኦርቺድ ማሽነሪ ሬንታል፣ ኤስ ኤንድ ኤስ እርሻ፣ ሂላል ቱር ኤን ትራቭል፣ ሜትሮሉክስ ፍላወር፣ ናይል ስፕሪንግ ውሀ፣ ሬንቦው ጊፍት ሾፕ፣ ሪል ሳልን፣ ወንደር ዊሌ ቢዝነስና ሌሎችም በአዲስ አበባና በመላው አገሪቱ ታዋቂ የሆኑ የንግድ ድርጅቶችን በስሩ አቅፎ መያዙን ኢሳት በማያያዝ ዘግቧሌ።
አቲኮ ስዩም ኢህአዴግ አዲስ አበባን ሲቆጣጠር ይህ ነዉ የሚባሌ ኃብት እንዳልነበራት ታሪኳን ያጠኑ ዘጋቢዎቹ ማረጋገጣቸውን የዘገበው ኢሳት ባለፉት 20 አመታት ግን በልዩ ትዕዛዝ “ኦርቺድ” ቢዝነስ ግሩፕ የሚባል ድርጅት ተከፍቶላት ሆን ተብሎ አያሌ የግንባታ ጨረታዎችን አንድታሸንፍና በአጭር ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ ውስጥ ካለ ቱጃሮች ተርታ ለመመደብ እንደቻለች መግለጹን አውስቷል።
የህወሀት/ኢህአዴግ ባለስልጣናት በዘመዶቻቸው ስም የሚገነቧቸው የቢዝነስ ተቋማት እየተበራከቱ መምጣቱን በተደጋጋሚ ሲዘግብ እንደነበር ያስታወሰው ኢሳት የባለስልጣናትን የሀብት ምዝገባ ጨርሶ በአጭር ጊዜ ይፋ አድረጋለሁ በማለት ሲፎክር የነበረው ጸረ ሙስና ኮሚሽንም ቃሉን ለመጠበቅ እንደተሳነውና ኮሚሽኑ ባለስልጣናቱ በዘመድቻቸው ስም የያዙትን ሀብትና ንብረት ለመመዝገብ ስልጣን እንዳልተሰጠው ገልጿል።
No comments:
Post a Comment