G7 March 5, 2013
የኢትዮጵያ መንግስት ከጾታ እኩልነትና ከሰብዓዊ መብት ጥበቃ ጋር የምንሰራዉን ስራ ለመግታት እራሱ ከጻፈዉ ህገመንግስት ጋር የሚጻረር ህግ አዉጥቷል ያሉት ሚስተር ፓትሪክ በርግ አገዛዙ ነገሮችን የሚያየዉ ህዝብን ይጠቃማል ወይስ ይጎዳል ብሎ ሳይሆን ከራሱ የስልጣን ዘመን ጋር እያስተያየ ስለሆነ ከዚህ አይነት አገዛዝ ጋር ምንም አይነት ህዝብንና አገርን የሚጠቅም ስራ መስራት አይቻልም ብለዋል።
ድርጀቱን ወክሎ ከሚስትር ፓትሪክ በርግ ጋር የተወያየዉ የብሉምበርጉ ሚስትር ዊልያም ዳቪሰን ደግሞ የሲቪክ ሶሳይቲና ቻርቲ ህግ የሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ውርስ መሆኑን ተናግሮ ህጉ የወጣዉ ከመንግስት የተለየ ሃሳብ ያላቸውን ተቃዋሚዎችና ምግባረ ሰናይ ድርጅቶችን ለመቆጣጠር ነዉ በማለት አምነስቲ ኢንተርናሽናልን በመጥቀስ ተናግሯል።
በሌላ በኩል ደግሞ የሂውማን ራይትስ ዋች የአፍሪካ ክፍል ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዳንኤል በቀለ ፣ መንግስት ያወጣው የሲቪክ ሶሳይቲና ቻሪቲ ህግ ዋና ግቡ በአገር ውስጥ ካለው ፖለቲካና ሲቪክ ሶሳይቲ ስራ ጋር የተያያዘ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ መንግስት ቃል አቀባይ የሆነዉ ጌታቸው ረዳ ደግሞ ህጉ በሙስና የተዘፈቁ የሲቪክ ድርጅቶችን ለመቆጣጠር ተብሎ የተረቀቀ መሆኑን በመግለጽ፣ የወያኔን አቋም አንጸባርቋል።
No comments:
Post a Comment