Sunday, July 20, 2014

ምናምንቴዎች በሠለጠኑ ግዜ ህዝብ ያልቀሳል !!!

ኢትዮጵያ ላይ ጥቂት ምናምንቴዎች ሰልጥነው ህዝቡን እያስለቀሱት ነው። ኢትዮጵያዊያን ለብዙ ዘመን በብዙ ሃዘንና እንባ ውስጥ መኖራቸው የታወቀ ነው። የአሁኑ ሃዘን እንዲሁ ተራ ሃዘን፤ ልቅሶውም ተራ ልቅሶ አይደለም። መራር ሮሮ እንጂ። ይህን የህዝብ ሮሮ የሚሰማ መንግስታዊ አካልም የለም። በ“Global terrorist database” ውስጥ የሥም ዝርዝሩ ተመዝግቦ የሚገኘው “የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ” ነኝ የሚለው ቡድን መንግስ ነኝ ቢልም የመንግስት መልክና ባህሪይ ሊኖረው አልቻለም። ህወሃት መንግስታዊ አሸባሪ እንጂ የኢትዮጵያ መንግስት ለመሆን የሞራልም ሆነ የእውቀት ብቃት ያለው ቡድን አይደለም።
ህወሃት ከተፈጠረ ጀምሮ የብዙ ንፁህ ዜጎችን ደም አፍሷል። ብዙ ዜጎችን ለስቃይ እና ለስደት ዳርጓል። ብዙ ቤተሰብን በትኗል። በተለይ ጠላቴ ነው ብሎ የሚያምነውን የአማራ ህዝብ ለማጥፋት ሴቶችን መካን የሚያደርግ ክትባት እስከ መከተብ ደርሷል። በዚህም የአማራው ቁጥር ከነበረው ቀንሶ ተገኝቷል። ይህ አሸባሪ ቡድን በኦጋዴን፤ በአፋርና በጋምቤላ የፈፀመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ዓለም ያወቀው ነው። በኦሮሚያ የፈሰሰው የንፁሃን ዜጎች ደም ከምድር ወደ ሰማይ እየጮኸ ነው። በአዲስ አበባ እና በደቡብ የተበተነውን የቤተሰብ ብዛት ቆጥረን አንዘልቀውም። በትግራይ የሚገኙ ምርጥ ኢትዮጵያውያን በሙሉ አልቀዋል። የተረፉ ጥቂቶች ቢገኙም መግቢያ መውጪያ አጥተው በሁለት ሰይፍ የሚቆረጡ ሁነዋል።
የትግራይ ነፃ አውጪዎች ያተረፉልን ነገር ቢኖር ውርደት ነው። ውረድቱ የከበዳቸው ዜጎች ራሳቸውን በእሳት አቃጥለዋል። ገደል ውስጥ ራሳቸውን ወርውረው የሞቱም አሉ። ህወሃቶች ባሉበት ከምንኖር ብለው ስደተን መርጠው የበርሃ ንዳድ፤ የባህር ዐዞ እራት የሆኑ ብዙ ናቸው። በባእዳን አገር ውስጥም ማረፊያ አጥተው የሚንከራተቱም ቁጥራችው በቀላል የሚገመት አይደለም። ይህ የህወሃት መራር ፍሬ ነው።
አዎን በአገራችን ላይ እነዚህ እግዜርን የማያውቁ የሰይጣን ድንኳኖች ከሰለጠኑ ዘመን ጀምሮ የንፁህ ሰው ደም ሳይፈስ የዋለበት ቀን የለም። ህወሃቶች የትልቁንም የትንሹንም ደም በማፈሰስ የሚረኩ፤ ቤተሰብንም በትነው ድሃ አደግ በማድረጋቸው የሚደሰቱ ፍጡራን ስለመሆናቸው የእስከዛሬው ምግባራቸው ቋሚ ምስክር ነው። ለስልጣን ካላቸው ሥሥት የተነሳም ከባዕዳን ጋር እየተመሳጠሩና ብዙ ሚሊዮን ገንዘብ እየከፈሉ ነፍሰ ገዳዮችንና አፋኞችን ቀጥረው ዜጎችን እስከማሳፈን ደርሰዋል። የዚህ ዕኩይ ተግባር ሰለባዎች ብዙ ናቸው። ታላቁ ሰው አንዳርጋቸው ፅጌ የዚህ እኩይ ተግባር ሰለባ ከሆኑ ብዙ ኢትዮጵያዊያን መካከል አንዱ ነው።
ጠላቶቻችን(ህወሃቶች) እና ወዳጆቻችን በሙሉ ስሙን ! አንዳርጋቸው የተነሳው ፡
  • ሚዛኑን ስቶ መሳለቂያ የሆነው ፍትህ ወደ ሚዛኑ ለመመለስና ፍጹም የህግ የበላይነትን በአገራችን ለማስፈን ነው።
  • የነፃነት ትርጉም ሳይገባው ስለነፃነት ሊነግረን ሳይሆን የነፃነትን ጣዕም አጣጥሞና ተርድቶ ከምር ኢትዮጵያዊያን ያለፍርሃት በነፃነት እንዲኖሩ ለማስቻል ነው።
  • ጥቂቶች ብዙሃኑን ተጭነው፤ ብዙሃኑም ጥቂቶቹን ተሸከመው መከራቸው በዝቶ የሚኖሩበት ሥርዓት ተወግዶ ሁሉም ዜጎች በእኩልነት እንዲኖሩ ለማደረግ ነው።
  • ጠባብ ጎሰኛነት ተወግዶ ሁሉም በኢትዮጵያዊነቱ ኮርቶ በሠላም መኖር የሚችልበት ንፁህ አገር እንድትኖረን ለማድረግ ነው።
  • ከዚያች ድሃ አገር ላይ እየዘረፈ በውጭ አገራት ባንኮች ውስጥ የሚደብቅ ይሄን ማድረግ ካልቻለም መሬት ምሶ የዘረፈውን ገንዘብ የሚቀብር ዘራፊ ቡድን ሳይሆን ያለውን ሁሉ ለአገሩና ለህዝቡ ለመስጠት ከልቡ ያመነ መሪ አገሪቷን የሚመራበት ሥርዓት እንዲዘረጋ ለማድረግ ነው።
  • ኢትዮጵያችን በውሸታሞች፤ ለህዝባቸው ክብር በሌላቸው፤ህዝባቸውን በሚንቁ፤ ከራሳቸውው ፍላጎት ውጪ ሌላ ወገን ህዝብ ማለትን በማያውቁ ደካሞች መገዛቷ አክትሞ ህዝቡን ፈርቶና አክብሮ የሚመራ፤ ህዝብ ላይ የሚጫን ሳይሆን በህዝብ የተመረጠና የተወደደ መሪ እንዲኖራት ለማብቃት ነው።
ግንቦት ሰባትንና መሪውን አንዳርጋቸው ፅጌን በህወሃቶች ዘንድ አሸባሪ እንዲሆኑ ያደረጓቸው እነዚህ ከላይ ለመዘርዘር የሞከርናቸው ቁም ነገሮች ናቸው እንጂ እንደ ህወሃቶች ግንቦት ሰባት ባንክ ሲዘርፍ፤ የእምነት ሥፍራዎችን ሲያወድም፤ ትምህርት ቤቶችን ሲያፈራርስ፤ የቀደመው ትውልድ በደምና አጥንቱ ያቆየውን ድንበር ቆርሶ ሲሸጥ፤ የአገሪቷን ለም መሬት ለባእዳን ሲሸጥ፤ አንዱን ጎሳ ከሌላው ጋር አጋጭቶ ደም እንዲፈስ ሲያደርግ ተገኝቶ አይደለም።
ባንክ መዝረፍ፤ የእምነት አምባዎችን ማርከስ፤ ትምህርት ቤቶችን ማውደም፤ የአገሪቷን ድንበር እያፈርሱ ለባዕዳን አሳልፎ መስጠት፤ ለም መሬቶችን ለባዕዳን መቸብቸብ፤ በህዝቦች መካከል ጥላቻን መዝራት፤ ከድሃ ጉሮሮ ላይ ሠርቆ በውጪ አገራት ባንኮች ውስጥ ገንዘብ ማጠራቀም ህወቶች እንደ ሙያ የተያያዙት የእለት ተዕለት ተግባራቸው ነው። ግንቦት ሰባት የተነሳው እንዲህ ዓይነት ነውረኞችን ከተቆናጠጡበት የስልጣን ወንበር ላይ አውርዶ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያዊያን የምትሆን አገር እንድትሆን ለማድረግ ነው። የመሪያችን የአንዳርጋቸው ፅጌም ምኞት ይሄው ነው። ኢትዮጵያን ከጥቂት ዘረኞችና ዘራፊዎች እጅ አውጥቶ የብዙሃኑ ኢትዮጵያዊ አገር እንድትሆን ማድረግ።
ይሄ የኢትዮጵያ ውድ ልጅ በነውረኞቹ የትግራይ ነፃ አውጪዎች እጅ ገብቷል። ነፃ አውጪ ነን ባዮቹ አንበሳውን ከበው ለመቦጫጨቅ እንደሚያጓሩ ጅቦች ዓይናቸውን አጉረጥርጠው እያሰቃዩት ይገኛሉ። ምንም እንኳ ይሄ ታላቅ ሰው በነፍሰ ገዳዮቹ እጅ ቢወድቅም እርሱ የጀመረው የነፃነት ጥያቄ የሚሊየኖች ጥያቄ ሆኖ ከመቸው ግዜ በላይ ሚሊየኖችን አስነስቷል። በዓለም ዙሪያ “እኔም አንዳርጋቸው ነኝ፤ እኔም ግንቦት ሰባት ነኝ” የሚሉ ድምፆች ከፍ ብለው እየተሰሙ ነው። አንዳርጋቸውን ማሰር እንጂ እርሱ የጀመረወን የነፃነት ጥያቄ፤ እርሱ የዘረጋውን የትግል መስመር ማሰር አይቻልም። ለዚህም ነው አንዳርጋቸው የማይጨበጥ ፅኑ መንፈስ ነው የሚባለው።
ግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ህወሃት የተባለው ዘረኛ እና የወሮበላዎች ቡድን የገነባው የሰይጣን ድንኳን ፈርሶ ፍትህ፤ነፃነት እና እውነተኛ ዴሞክራሲ ተገንብቶ እስከሚያይ ድረስ የጀመረውን ሁለ ገብ ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል።
የተከበራችሁ ያገራችን ዜጎች ሆይ ስሙን ! እኔም አንዳርጋቸው ነኝ ማለታችሁ አንድ በጎ እርምጃ ነው። እኔም አንዳርጋቸው ነኝ ማለት አንዳርጋቸው ራሱን አሳልፎ ለሰጠው ድንቅ ዓላማ ራሳን አሳልፎ መስጠት ማለት መሆኑንም መረዳት ያስፈልጋል። አንዳርጋቸው የቆመለትን ዓላማ ለማስፈፀም እኛ ወደ እናንተ እሰከምንመጣ መጠበቅ የለባችሁም። በያላችሁበት አምስትም ስድስትም አስርም እየሆናችሁ የአርበኝነት ተግባር መፈፀም መጀመር አለባችሁ። የቀደመዉ ትውልድ ፋሽት ጣሊያንን በየመንደሩ እየተደራጀ እና የጎበዝ አለቃ እየመረጠ መፋለሙን አስታወሱ። እናንተም ከምታምኑት ጋር እየተደራጃችሁና የጎበዝ አለቃ እየመረጣችሁ የዘመኑን ፋሽስት ልትፋለሙት ይገባል። ዘመቻ አንዳርጋቸው ማለት እኔ ለነፃነቴ፤ እኔ ለፍትህ እና ለህግ የበላይነት፤ እኔ ከዘረኞቹና ከሌቦቹ ህወሃቶች የፀዳች አገር ለመፍጠር ተነስቼአለሁ ማለት ነው። ለዚህም ዓላማ ለመሞትና ለመግደል ዝግጁ ነኝ ልትሉ ግዜው አሁን ነው። እንደ ቀድሞ ዝም ብላችሁ የምትሞቱ ሳትሆኑ ለመግደልም የምትችሉ መሆኑን በተግባር ማሳየት መቻል አለባችሁ።
“ትግሬን ነፃ” እናወጣለን ብላችሁ የተነሳችሁ እናንት ነውረኞች ሆይ ስሙ ዓይናችሁ እያየ፤ ጆሯችሁም እየሰማ ከወገኖቻችን ጎን ሁነንና እጅ ለእጅ ተያይዘን ልትገነቡ የሞከራችሁትን የዘረኝነትና የዝሪፍያ መረብ እንበጣጥሰዋለን። እናንተ ዘረኞችና ዘራፊዎች ስሙ! ህዝብን እንዳስለቀስዋችሁ መቀጠል እንደማትችሉ እርግጠኛ ሁኑ። አገራችን ኢትዮጵያም እናንተን ከመሰሉ ምናምንቴዎች ፀድታ ህዝቦቿም በነፃነት የሚኖሩበት ግዜ እሩቅ አይደለም። ያን ግዜ በእናንተ ነውሮኞች ግፍ የሚያለቅስ ህዝብ አይኖርም። አበቃን!!!
ድል ለኢትዮጵያችን ይሁን !!!!

Ethiopia-stop using “anti-terrorism” law to stifle dissent.


In 2009 a controversial anti-terrorism law (Proclamation No. 652/2009) was established in Ethiopia. The law criminalises any contact or reporting that encourages individuals or groups which the government labelled ‘terrorists.’  Since then, opposition members and journalists are convicted by the broad and ambiguous anti-terrorism law.

That proclamation has been thoroughly condemned and criticized by all of the major international human rights organization. For instance, Human Rights Watch criticized that “law” for providing “an extremely broad and ambiguous definition of terrorism that could be used to criminalize non-violent political dissent and various other activities that should not be deemed as terrorism.” Even the U.S. State Department expressed its disapproval of the “extremely harsh and politicized use of Ethiopia’s anti-terrorism law” in persecuting political opponents.

Since Ethiopia’s anti-terrorism law was adopted in 2009, the independent media have been decimated by politically motivated prosecutions under the law. The government has systematically thwarted attempts by journalists to establish new publications. Blogs and Internet pages critical of the government are regularly blocked, and in 2012 printing houses came under threat for printing publications that criticized the authorities.
Since the laws’ passing, what has precipitated is exactly what rights groups predicted. In less than four years, over 200 people have been arrested under the anti-terrorism law and more than 35 journalists and opposition leaders had been convicted of terrorism.

One of the journalists sentenced under the law who remain in prison is Eskinder Nega , a veteran Ethiopian journalist. He had been detained numerous times, and was sentenced in July 2012 to 18 years in prison for conspiracy to commit terrorist acts, as well as participation in a terrorist organization. The United Nations Working Group on Arbitrary Detention, a panel of independent experts, concluded in November 2013, that Eskinder’s imprisonment was arbitrary and “a result of his peaceful exercise of the right to freedom of expression.”

Human Rights Watch has repeatedly raised concerns about the anti-terrorism law’s overly broad definition of “terrorist acts.” The law’s provisions on support for terrorism contain a vague prohibition on “moral support” under which only journalists have been convicted.

The latest victims of this repressive policy regime seem to be six young professionals that are part of a group of bloggers called Zone 9 and three journalists. A group of Ethiopian bloggers and journalists detained for nearly three months have been charged with “terrorism” for having links to outlawed groups and for planning attacks.

On May 2, this year, the UN High Commissioner for Human Rights, Navanethem  Pillay, expressed deep concern at the arrest of these bloggers and journalists. The High Commissioner called for a reform of the country’s anti-terrorism legislation to come into line with international human rights law and stated that
“The fight against terrorism in Ethiopia cannot be used as an excuse to intimidate and silence journalists, bloggers, activists and members of civil society organizations.”|

The United States said it is deeply concerned by the Ethiopian Federal High Court’s decision to press charges against six bloggers and three independent journalists under the Anti-Terrorism Proclamation.
Human rights watch reportedly said the Ethiopian government should immediately drop politically motivated charges brought against 10 bloggers and journalists on July 17, 2014, under the country’s deeply flawed anti-terrorism law.

As many human rights groups have said, Ethiopia’s anti-terrorism “law” is merely a convenient mechanism for “politically motivated trials and convictions of opposition figures, activists, journalists, and bloggers, as well as increased restrictions on print media.”  It is State terrorism through the use of “anti-terrorism law” and violation of the rule of international law. The “war on terrorism” should not be a war on international law where anti-terrorism efforts become a convenient justification for thuggery.

The Ethiopian regime should cease using its overly broad anti-terrorism law against journalists and peaceful political activists. International actors should pay close attention to the recent, intensified crackdown of freedom of expression. Expressing critical views is not a terrorist act.  The “Terrorism” charges against bloggers and journalists are politically motivated. The fight against terrorism in Ethiopia cannot be used as an excuse to intimidate, silence and detain journalists and activists. Using “anti-terror” law to stifle peaceful dissent has to stop.

Journalism is not a crime!